Thursday 10 January 2019

በምሁራችን ተስፋ እንቁረጥ?

እስቲ ይህን የምጸሃፍ ትችት ያንብቡ፡ https://www.ethiopiaobserver.com/2019/01/06/book-review-overcoming-agricultural-and-food-crises-in-ethiopia/

የመጸሃፉ ጸሃፊ የኢትዮጵያ የእርሻ ምርት ችግር የኦርቶዶክስ ኃይማኖት ነው ይላል? ምሁራኖቻችን ከዚህ የፈረንጅ ማርክሲስት የ60 ዓመት በፊት አስተሳሰብ መውጣት አቅቷቸዋልን? ያሳዝናል።

ለ40 ዓመታት ኢትዮጵያ የተመራቸው በዚህ አይነት አስተሳሰብ ነው። የእርሻ ምርታችን እንደወረደ ነው። ታድያ አሁንም ምክንያቱ ቤተ ክርስቲያን ነው? እስቲ ምሁራን ትንሽ indoctrinate ካደረጋችሁ መጸሃፍት ውጡ እና imaginative ሁኑ። ምናልባት ወደ ወጋችን ብትመለሱ እና እሴቶቻችንን ብትመለከቱ መናባችሁ መስራት ይጀምር ይሆናል።

እስቲ ገበሬዎቻችንን እግዚአብሔር የሰጣቸውን ነጻነት እንስጣቸው። ከ43 ዓመት በፊት የነጠቅናቸውን መሬት እንመልስላቸው። ባለቤት እናንተ ናችሁ እንበል። ከዛ እንተዋቸው ድጋር ካስፈለጋቸው እንርዳቸው። እርስ በርስ መሻሻጥ ከፈለጉ ያድርጉት። ህበረቶች መፍጠፍ ከፈለጉ ያድርጉ። መንግስት/ወረዳ/ቀበሌ ጉዳያቸውስጥ አይግባ። እስቲ በዚህ እንጀምር።

ገቤሮዎቻችን የባህል እስረኞች አይደሉም። ለ43 ዓመት የመንግስት የማርክሲዝም የሞደርኒዝም እስረኞች ሆነው ቆይተዋል። በራሳቸው መሬት እና ክህሎት ኢንቬስት እንዳያደርጉ ተደርግዋል። ምሁራኖቻችን በትዕቢት የራሳቸውን ፍላጎት ጭነውባቸዋል። ከዛ ደግሞ ባህላቸውን እና ወጋቸውን ይተቻሉ! ህም።

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!