Tuesday 1 January 2019

የአማራ «ልሂቃን» እና የአማራ ህዝብ ቅነሳ

ማንም በማይክድበት ደረጃ በአማራ ክልል የተካሄደው የወሊድ ቅጥጥር (በተዘዋዋሪ የህዝብ ቁጥር ቅነሳ) ዘመቻ ከሁሉም ክልል በላይ በደምብ «ተሳክቷል»። ማለት የህዝብ ቁጥር ጭማሬ በደምብ እንዲቀንስ አድርጓል።

ይህ ለኔ እጅግ የሚያሳዝን ክስተት ነው። የአማራ ክልላዊ መንግስት በአማራ ልሂቃን ተደግፎ ያልተሟላ እና ኋላ ቀር የህዝብ ብዛት መጥፎ ነው የሚል ፍልስፍና ተሸክሞ የአማራ ክልልን ህዝባዊ አቅምን መንምኖታል። ህዝቡም በመርፌ የሚወገ የወሊድ መቆጣጠርያ መድሃኔት በmarketing እና coercion ኃይል እንዲጠቀም በማድረግ ከባህሉ፤ ከጤንነቱ እና ከራሱ (ከህሊናው) ጋር እንዲጣላ አድርጓል። ሌሎቹ ክልሎች ይህንን መርዛማ አካሄድ ላለመከተል ሲታገሉ የአማራ መንግስት እና ልሂቃን አዋቂ እና ተምረናል ባዮች ሙሉ በሙሉ capitulate አደረጉ። እውነትም «የተማረ ገደለን» (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2016/12/blog-post_7.html)።

ዛሬ የኢትዮጵያ መሰረታዊ ችግር የህዝብ ብዛት አይደለም። ከመሰረታዊ ችግሮች መካከል የመሬት ፖሊሲው (መሬት የመንግስት መሆኑ) እንደ ችግር ይበልጠዋል። የህዝብ ብዛት እንዲህ እንዲጨምር ያደረገው ገበሬው መሬቱን ሽጦ ወደ ከተማ መምጣት ስለማይችል የኢትዮጵያ ህዝብ ለ40 ዓመታት artificially ገጠር እንዲቆይ ተደርጓል። ገበሬው በነጻነት መሬት መሸጥ መለወት ቢችል ኖሮ ዛሬ 80-85% የገጠር ነዋሪ ከሚሆን ወደ 60% ደርሰን ይሆን ነበር። የገጠር ህዝብ ስድስት ልጅ ይወልዳል የአዲስ አበባ ህዝብ ሁለት ልጅ ይወልዳል። 40% የከተማ ነዋሪ ሆኖ ከስድስት ፋንታ ሁለት ልጅ በአማካኝ ሲወልድ የህዝብ ቁጥራችን እንዲህ አይጨምርም ነበር። ስለዚህ ልክ እንደ ቻይና በማኦ ዘመን የመሬት ፖሊሲው ነው የዝብ ቁጥራችንን artificially እንዲንር ያደረገው። አሁን ታድያ መሰረታዊ ችግሩን አምኖ ለመቅረፍ ከመሞከር symptomኡን ለማከም እንሞክራለን። ይህ ታላቅ ጥፋት ነው።

በሁለተኛ ደረጃ አንድ ህዝብ የሚወልደውን ልጅ መጠን እራሱ የራሱን ጥቅም አይቶ በholistic እና organic መንገድ ቢቆጣጠር ነው የሚሻለው (በስነ ልቦና እና ማህበራዊ ሰላም ደረጃ)። ከተሜ ሲሆን፤ ቆይቶ ሲያገባ፤ ወዘተ እራሱ አስቦ መወሰን ይጀምራል። በመንግስት እና ኤንጂኦ ኃይል በግፊት እና ጫና በቅኝ ግዛት መልክ ከተመጣበት ችግሩን በደምብ ሳያውቀው ወደ አደገኛ የወሊድ ቁጥጥር ይገባበታል። ከዛ ዛሬ የምናየው backlash ይመጣል። ሴቶች መውለድ አቃተን ይላሉ። ልጆች ጠፉ ይባላል። ወዘተ። የብአድ መፍትሄ ብዙ ጊዜ መፍትሄ አይደለም።

ሶስተኛ፤ መላ ኢትዮጵያም አማራም ለህዝብ ቁጥር እድገት በቂ ቦታ አላት። አልተጨነቀችም። ሌሎች የመንግስት ፖሊሲዎች ናቸው ችግሮቹ። አልፎ ተርፎ አንዱ ላለፉት አመታት የኤኮኖሚ እድገት ያመጣው ግበአት የህዝብ ብዛት ነው። የ100 ሚሊዮን ገበያ እና ሰራተኛ ኃይል ቀላል አይደለም። ጥቅም አለው። ይህ በአማራ ክልል እና ልሂቃን የታሰበበት አይመስለኝም። ውሳኔዎችን በ one track mind ሆነው ነው የወሰኑት።

አራተኛ፤ በዛሬው የጎሳ ችግር ሁኔታ ዴሞግራፊ ወሳኝ ነገር ነው። የአማራ ክልል ህዝብ ቁጥር ቀነሰ ማለት በአንድነት የሚያምነው ህዝብ ቁጥር ቀነሳ ማለት ነው (አማራው ከሞላ ጎደል እንዳለ ከአንድነት ኃይሉ ውስጥ ስለሆነ)። ዛሬ ይህን ሃቅ መካድ አይጠቅምም። ይህ ፖለቲካዊን ይቀይራል። መሃሉን ያደክማል ጎሰኝነትን የሚያራምድ ፖለቲካን ያጠነክራል። ፖለቲካው ይዛባል። የአማራ ክልል መንግስት እና ልሂቃን ይህን እንደ አንድ ግበአት አለማሰባቸው እጅግ ያሳፍራል። ወይ ክፋት ወይንም ጅልነት ነው፤ ይቅርታ አድርጉልኝ። ነባራዊ እውነታን አለመቀበል ነው። ለጎሳ ፖለቲካ ተብሎ የህዝብ ቁጥር እንዲንር ይደረግ ማለቴ እንዳልሆነ መችሄስ ግልጽ ይመስለኛል። ግን ሁሉ ነገር መታየት አለበት እና ሚዛናዊው መንገድ መከተል አለብን ነው የምለው።

መፍትሄው ምንድነው? የወሊድ መቆጣጠርይ ይከልከል ወዘተ አይነት የማይሆን ነገር አደለም የምለው፤ ከአንዱ ጸንፍ ወደ ሌላው! መንግስት ለወሊድ መቆጣጠርያ marketing እና እርዳታ ይተው ነው የምለው። በዚህ ዘርፍ የሚሰሩ ኤንጂኦዎች ይከልከሉ። የታወቁ ጉዳታቸው ያነሰ የወሊድ መቆጣጠርያ መንገዶች ይሸጡ ግን ህዝቡ ላይ አይጫኑ። ህዝቡ አለ ጫና እና ግፊት በorganic እና holistic መንገድ የራሱን ግላዊ ውሳኔ ያድረግ። አለ ጫና እና ግፊት። ይህ መፍትሄ ሁለት ግቦች ይኖሩታል፤ 1) የህዝቡ ስነ ልቦና እና የማህበረሰቡ ስነ ልቦና ይገጋጋል እና ይጠበቃል እና 2)  የህዝብ ቁጥር ጭማሬ ከፍ ይላል፤ ወደ naturally መሆን ያለበት ደረጃዎች ይሄዳል እና ከሌሎች ክልሎች ብዙ አያንስም። በአጭሩ የክልሉ ፖሊሲ ከጫፍ ወደ ሚዛን ይመለሳል ነው (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/04/blog-post_6.html)።

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!