Thursday 10 January 2019

ግብዝነት ያጠፋል

"Correct faith does not benefit anything, when life is corrupted."

St. John Chrysostom

ከቤተ ክርስቲያን ሰው ካፈነገጠ፤ እምነት ካጣ፤ ከብርሃን ወደ ጭለማ ከገባ፤ ለነዚህ ሁሉ ዋና ምክንያት የኛ የቤተ ክርስቲያን ምዕመናን እና አመራር ግብዝነት ነው። ቤተ ክርስቲያን ባለእንጀራህን ክርስቶስ እንደሚወዳችሁ ውደዱ ብላ ታስተምራለች። እኛ ግን በተለያየ ደረጃ ይህን እውነታዊ ትዕዛዝ አንፈጽምም። «ግብዞች» ነን። ይህን ባለማድረጋችን ወንድም እህቶቻችን ቤተ ክርስቲያንን እንዳያምኑ እና ወደ ፈተና እንዲገቡ እናረጋለን። ለዚህም ነው ክርስቶስ ግብዝነትን ለይቶ የወቀሰው። ሁላችንም ኃጢአተኞች ነን። ግን ግብዝነታችን በበዛ ቁጥር እራሳንን (ቤተ ክርስቲያንን) እጅግ እየጎዳን እንሄዳለን ሰውንም እናሳስታለን። (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2017/11/blog-post.html)

ይህንን ትምሕርት ተከትሎ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ሲኖዶስ የራስ ማጽዳት ዘመቻውን አጠንክሮ እና እንደ ዋናው እና መጀመርያ ስራቸው ይያዙት ብዬ በአቅሜ እለምናለሁ። ዛሬ ሚሊዮኖች አማኝ ናቸው። ቤተ ክርስቲያኖች ይገነባሉ። ነገ በግብዝነታችን ምክንያት ሁሉም ሌጠፋ ይችላል። ይህ እንዳይሆን እራሳችንን እናጽዳ።

እስቲ ግብዝነትን በሌላ ምሳሌ እንመልከተው… በሀገራችን መሃበረሰብ ማመንዘርም ማስገደድ/መስረቅም ኃጢአት እና ነውር ነው። ሆኖም የሃገራችን ሴቶች በተለይ ከተማ ዙርያ አንዳንድ ወንዶች ሲያመነዝሩ፤ ከኛ ጋር ካልወታሽ መስርያቤቱ እንዳይቀጥርሽ አደርጋለው ሲሉ፤ ሚስቶቻቸውን ሲደበድቡ ወዘተ ይሰማሉ ወይንም ያያሉ። ይህ ሁሉ በባህላችን በወጋችን ክፉ የሚባሉ ነገሮች ሆነው ግን ይከሰታሉ። ይህን እያየች ያደገች ሴት በቀለም ትምሕርት ገፍታ ሄዳ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ አንዱ የ«ፌሚኒዝም» ፍልስፍናን አቅፋ ጣኦት ታደርጋለች። ለምን በዚህ ታምኛለሽ ካልናት ባህላችን በጅምላ ጭፍጭፍ ታደርጋለች። ለምን? ግብዝ የሆነ የራሱን እሴቶች የማያከብር ህብረተሰብ መካከል ስላደገች። ልክ ያንን «ተቃራኒ» ስታገኝ ሮጣ አቀፈችው።

አያችሁ የግብዝነት ጉዳት። እንታገለው። ወደ ማንነታችን ወደ እውነት የሆኑት እሴታችን እንመለስ። አለበለዛ ሀገራችንንም ማንነታችንንም እናጣለን።

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!