Wednesday 17 October 2018

ኢትዮጵያን የሚገላት የአንድነት ኃይሉ ነው (ክፍል 2)

ወኪሎች ማፍራት ያልቻለ ህዝብ ይጠፋል።

አዲስ አበባ የአምስት ሚሊዮን በ«ኢትዮጵያዊነት» የሚያምን ህዝብ ከተማ ነው። ቅንጅት በ100% መርጧል። ግን ይህ ህዝብ አንድም የፖለቲካ እና ማህበራው መብቱን የሚከራከርለት፤ የሚሟገትለት፤ የሚወክለው ድርጅትን ማቋቋም አልቻለም። አንድም!

ታድያ መብቶች ሲገፈፉ፤ ፍትህ ሳይኖር፤ ሰላም ሲጠፋ ምንድነው ምክንያቱ? ትብብር እና ድርጅት የሌለው ህዝብ እንዴት ፍትህ እና ሰላም ይኖረዋል? ማን መብቱን ያስከብርለታል እራሱ ካላስከበረ?!

ወኪሎች ማፍራት ያልቻለ ህዝብ ይጠፋል።

አንድ ምሁራን እንዲህ ብልዋል፤  “When people realize things are going wrong, there are two questions they can ask. One is, ‘What did we do wrong?’ and the other is, ‘Who did this to us?’ The latter leads to conspiracy theories and paranoia. The first question leads to another line of thinking: ‘How do we put it right?’”

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!