Wednesday 17 October 2018

ኢትዮጵያን የሚገላት የአንድነት ኃይሉ ነው (ክፍል 1)

ባለፈው ኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት የኤርትራ ዲያስፖራ እንደልማዳቸው እየተሯሯጡ ለሀገራቸው ገንዘብ እያዋጡ ነበር። ምን ያህል አዋጡ? ልምሳሌ ያህል፤ በአንድ ቀን ከአንድ ከተማ ሲአትል (ዋሺንግተን ስቴት) አንድ ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር አዋጥተዋል! ከዋሺንግተን ዲሲ አይነቱ ብዙ ኤርትራዊ ያለበት ከተማ ምን ያህል እንደተዋጣ ባላውቅም መገመት ይቻላል።

ተወዳጁ «ኢትዮጵያዊነትን» የወከለው ቅንጅት ለሰላም እና ዴሞክራሲ ፓርቲ መሪዎቹ ከተፈቱ በኋላ ሰሜን አሜሪካ መጥተው ለወራት ቆዩ። ከመላው ሰሜን አሜሪካ የሚኖር ኢትዮጵያዊያን ከአንድ ሚሊዮን ዶላር በታች ሰብስበው (እና እርስ በርስ ተጣልተው) ተመለሱ!

የአንድነት ኃይሉ እርስ በርስ አለመስማማት እና አለመደራጀት ኢትዮጵያን ይገላል።

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!