Wednesday 17 October 2018

ኢትዮጵያን የሚገላት የአንድነት ኃይሉ ነው (ክፍል 3)

በደርግ ዘመን ብዙ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ስራ ከሀገር ውጭ (በዲያስፖራ) ነበር የሚደረገው ሀገር ውስጥ በነፃነት መስራት ስለማይቻል።

በዚህ ጊዜ ሻዕብያ እና ህወሓት ከዲያስፖራ በርካታ ገንዘብ እና ሌላ ድጋር እየሰበሰቡ ግዙፍ ተቋማት ሆነው ኢትዮጵያን አንቀጠቀጡ።

የ«ኢትዮጵያዊነት» ኃይል ግን «ዴሞክራት» (ኢዲዩ) እና «ማርክሲስት» (ኢህአፓ፤ መኢሶን፤ ደርግ ወዘተ) ሆኖ ተከፋፍሎ ቆየ። ኤዲዩ እርስ በርስ ተከፋፍሎ እና ተጣልቶ በፍጥነት እራሱን ከፖለቲካ ዓለም አባረረ! ማርክሲስቶቹ እርስ በርስ ተፋጁ፤ ሀገሪቷን አሰቃዩ እና ፈትፍተው ለጎሳ ብሄርተኞቹ አጎረሱ።

እኛ ኢትዮጵያዊ ብሄርተኞች አንድ አላማ ኖሮን መተማመን፤ መስማማት፤ አብሮ መስራት፤ መተባበር እና መደራጀት አለመቻል በሽታችን አሁንም አንቆ ይዞናል።

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!