Tuesday 23 October 2018

ብስለት የሞላው ውይይት

ይህንን ውይይት ጠንቅቃችሁ አዳምጡት ብዬ እለምናለሁ።

https://www.youtube.com/watch?v=PY9RFsmu_ks

የተነሱት ዋና ዋና ነጥቦች፤

1.ዛሬ ያለንበት ፓለቲካዊ እና ማህበረሰባዊ ሁኔታ እና ችግሮች 27 ወይን 44 ወይን 50 ዓመት የፈጠረው አይደለም። ከዛ በፊት ያለን የረዥም ዓመታት ታሪክም አስተዋጾ ያለው ነው። ይህን አውቀን ነው ወደ እውነት እና ትክክለኛ መፍትሄ ምድረስ የሚቻለው።

2. ራስን መመርመር ግድ ነው። ችግሮቻችን በመንግስት እና በፖለቲከኞች ምክንያት ነው የመጣው ማለት ልክ አይደለም። እውነት አይደለም። ሁሉም ዜጋ በራሱ በኩል ሚና ተጫውቷል እና ላለፈውም ለወደፊቱም ሃላፊነት መውሰድ አለበት።

3. ፖለቲካ አንድ የማህበረሰባዊ ኑሮ ክፍል ነው። በመሆኑ ሁሉ ዜጋ በአቅሙ እና በአግባቡ መሳተፍ አለበት። እናት እንደ እናት፤ አባት እንደ አባት፤ ልጅ እንደ ልጅ፤ ሃይማኖት መሪ እንደ ሃይማኖት መሪ፤ ምሁር እንደ ምሁር፤ ሰራተኛ እንደ ሰራተኛ ወዘተ።

4. የግብረ ገብ እጦት ታላቅ ችግር ነው እና ሊሰራበት ይገባል። እንደማንኛውም ችግር ይህ ችግር የሚፈታው መጀመርያ አመጣጡ፤ ምክንያቱ እና ምንጩ ሲታወቁ እና ሲታመኑ ነው።

5. ለውጥ ማለትም ወደ የተሻለ ፖለቲካ እና ማህበራዊ ሁኔታ መቀየር ጊዜ ይፈጃል። ትዕግስት ይጠይቃል። ምርጫ እና ተመሳሳይ ስርዓቶች አለ ቅድመ ዝግጅት እና የአስተሳሰብ ለውጥ ጎጂ ነው የሚሆኑት።

6. ዛሬ ከሞላ ጎደል የፖለቲካ «ነፃነት» አለ። ቋሱ በኛ በህዝቦቹ ሜዳ ነው ያለው። ችግር ካለ መፍታት የኛ ሃላፊነት ነው። ሃላፊነታችንን እንደ ዜጎች መቀበል ግድ ነው። በሌላ ለምሳሌ በመንግስት ባሳበብ አብቅቷል።

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!