Friday 19 October 2018

የወሬ ፖለቲካ

እኛ ኢትዮጵያ ብሄርተኞች ለ27 ዓመት ወያኔን ከመውቀስ ሌላ ስራ ባለመስራታችን የወያኔን ለሩብ ክፍለ ዘመን እንዲገዛ አደረግን። በቂ ጸረ-ወያኔ ፕሮፓጋንዳ ካሰራጨን ህዝቡ በአመጽ ይነሳል ብለን ገምተን ይሆናል ግን አልሆነም። በመጨረሻ አመጹን ያስነሳው ህዝቡ በእውን የትግሬ አድሎ በዝቶበት ነው። የትግሬ አድሎ አለ ብሎ በነ ኢሳት ስለተነገረ ሳይሆን ህዝቡ በለት ኑሮው ስላየው ነው (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2016/10/ethnic-federalism-kills-meles.html)።

ስለዚህ የወሬ ፖለቲካ እንደማይሰራ የ27 ዓመት ማስረጃ አለን። እኛ ኢትዮጵያ ብሄርተኞች 100% ጊዜአችንን ስለ ወያኔ በማልቀስ ከማዋል ፋንታ 50%ኡን ህዝብ እና ልሂቃንን በማደራጀት ብናውለው የት ደርሰን ነበር።

አሁንም አንዳንድ ጓዶቻችን የወሬ ዘመቻ በጎሳ ብሄርተኞች እና አሁን በ ጠ/ሚ አቢይ ማካሄድ ጠቃሚ ይመስላቸዋል። የድሮውን ስህተት መድገም። ለ27 ዓመት ያልሰርዋን መቀጠል። ምን ማለት ነው የማይሰራን ነገር መደጋገም?

ምን አልባት ውስጣችን ማደራጀት እና ሌሎች የእውነት የፖለቲካ ስራዎች ከባድ እንደሆኑ ስለምናውቅ ወሬ ላይ በማተኮር ማምለጥ እንፈልግ ይሆን። ወይንም ሻዕብያ እና ህወሓት ግዙፍ በህዝባቸው ጽናት ግዙፍ ድርጅቶች ሆነው ሲገኙ እኛ ኢትዮጵያ ብሄርተኞች የነሱን 1% የሚያክል ድርጅት መመስራት ስላቃተን አፍረን ይህንን ላለማየት ይሆን ወደ ወሬ ፖለቲካ የምንሸሸው። የዝቅተኛ ስሜት አድሮብን ይሆን 6% ድጋፍ ያለው ወያኔ ለ27 ዓመት ሲገዛን አንድ ጠንካራ ድርጅት መፍጠር ባለመቻላችን?

ምክንያቱ ምንም ቢሆን የወረ ፖለቲካ አይሰራም እና ካሁኑኑ አቅማችንን ከዛ ወደ ከባድ ስራው ወደ መደራጀት ማሸጋሸግ አለብን። ይህ ማለት ካሁን ወድያ ወሬ ሳይሆን ስራ መስራት። መሳደብ ሳይሆን ብልጥ ሆኖ ትብብሮችን መፍጠር ለጊዜውም ቢሆን እስከንደራጅ። ድልዲዮችን ከማቃጠል መጠቀም። እንደ ጠ/ሚ አቢይ አይነቱን ከማራቅ ማቀፍ እና መጠቀም። ይህ ነው ፖለቲካ። እንጂ ዝም ብሎ ማውራት መገዛት ማለት ነው።

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!