Tuesday 16 October 2018

የለቅሶ ፖለቲካ አሳፋሪ ነው፤ ያብቃ!

ኢሳት ለበርካታ ስዓት ስለ የታፈሱ የአዲስ አበባ «ወጣቶች» ዜና እና አስተያየት እያቀረበ ነው (https://www.youtube.com/watch?v=4KugoBLSfFY)።

እኔ እስካየሁት ድረስ ኢሳት አንዲት ደቂቃ ስለ መሰረታዊ ችግሩ ውይይት አላቀረበም። መሰረታዊ ችግሩ የአዲስ አበባ ህዝብ እና በመላው ኢትዮጵያ በኢትዮጵያዊነት የምናምነው የኢትዮጵያ ብሄርተኞች በበቂ ደረጃ አለመደራጀታችን ነው።

አስቡት… የአምስት ሚሊዮን ህዝብ ከተማ አንዳች ይሄ ነው የሚባል ህዝብ ወኪል ተቋም የለውም! ይህ ነው ጉዱ።

ይህን ጉድ አምነን ወደ መፍትሄ ከመሄድ ወደ መደራጀት ከመሄድ ጊዜአችንን «በለቅሶ ፖለቲካ» እናጠፋለን። እንደ ክብር የሌለን ሰዎች የራሳችን ገበና ሳናስተካክል ሌሎችን «አትግዱን» ብለን 24 ሰዓት እንለምናለን። በራሳችን ድክመት ስለምናፍር ይመስለኛል ሁል ጊዜ ጣታችንን ወደ ሌሎች የምንጠቁመው። እነሱ ደግሞ እኛ እራሳችንን ካላልጎለበትን ምንም አያደርጉልንም።

አንድ ምሁራን እንዲህ ብልዋል፤  “When people realize things are going wrong, there are two questions they can ask. One is, ‘What did we do wrong?’ and the other is, ‘Who did this to us?’ The latter leads to conspiracy theories and paranoia. The first question leads to another line of thinking: ‘How do we put it right?’”

የኛ የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ምሁራን እና ልሂቃን አሁንም «ማን ነው የሚያጠቃን» የሚለው ላይ ነን። በጃንሆይ ዘመን በ«አለመተባበር ብሽታችን» ምክንያት በየቀኑ ለዳኝነት ወደ ጃንሆይ እንሄድ ነበር። ከዛ አድሃሪ/ተራማጅ እየተባባልን ተገዳደልን። የተረፉት «አድሃሪዎቹም» ኢዲዩ መስርተው አብሮ መስራት አቅቷቸው ፈራረሱ። ማርክሲስቶቹ ከመተባበር እርስ በርስ ተፋጁ። ኢህአዴግ ስልጣን ሲይዝ እራሳችንን «ተቃዋሚ» ብለን ሰይመን ይሄ ነው የሚባል ተቋም ማደራጀት አቃተን። ወዘተ። የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ደጋግሞ መውደቅ ረዥም ታሪክ ነው። ግን አሁንም ይህን ድምከት ላይ ከማተኮር ይልቅ ሌሎችን እባካችሁን አድኑን ብለን እንለምናለን!

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!