Thursday 1 February 2018

ትህትና

አባ ቲኾን በጻፉት መጸሃፍ "Everyday Saints" አባ ቲኾን አንድ ታላቅና ጀግና መኖክሲት፤ በሶቪዬት መንግስት ደጋግመው የታሰሩ የሆኑ፤ ስለ ገዳም ኑሮ ሲጠይቋቸው እኚህ መኖክሲት እንደዚህ አልዋቸው፤ «ዋናውና መጀመርያው ነገር ይህ ነው፤ ማንንም ላይ አትፍረድ»

አለመፍረድ ማለት አለመኮነን ነው። ይህ መፍረድ ድርጊትን ወይም አቋምን ጥሩ ነው ወይ መትፎ ነው ማለት አይደለም። እንደዚህ አይነት ፍርድ ተገቢም አስፈላጊም ነው። አትፍረዱ ማለት አትኮንኑ፤ ሰውን ከድርጊቱ ጋር አታቆራኙ። ሰውየው እራሱ መጥፎ ነው፤ ሃጥያተኛ ነው፤ እኔ ከሱ እሻላለሁ፤ እሱ ወደ ገሃንም ይገባል አይነቱ ነው አትበሉ አታስቡ የምንባለው። ስለዚህ ለክርስቲያን በድርጊት መፍረድ ተገቢ ነው ግን በሰው ማንነት መፍረድ ትክክል አይደለም።

በሰው መፍረድ ኢክርስቲያናዊ የሆነው አንዱ ምክነያት መፍረድ ወደ ተዕቢት ስለሚመራ ነው። ተዕቢት ደግሞ የመጀመርያውና ዋናው እግዚአብሔርን ያጣንበት ምክንያት ነው። አዳምና ሄዋን በትዕቢታቸው ምክንያት መልአክት ለመሆን አስበው ነው እጸ በለሱን የበሉትና። ስለዝህ እንደ ክርስቲያን ከትእቢት ርቀን ወደ ተቃራኒው ትህትና ነው መጠጋት ያለብን።

አዎን ትህትና አንድ ክርስቲያን ከሚፈልገው ዋና ጥሩ ባህርይ ነው። «ትህትናና ፍርሃ እግዚአብሔር ከሁሉ መልክአ ምግባር በላይ ናቸው» ትብሏል። ትህትና የሰው ልጅን ዋና ተልኮ፤ ማለት ወደ እግዚአብሔር መቅረብ፤ ለማሟላት ግድ ነው። እራሱን እንዲገመግም፤ ከፈተናና ሴጣን እንዲርቅ፤ ሌሎችን ላይ ከመጠቆም እራሱን ላይ መጠቆም። እነዚህ በሙሉ ትህትና ይጠይቃሉ።

እንደዚህ ሆኖ ማንም ሰው፤ በተለይ መሪ፤ ትህትናን ሲያንጸባርቅ ደስ ይለኛል። እራሱን ወይም ወገኑን የማያሞገስ፤ እራሱን አጥፊና ሃላፊ የሚያደርግ፤ እራሱን ጥልቆ የሚገመግም፤ ሌሎችን በፍርድ ሳይሆን በመቆርቆር አይን የሚያይ ሰው ደስ ይለኛል። ይህ ባህሪዎች ለራሱም ለዙርያው ላሉትም እጅግ ይበጃል።

እኔ አቶ ለማ መገርሳን አላውቋቸውም ግን ያዳማጥኳቸው ንግግሮቻቸው በትህትና የተሞሉ በመሆናቸው ተደስጭያለው። በዚህ ረድፍ ለሁላችንም ታላቅ ምሳሌ መሆናቸው ነው ከሁሉም በላይ ያስደሰተኝ።

ከአቶ ለማ ሌሎችን በሰሞኑ አይቻለሁ። ብአዴን በደብረ ብርሃን የጠራው የምሁራን ስብሰባ ላይ አንድ ወጣት ምህሩን በጥህትና እጅግ እጅግ አስደሰተኝ። እኛ ምሁራን ባንኖር ገበሬው (ብዙሃኑ) በሰላም አብሮ ይኖር ነበርና እኛ ነን ችግሩ። ለችግሩ መፍትሄ እናገኝለታለን ከማለት መጀመርያ እራሳችንን እንፈትሽ ብሎ ታላቅና አስደናቂ ንግግር አቀረበ። እንደዚህ አይነቱ የምላስ ሳይሆን የመንፈስ ጀግና ነው ሁላችንም የሚያስፈልገን።

ሁላችንም በሌላ ላይ ከመጠቆም፤ ችግርሮቻችንን ብሌላ ከማሳበበ፤ መፍትሄም ከሌሎች ነው የሚመጣው ብለን ከምናሰብ፤ እራሳችንን ወድቅ (disempower) ከማድረግ፤ ውስጣችንን መርምረን ሌሎች ላይ ሳንፈርድ ብንራመድ ለሁላችንም መልካም እንሆን ነበር።

እግዚአብሔር ትህትና ይስጠን። ከትዕቢት ፈተና ያርቀን። የእርስበርስ ሰላም እንድሽ ይርዳን።

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!