አሳፋሪና አገር አፍራሽ ታሪካችንን እንዳንደግም ነው ይህን ጽሁፍ የምጽፈው። ታሪክ እንደመዘገበው ከኢህአዴግ ውጭ ያለነው ምሁራን፤ ፖለቲከኞችና ብዙሃን በፖለቲካ ረገድ ቁም ነገር ለማድረግ እድል ባጋጠመን ቁጥር እልዳችንን አበላሽተናል። በተደጋጋሚ ጊዜ ለአገራችን የፖለቲካ መስተካከል ከኢህአዴግም ይበልጥ እንቅፋት ሆነን ተገኝተናል። ይህን ደፍሬ መናገር የምችል ይመስለኛል።
አንዱ የድክመታችን ምክንያት ተልዕኮአችንን አለማወቃችን ወይም መርሳታችን ነው። ተልዕኮአችን የአገር ፖለቲካ ግንባታ ነው እንጂ የፖለቲካ ውድድር አይደለም። የአገር ፖለቲካ ስርዓት ግንባታ ሲባል ሁላችንም ስለ ህገ መንግስትን ማርቀቅ ነው የምናስበው። ግን ከዚህ ህገ መንግስት ማርቀቅ ስራ በፊት የልብ ለልብ መተዋወቅ፤ በተወሰነ ደረጃ መተማመን፤ መግባባትና መስማማት ያስፈልጋል። እነዚህ ለአገር ግንባታ የፖለቲካ ድርድር ቀድሞ ሁኔታዎች ናቸውና። አለነዚህ ማንኛውም በወረቀት ያለ ህግ፤ ምንም አይነት ወርቅ የሆነ ህግ ቢሆነም፤ በስራ ሊተገበር አይችልም።
ቀጥሎ በነዚህ ተመስርቶ ህገ መንግስትና ሌሎች የርዓይና የህግ ሰነዶች ይደነገጋሉ። ቅራኔ ወይም አለመግባባት ካለ በህግ መሰረት ይፈታል ህጉ ደግሞ በቂ ካልሆነ ያለው መተማንና ስምምነት ለፍትህ ይረዳል። የአገር የፖለቲካ ግንባታ ሂደት እንደዚህ ነው መሆን ያለበት።
የፖለቲካ ውድድር ደግሞ የሚጀምረው የፖለቲካ ስረዓቱ ከተዋቀረ በኋላ የሚመጣው የፖለቲከኞችና ሌሎች ለመሪነት እርስ በርስ በህጉ መሰረት መወዳደር ነው። በምእራብ «ዴሞክራሲዎች» እንደዚህ አይነቱ ውድድር በርካታ ክርክር፤ ክስ፤ ዘለፋም ወዘተ ያካትታል። የህጉን ገደብ ዳር ዳር እየነኩ ግን ሳያልፉ እነዚህን አይንቶች ባህሪዎችን ያንጸባርቃሉ። ይህ ስልጣን ለመያዝ ሊበጃቸው ይችላል ግን ምንም አይገነባም። እርግጥ መተማመንንና ውይይትን ይጎዳል ግን ከምርጫው በኋላ የደረሰውን ጉዳት ይጠግኑና የአገር ማስተዳደር ስረአቸውን ይጀምራሉ። ይህ ነው በተለምደው የምናውቀው የፖለቲካ ውድድር።
የፖለቲካ ውድድር ደግሞ የፖለቲካ ስርዓቱ ከተዋቀረ በኋላ የሚከተለው የፖለቲከኞችና ሌሎች ለመሪነት እርስ በርስ በህጉ መሰረት መወዳደር ነው። በምእራብ «ዴሞክራሲዎች» እንደዚህ አይነቱ ውድድር በርካታ ክርክር፤ ክስ፤ ዘለፋ ወዘተ ያካትታል። የህጉን ገደብ ዳር ዳር እየነኩ ግን ሳያልፉ እነዚህን አይንቶች ባህሪዎችን እያንጸባርቁ ይወዳደራሉ። ይህ ስልጣን ለመያዝ ሊበጃቸው ይችል ይሆናል ግን አገርን አይገነባም ይጎዳልም። ሰልዚህም ነው ውድድሩ ምርጫው ካለፈ አሸናፊዎቹ ውድድሩ ያደረሰውን ንዴት፤ ቂምና ጉዳት ይጠግን ዘንድ ትሸናፊዎቹንም መላው የአገሪቷን ህዝብ አንድ የሚያረግ እርቃዊ ንግግርና ተግባር የሚአደርጉት። ይህ ነው በተለምዶ የምናውቀው የፖለቲካ ውድድር።
ስለዚህ አገርን መገንባትና የፖለቲካ ውድድር የተለያዩ ባህሪያት፤ ተግባራትና ልምድ ያስፈልጋቸዋል። የአገር ግንባታ ሂደት እንደ መተማመን፤ ስምምነት፤ አንድነት፤ መግባባት፤ ህብረት፤ ቅራኔን መፍታት፤ ውይይት ወዘተ አይነቱ ባህሪያትና ልምዶች ያስፈልጉታል። የፖለቲካ ውድድር ግን ክርክር፤ ውድድር፤ ፉክክር፤ መካሰስ፤ ህግና ስረዓትን ዳር ዳሩን መጣስ፤ ወዘተ አይነቱን ልምዶች ያካትታል። በአገር ግንባታ ሂደት መካከል እነዚህን የፖለቲካ ውድድር ባህሪያትና ልምዶች ይዘን ከገባን አገርን መገንባት ሳይሆን ማፍረ ነው የምናደርገው።
ለዚህ ደግሞ በርካታ ታሪካዊ ምሳሌዎች አሉን። እስቲ ወደ 15 ዓመታት ወደ ኋላ ተመልሰን የ«ተቃዋሚ» ምሁራን፤ ጋዜጠኛና ፖለቲከኞች እያደረጉ፤ እየተናገሩ፤ እየጻፉ ምን እንደነበር እናስታውስ። ስራቸውን ባጭሩ ለመግለጽ «እርስ በርስ መበላላት» ማለት ይቻላል! ተቃዋሚዎች ኢህአዴግ ከሚተቹት ይበልጥ እርስ በርስ ነበር የሚፋጁት። ጋዜጣ ላይ ቁም ነገር ሳይሆን ስድብና የመንደር ወሬ ነበር የሰፈነው። ከሞላ ጎደል ስራቸው 90% አፍራሽ 10% ገምቢ ነበር። ስለዚህም ነው ተቃዋሚው ጎራ ምርጫ '97 በግንቦት ሆኖ እሰከ የካቲት አካባቢ የትብብር መዋቅሮች ያላደራጀው! ለዚህም ነው ከምርጫው በኋላ ተቃዋሚዎች በቀላሉ የተበታተኑት። በበፊቱ ዓመታት እዱሉ እያለን ቅስ ብለን በትብብር ጉዳይ ተወያይቶ ትብብርን ከመፈጸምና ጠንካራ መሰረት የሆነ መዋቅርን ከመገንበት እንደ ምርጫ ተዋዳዳሪዎች እየተሰዳደብን ዋልን። ችግር ሲመጣ ለመቋቋም አቅሙ አልነበረንም። እርስ በርስ ተፋጅተን አለቅን። የግንባታ ስራ ያልተሰራባቸው ቅንጅትና ህብረት በቀላሉ ፈረሱ። የፖለቲካ መዋቅር ግንባታንና የፖለቲካ ውድድርን መለየት ያልቻሉትም ከፖለቲካ ወጡ። የህዝብም ትዝብት አደረባቸው።
በርካታዎቻችን በምዕራብ የሚዲያ ዜና፤ ትምህርትና ፕሮፓጋንዳ ስላደግን የነዚህ አገራት ፖለቲካ ስናይ ፖለቲካ እንደዛ መሆን እንዳለበት ይመስለናል። የናየው ደግሞ የፖለቲካ ውድድራቸውን ነው። ክርክሩን፤ ዘለፋውን፤ ስድቡን፤ ሴራውን ወዘተ። እኛም እንደነሱ ማድረግ እንወዳለን መሰለኝ። ግን ኢትዮጵያ ያለችበት ቦት፤ ለረዥም ዓመታት ያለችበት ቦታ፤ ገና የአገር ፖለቲካ ግንባታ ላይ ናት። ብዙሃኑም ልሂቃኑም የፖለቲካ መደቦቻችን እስካሁን በእምነት የተመሰረተ አገራቷን ምን መምሰል አለበት የሚል ሰፊ ስምምነት ላይ አልደረስንም። አሁንም ያለው ዋና ስራችን የህ ነው። አዎን ህገ መንግስት አለን ግን ሰፊው ርአይና ስምምነት የለንም። ነገ ኢህአዴግ ከስልጣን ቢወርድም ይህ ስምምነቱ ስለሌለ ሁከትና አብዮት ይከተላል።
በዚህ ምክንያት ሁላችንም፤ ምሁራን፤ ብዙሃን፤ ፖለቲከኛ፤ የመንግስት ሰራተኛ፤ ወዘተ ትኩረታችን ወደ አገር ግንባታ መቀየር አለበት። ይህ ማለት ከታች የተጠቀሱትን ለአገር ግንባታ አስፈላጊ የሆኑትን ብሃሪያት፤ ተግባሮችና ልምዶች ከራሳችን ጋር መዋሃድና በዚህ አስተሳሰብ ወደ ፊት መራመድ።
ስምምነት፤ አንድነት፤ መግባባት፤ ህብረት፤ መተማመን፤ በስነ ስረዓት መነጋገር፤ ውይይት፤ ቅራኔን መፍታት።
የሚቀጥለው ጊዜ አንድ ሰውን ወይም ቡድንን መዝለፍ ወይም መስደብ ካሰኘን ቆመን እናስብ። የፖለቲካ ውድድር ውስጥ አይደለንም። እንደዚህ አይነቱ ባህሪያት ታሪካችን እንደሚያረጋግጠው ሁላችንንም ጠርጎ ገደል ውስጥ ያስገባል አገራችንን ያፈርሳል። በሰላም እየተከባበርን እየተማመንን ነው መወያየት ያለብን። ይህ የሁላችንንም ጥቅም ያስከብራልና። ይህንን ብቻ ተግባራዊ ካደረግን አለ ምንም ጥርጣሬ ታላቅ አገር እንገነባለን ጠላት የምንላቸውም ምንም ሊጎዱንም አይችሉም።
የሰላም ክፍሌ ይትባረክ ብሎግ፤ ስለ ሀገራችን ኢትዮጵያ ያለኝን ትናንሽ ሀሳቦች በትህትና አቀርባለሁ። ለስሕተቶቼም በቅድሚያ ይቅርታ እጠይቃለሁ
Tuesday, 20 February 2018
Monday, 19 February 2018
የህወሓት ትግል
ለህወሓት እራሱን መቀየር እጅግ ከባድ ስራ ነው የሚሆንበት። እንደምናውቀው ህወሓት የተመሰረተው የጽንፈኝነት በሽታ የኢትዮጵያ ምሁራንንና ፖለቲከኞችን በከባድ በሚያጠቃበት ዘመን ነበረ። ከጽንፈኝነት አልፎ ተርፎ ባህልን እና ተውፊትን የሚንቅ የምሁራን ትውልድ ነበር። ይህ ትውልድ ነው እነ ህወሓት፤ ሻዕቢያ፤ ኢህአፓ፤ መኢሶን፤ ደርግ ወዘተ የፈጠረው። በዚህ ዘመን የተፈጠረ እና ኮሙኒዝም/አብዮታዊ ዴሞክራሲ/ጎሰኝነት አይነቶችን ርዕዮተ ዓለም እንደ ጣዖት የሚያመልክ ድርጅት መሰረታዊ ተሃድሶ ለማድረግ ከባድ ነው። ይህን በማውቅ እስካሁን ላደረጉት ትንሽም ቢሆኑ የአስተሳሰብ ለውጦች ህወሓት ሊደነቅ ይገበዋል።
ሌሎቻችን ይህ አመሰራረት ለህወሓት ምን ያህል ማነቆ እንደሆነ በቂ የሚገባን አይመስለኝም። በተማሪ ንቅናቄ ዘመን በነ ዋለልኝ መኮነን አይነቱ ተማሪና ምሁራን አመለካከት የኢትዮጵያ መሪዎች ብቻ ሳይሆኑ ኢትዮጵያ ሀገሪቷ እራሷ ጥላቻና ስር ነቅል ለውጥ ይገባት ነበር። የኢትዮጵያ ታሪክና ትውፊት በሙሉ ክፉና የተጣመመ ነውና መደምሰስ አለበት ተብሎ ነበር የሚታሰበው። ሃይማኖትም አብሮ እንደ ጠላት ይታይ ነበር። ኢትዮጵያ እንዳለ ተጥሎ ሙዚቃ፤ ጭፈራና ሙዚየሞች ብቻ ቀርተው ሌላው ባህልና ትውፊት በሁሉም ዘርፍ መጣል አለበት ነበር የነበረው አስተሳሰቡ።
ሻዕቢያና ህወሓት መካከል ደግሞ ከዚህ ሁሉ «የማንነት ጥላቻ» አልፎ የ«አማራ» ትላቻን አቀፉ። ለምን ቢባል ርዕዮተ ዓለማቸው ሁልጊዜ በጠላትነት የሚሰየም ቡድን ስለሚያስፈልገው የአማራ የግዥ መደብ ጨቋኝ ነው ተብሎ የዚህ የ«ጠላትን» ሚና ለመጫወት ምቹ ስለነበር።
እዚህ ጋር ቆም ብለን አንድ ጥያቄ መመለስ አለብን። በዛን ዘመን ከኢትዮጲያ ምሁራንና ፖለቲከኞች መካከል እንደዚህ አይነት አስተሳሰብ የሰፈነው በዓለም ዙርያ የነበረው የግራ ጸንፍ አመለካከት ብቻ ተመስርቶ ነው? በፍፁም። ሃገር ውስጥ ያለው ሁኔታ ነው ታላቁን ሚና የተጫወተው። በዛን ወቅት የነበረው የፖለቲካ አመራር ብዙሃኑ የሚያስፈልገውን የፍትሕና የሰላም መግባሮች ስላላሟላ ነው። መልካም አስተዳደር ባለመኖሩ ብሶት ተከማችቶ ነው ምሁራኑም ፖለቲከኞችም ወደዛ ወደ ሀገር አጥፊ ርዕዮተ ዓለም የገቡት።
ይህ ዋና ነጥብ ነው። ጣቶቻችንን እነህወሓት ላይ ብቻ እንዳንጠቁም ያስታውሰናል። እራሳችንን በሃሰት ከችግሩ መንጭ ነጻ አድርገን እንዳናይ ይረዳናል። ለሀገራችን ህልውና እና ትክክሉን መፍትሄ ለማግኘት «የተማሪው ንቅናቄ እና ተከታዮቹ የተፈጠሩት በራሳችን ጥፋት ነው» ብለን ማመን አለብን። እነዚህ ነገሮች ከመሬት አልተነሱም። ሁላችንም ጥፋታችንን መቀበል አለብን። ፈራጅ መሆን የለብንም። እርግት መፀፀት ነው ያለብን። በዚህ አህነት አስተሳሰብ ብቻ ነው እውነተኛው ፍትሕ እና ሰላም የሚገኘው። ሌሎችን ዝምብሎ በመኮነን ሳይሆን ሌሎችን በመረዳት እና እንደወንድማማቾች አንዱ የሌላውን ችግርና አመጣጥ በማወቅ ነው መፍትሄ ማምጣት የሚቻለው።
በዚህ ረገድ የህወሓትን እና የሻዕቢያን ታሪክን ስንመለከት እነዚህ ድርጅቶች ከተመሰረቱ ጀምሮ በተለይ የደርግ የኢትዮጵያ መንግስት ጽንፈኝነታቸውን እና በኢትዮጵያ ያላቸውን ጥላቻ እንዲጨምርና እንዲንር ነው ያደረገው። የደርግ መንግስት የነህወሓትን ጥላቻና ብሶት ደመደመላቸው። በታሪክ በጎሳና በኢትዮጵያዊነት ያላቸውን ርዕዮተ ዓለማቸውን አረጋገጠላቸው። ከዛም ይባስ ሀገሪቷን አሳልፎ ሰጣቸው!
በ1950 አብዛኛው ኤርትራዊ ኢትዮጵያን ይወዱ ነበር ኢትዮጵያዊ ነን ይሉ ነበር። 40 ዓመት በኋላ ኢትዮጵያን ይጠሉ ነበር ኢትዮጵያዊም አይደለንም አሉ። እጅግ ያሳዝናል። የሀገራችን የፖለቲካ ችግር መጠኑን ምን ያህል እንደነበረ አሁንም እንደሆነ በደምብ ያሳየናል።
ህወሓት ስልጣን ከያዘ ጀምሮ የሚያምንበት እና እንደ የስልጣን ስልት የሚጠቀምበትን ጎሰኝነትን አራግቧል። በህግ ደረጃ ብቻ ሳይሆን በማሕበረሰቡ ፕሮፓጋንዳ በመንዛት። ህወሓት ለነባር ኢትዮጵያ ያለውን ጥላቻ በተግባር አሳይቷል። ለምሳሌ «ኦርቶዶክስ ሃይማኖት ይድከም»፤ «ኢትዮጵያዊነት ይድከም» የህወሓት እና ደጋፊዎቹ መፈከር ነበሩ። ትንሽ ቢያሰቡበት ኖሮ ግን ይህ አቋማቸው ለሚወክሉት የትግራይ ህዝብ እጅግ ጎጂ እንደሆነ ይገነዘቡት ነበር! አብዛኛው ትግሬ ኦርቶዶክስ ነው። ትክክል ቢሆንም ባይሆንም የጽንፈኛ ሙስሊም አካሄድ ያሳስባቸዋል። ኢትዮጵያ ውስጥ ደግሞ ጎሰኝነት ከሰፈነ በኢትዮጵያ ተጠቃሚ የሆኑት ትንናሽ ብሄሮች እንደ ትግሬና ጉራጌ ነው በመጀመርያ የሚጎዱት። እንደ ኦሮሚያ አይነቱ ትልቅ ብሄር ጎሰኝነትን ቢያራምድም የሚከተሉትን ጉዳቶችን በመጠኑም ቢሆን በግዙፍነቱ ምክንያት ሊቋቋማቸው ይችል ይሆናል። ትግራይ ግን የጎሰኝነትን እልቂት ልትቋቋም አትችልም። በነዚህ ምንክንያቶች የትግራይ ጥቅም የነበረው አሁንም የሆነው በጎሳ ያልተከፋፈለች አንድ ፈደራላዊ ኢትዮጵያ ነው። ግን ህወሓት ይህን እውነታ ትቶ የሚወክለውን ህዝብ የሚጎዳው አቋምን አራመደ።
ይህ የህወሓት ቅዠት (ወይም schizophrenia)በኃይለ ሥላሴ ዘመን የነበረው የኢትዮጵያ ፖለቲካ አለመስተካከል ምን ያህል ጉዳት እንዳመጣ ያሳየናል። የተለያዩ ጎራዎች ለመብትና ለጥቅማቸው ከመታገል ፋንታ በሚጎዳቸው እና ጥማቸውን በሚሽር መንገድ እንዲ ሄዱ አረገ! ህወሓት ለዚህ ሁሉ ዓመት ህዝቧን ለሚጠቅም አንድነት ከመቆም ፋንታ ህዝቧን ለሚጎዳ ጎሰኝነት ቆመች! ከጎሰኞች ጋር አብሮ አጨበጨበች። ምክር አልሰማ (https://www.youtube.com/watch?v=WaDzzD8uCYU&t=9s) አለች። አሁን ጉዳቱን እያየች እያለ እንዴት የ40 ዓመት እምነቷን ትቀየር?!
ከባድ ነው። ቅድም እንዳልኩት እስካሁን መግዛታቸውም አሁን ለውጥ ለማድረግ ማሰባቸውን ይደነቃል። ከተነከሩበት ርዕዮተ ዓለም መውጣት ከባድ ነው። ይህ ነው የህወሃት ትግል። የኛ ትግል ደግሞ አይዟችሁ እያልን ሳንፈርድባቸው እራሳችንን ደግሞ እያጠነከርን መሄድ ነው።
ሌሎቻችን ይህ አመሰራረት ለህወሓት ምን ያህል ማነቆ እንደሆነ በቂ የሚገባን አይመስለኝም። በተማሪ ንቅናቄ ዘመን በነ ዋለልኝ መኮነን አይነቱ ተማሪና ምሁራን አመለካከት የኢትዮጵያ መሪዎች ብቻ ሳይሆኑ ኢትዮጵያ ሀገሪቷ እራሷ ጥላቻና ስር ነቅል ለውጥ ይገባት ነበር። የኢትዮጵያ ታሪክና ትውፊት በሙሉ ክፉና የተጣመመ ነውና መደምሰስ አለበት ተብሎ ነበር የሚታሰበው። ሃይማኖትም አብሮ እንደ ጠላት ይታይ ነበር። ኢትዮጵያ እንዳለ ተጥሎ ሙዚቃ፤ ጭፈራና ሙዚየሞች ብቻ ቀርተው ሌላው ባህልና ትውፊት በሁሉም ዘርፍ መጣል አለበት ነበር የነበረው አስተሳሰቡ።
ሻዕቢያና ህወሓት መካከል ደግሞ ከዚህ ሁሉ «የማንነት ጥላቻ» አልፎ የ«አማራ» ትላቻን አቀፉ። ለምን ቢባል ርዕዮተ ዓለማቸው ሁልጊዜ በጠላትነት የሚሰየም ቡድን ስለሚያስፈልገው የአማራ የግዥ መደብ ጨቋኝ ነው ተብሎ የዚህ የ«ጠላትን» ሚና ለመጫወት ምቹ ስለነበር።
እዚህ ጋር ቆም ብለን አንድ ጥያቄ መመለስ አለብን። በዛን ዘመን ከኢትዮጲያ ምሁራንና ፖለቲከኞች መካከል እንደዚህ አይነት አስተሳሰብ የሰፈነው በዓለም ዙርያ የነበረው የግራ ጸንፍ አመለካከት ብቻ ተመስርቶ ነው? በፍፁም። ሃገር ውስጥ ያለው ሁኔታ ነው ታላቁን ሚና የተጫወተው። በዛን ወቅት የነበረው የፖለቲካ አመራር ብዙሃኑ የሚያስፈልገውን የፍትሕና የሰላም መግባሮች ስላላሟላ ነው። መልካም አስተዳደር ባለመኖሩ ብሶት ተከማችቶ ነው ምሁራኑም ፖለቲከኞችም ወደዛ ወደ ሀገር አጥፊ ርዕዮተ ዓለም የገቡት።
ይህ ዋና ነጥብ ነው። ጣቶቻችንን እነህወሓት ላይ ብቻ እንዳንጠቁም ያስታውሰናል። እራሳችንን በሃሰት ከችግሩ መንጭ ነጻ አድርገን እንዳናይ ይረዳናል። ለሀገራችን ህልውና እና ትክክሉን መፍትሄ ለማግኘት «የተማሪው ንቅናቄ እና ተከታዮቹ የተፈጠሩት በራሳችን ጥፋት ነው» ብለን ማመን አለብን። እነዚህ ነገሮች ከመሬት አልተነሱም። ሁላችንም ጥፋታችንን መቀበል አለብን። ፈራጅ መሆን የለብንም። እርግት መፀፀት ነው ያለብን። በዚህ አህነት አስተሳሰብ ብቻ ነው እውነተኛው ፍትሕ እና ሰላም የሚገኘው። ሌሎችን ዝምብሎ በመኮነን ሳይሆን ሌሎችን በመረዳት እና እንደወንድማማቾች አንዱ የሌላውን ችግርና አመጣጥ በማወቅ ነው መፍትሄ ማምጣት የሚቻለው።
በዚህ ረገድ የህወሓትን እና የሻዕቢያን ታሪክን ስንመለከት እነዚህ ድርጅቶች ከተመሰረቱ ጀምሮ በተለይ የደርግ የኢትዮጵያ መንግስት ጽንፈኝነታቸውን እና በኢትዮጵያ ያላቸውን ጥላቻ እንዲጨምርና እንዲንር ነው ያደረገው። የደርግ መንግስት የነህወሓትን ጥላቻና ብሶት ደመደመላቸው። በታሪክ በጎሳና በኢትዮጵያዊነት ያላቸውን ርዕዮተ ዓለማቸውን አረጋገጠላቸው። ከዛም ይባስ ሀገሪቷን አሳልፎ ሰጣቸው!
በ1950 አብዛኛው ኤርትራዊ ኢትዮጵያን ይወዱ ነበር ኢትዮጵያዊ ነን ይሉ ነበር። 40 ዓመት በኋላ ኢትዮጵያን ይጠሉ ነበር ኢትዮጵያዊም አይደለንም አሉ። እጅግ ያሳዝናል። የሀገራችን የፖለቲካ ችግር መጠኑን ምን ያህል እንደነበረ አሁንም እንደሆነ በደምብ ያሳየናል።
ህወሓት ስልጣን ከያዘ ጀምሮ የሚያምንበት እና እንደ የስልጣን ስልት የሚጠቀምበትን ጎሰኝነትን አራግቧል። በህግ ደረጃ ብቻ ሳይሆን በማሕበረሰቡ ፕሮፓጋንዳ በመንዛት። ህወሓት ለነባር ኢትዮጵያ ያለውን ጥላቻ በተግባር አሳይቷል። ለምሳሌ «ኦርቶዶክስ ሃይማኖት ይድከም»፤ «ኢትዮጵያዊነት ይድከም» የህወሓት እና ደጋፊዎቹ መፈከር ነበሩ። ትንሽ ቢያሰቡበት ኖሮ ግን ይህ አቋማቸው ለሚወክሉት የትግራይ ህዝብ እጅግ ጎጂ እንደሆነ ይገነዘቡት ነበር! አብዛኛው ትግሬ ኦርቶዶክስ ነው። ትክክል ቢሆንም ባይሆንም የጽንፈኛ ሙስሊም አካሄድ ያሳስባቸዋል። ኢትዮጵያ ውስጥ ደግሞ ጎሰኝነት ከሰፈነ በኢትዮጵያ ተጠቃሚ የሆኑት ትንናሽ ብሄሮች እንደ ትግሬና ጉራጌ ነው በመጀመርያ የሚጎዱት። እንደ ኦሮሚያ አይነቱ ትልቅ ብሄር ጎሰኝነትን ቢያራምድም የሚከተሉትን ጉዳቶችን በመጠኑም ቢሆን በግዙፍነቱ ምክንያት ሊቋቋማቸው ይችል ይሆናል። ትግራይ ግን የጎሰኝነትን እልቂት ልትቋቋም አትችልም። በነዚህ ምንክንያቶች የትግራይ ጥቅም የነበረው አሁንም የሆነው በጎሳ ያልተከፋፈለች አንድ ፈደራላዊ ኢትዮጵያ ነው። ግን ህወሓት ይህን እውነታ ትቶ የሚወክለውን ህዝብ የሚጎዳው አቋምን አራመደ።
ይህ የህወሓት ቅዠት (ወይም schizophrenia)በኃይለ ሥላሴ ዘመን የነበረው የኢትዮጵያ ፖለቲካ አለመስተካከል ምን ያህል ጉዳት እንዳመጣ ያሳየናል። የተለያዩ ጎራዎች ለመብትና ለጥቅማቸው ከመታገል ፋንታ በሚጎዳቸው እና ጥማቸውን በሚሽር መንገድ እንዲ ሄዱ አረገ! ህወሓት ለዚህ ሁሉ ዓመት ህዝቧን ለሚጠቅም አንድነት ከመቆም ፋንታ ህዝቧን ለሚጎዳ ጎሰኝነት ቆመች! ከጎሰኞች ጋር አብሮ አጨበጨበች። ምክር አልሰማ (https://www.youtube.com/watch?v=WaDzzD8uCYU&t=9s) አለች። አሁን ጉዳቱን እያየች እያለ እንዴት የ40 ዓመት እምነቷን ትቀየር?!
ከባድ ነው። ቅድም እንዳልኩት እስካሁን መግዛታቸውም አሁን ለውጥ ለማድረግ ማሰባቸውን ይደነቃል። ከተነከሩበት ርዕዮተ ዓለም መውጣት ከባድ ነው። ይህ ነው የህወሃት ትግል። የኛ ትግል ደግሞ አይዟችሁ እያልን ሳንፈርድባቸው እራሳችንን ደግሞ እያጠነከርን መሄድ ነው።
Friday, 16 February 2018
ይሄ ነው ራዕይ!
በያንዳንዷን ጥቃቅን ነጥብ ባልጋራም አቶ አቢይ አህመድ በዛሬው ኢትዮጵያ እንደዚህ አይነት ወርቅ የሆነ አመለካከት፤ ሃሳብና እቅድ ማርቀቅ መቻላቸው እጅግ ያስደንቃል!
በተለይ ስለውህደት ለሰላምና ፍቅር አስፈላጊነት ያሉትን በደንብብ ያዳምጡ። በተለይ በተለይ ስለቋንቋ በውህደት ያለው ሚና!
የአብይ አህመድ ራዕይ!
ብራቮ!
በተለይ ስለውህደት ለሰላምና ፍቅር አስፈላጊነት ያሉትን በደንብብ ያዳምጡ። በተለይ በተለይ ስለቋንቋ በውህደት ያለው ሚና!
የአብይ አህመድ ራዕይ!
ብራቮ!
ጨቋኝና ተጨቋኝ
እንደተረዳሁት ባለፈው ባወጣው መግለጫ ኦህዴድ የኢትዮጵያ መሰረታዊ የጭቆና ታሪክ የ«መደብ ጭቆና» ነበር እንጂ የ«ብሄር ጭቆና» አልነበረም ብሏል። ለዚህ አቋማቸው ኦህዴድን አደንቃለው አመሰግናለውም። ከረዥም ዓመታት የተሳሳተ እምነታቸው መቀየር ከባድ ነውና ጥንካሬና ህሊና ይጠይቃል። ዛሬ በሃገራችን ያለውን ከፍተኛና ኢ-ጤናማ የጎሳ ውጥረትንም ተገንዝበው የተሳሳተ ርእዮተ ዓለማቸውን ገምግመው ሃሳባቸውን ቀይረው ይህንን በይፋ ማውጣታቸው ትልቅ ነገር ነው። ደግሞ ከሌሎች አጋር ፓርቲዎቻቸው ቀድመው ይህን ማድረጋቸውም ሊደነቅላቸው ይገባል። እነ ለማ መገርሳ ለኢትዮጵያዊነት ታላቅ አስተዋጾ እያደረጉ ነው።
ሆኖም ይህ ዜና በሃገራችን መሰረታዊ የሆነ አሳዛኝ አስተሳሰብ አሁንም እንዳለ ይገልጻል? «ጨቋኝ» እና «ተጨቋኝ» እራሱ የተሳሳተ ቋንቋ ነው። ጽንሰ ሃሳብ የመጣው ከውሸትና ኢባህላዊ የሆነ የምእራባዊ የኮምዩኒስት አስተሳሰብ የመነጨ ነው። እስቲ አንድ እርምጃ ወደ ኋላ ተመልሰን ለምንድነው የሰው ታሪክ በ«ጨቋኝና ተጨቋኝ» የሚለው አስተሳሰብ መወሰን ያለበት? እንደዚህ አይነቱ አስተሳሰብ በሃሳብም ደረጃ በተግባርም ግጭት፤ ቅሬታ፤ ቂም፤ ጦርነት፤ ግድያ፤ አብዮት ወዘተ የሚያስገድድ ነው። አንድነት፤ ፍቅር፤ ይቅርታ፤ ትህትና፤ መስማማት ወዘተ የሚቃረን አስተሳሰብ ነው።
አልፎ ተርፎ ማን ግለሰብም ህብረተሰብም ፍፁም ንፁሃን ፍፁም ጥፋተኛ የሆነ የለም። እያንዳዳችን ጨቁነናል ተጭቁነናል፤ በድለናል ተበድለናል፤ ወደናል ተወደናል፤ ተስማምተናል ተጣልተናል፤ ተሳስተናል ስታታችንን አምነን ይቅርታ ጠይቀናል፤ ቂም ይዘናል ይቅርታን ተቀብለናል። በዚህ ዓለም እኔ ነኝ ንጹ ተጨቋኝ የሚል የራሱን ጥፋት ስለማይመለከት ወደ ከባድ ጥፋጡስት ይገባል ሰፊ በደልም ይፈጽማል።
በዚህ ጉዳይ ታላቅ የሩሲያ ደራሲ አለክሳንደር ሶልዠኒትሲን ያሉትን በደምብ ሊገባን ይገባል፤
ይህ ሩሲያዊ ሶልዠኒትሲን የዘመኑን «ጭቋኝና ተጨቋኝ» አስተሳሰብን ትተው የእውነትን ባህላዊ የኢትዮጵያዊ አስተሳሰብ ነው የገለጹት። ሩሲያዊው ኦርቶዶክስ ባህላችንን ያስታውሱን። ለምንናውም የኢትዮጵያ ባህል፤ ማንኛውም ሃይማኖት፤ ይህ የ«ጨቋኝና ተጨቋኝ» ርእዮተ ዓለም በአድ ነው። በአድ ነው። ሚስኪኖቹ የጃንሆይ ተመሪዎች ወደ ሃገራችን ከምእራብ ሃገራት ያመጡት መርዝ ነው። መርዙን እናውጣው። ወደ እራሳችን እንመለስ።
ሆኖም ይህ ዜና በሃገራችን መሰረታዊ የሆነ አሳዛኝ አስተሳሰብ አሁንም እንዳለ ይገልጻል? «ጨቋኝ» እና «ተጨቋኝ» እራሱ የተሳሳተ ቋንቋ ነው። ጽንሰ ሃሳብ የመጣው ከውሸትና ኢባህላዊ የሆነ የምእራባዊ የኮምዩኒስት አስተሳሰብ የመነጨ ነው። እስቲ አንድ እርምጃ ወደ ኋላ ተመልሰን ለምንድነው የሰው ታሪክ በ«ጨቋኝና ተጨቋኝ» የሚለው አስተሳሰብ መወሰን ያለበት? እንደዚህ አይነቱ አስተሳሰብ በሃሳብም ደረጃ በተግባርም ግጭት፤ ቅሬታ፤ ቂም፤ ጦርነት፤ ግድያ፤ አብዮት ወዘተ የሚያስገድድ ነው። አንድነት፤ ፍቅር፤ ይቅርታ፤ ትህትና፤ መስማማት ወዘተ የሚቃረን አስተሳሰብ ነው።
አልፎ ተርፎ ማን ግለሰብም ህብረተሰብም ፍፁም ንፁሃን ፍፁም ጥፋተኛ የሆነ የለም። እያንዳዳችን ጨቁነናል ተጭቁነናል፤ በድለናል ተበድለናል፤ ወደናል ተወደናል፤ ተስማምተናል ተጣልተናል፤ ተሳስተናል ስታታችንን አምነን ይቅርታ ጠይቀናል፤ ቂም ይዘናል ይቅርታን ተቀብለናል። በዚህ ዓለም እኔ ነኝ ንጹ ተጨቋኝ የሚል የራሱን ጥፋት ስለማይመለከት ወደ ከባድ ጥፋጡስት ይገባል ሰፊ በደልም ይፈጽማል።
በዚህ ጉዳይ ታላቅ የሩሲያ ደራሲ አለክሳንደር ሶልዠኒትሲን ያሉትን በደምብ ሊገባን ይገባል፤
ከእስርቤታችን አልጋ የሆነው የበሰበሰው ገለባ ላይ ጋደም ብዬ ነው ለመጀመርያ ከውስጤ የበጎ መንፈስ የተሰማኝ። ቀስ በቀስ መረዳት የጀመርኩት ይህ ነው፤ ጥሩና ክፉን የሚለየው መስመር በሀገሮች፤ መደቦች፤ የፖለቲካ ፓርቲዎችም መካከል አይደለም የሚያልፈው፤ ይህ መስመር የሚያልፈው በያንዳንዱ የሰው ልብ መኻል ነው። መስመሩ እድሜአችን በሙሉ ከውስጣችን ወደፊት ወደኋላ ይላል። በክፉ የተሞሉ ልቦችም ቢያንስ ቅንጣት ያህል ጥሩነት ይኖራል፤ ከሁሉም ጥሩ ከሚባለውም ልብ ከአንድ ጥጓ ትንሽ ክፉነት ይኖራል።ሶልዘኒትሲን ኮምዩኒስት የነበሩ ወታደር የነበሩ ስታሊን ለዓመታት በሞት እስር ቤት (ጉላግ) ያሰራቸው ከሩሲያ ወደ ኦርቶዶክስ ሃይማኖታቸው የተመለሱ የሩሲያ ጀግና ነበሩ። ተጨቋኝ ነኝ ማለት የሚገባቸው ነበሩ። ለሃገረቸው ጦርነት ተዋግተው በማግስቱ የታሰሩ ናቸው። አለምንም ጥርጥር ተጨቋኝ ነኝ ማለት የሚገባቸው ነበር። ግን እስር ቤት የሌሎችን ሳይሆን የራሳቸውን ኃጢያት እንዲገለጽላቸው አደረገ! የሰው ልጅ እውነተኛ ባሕርይ እንዲረዱ አደረገ። የሰው ልጅ ችግርም እንዴት መቅረፍ እንደሚቻል ገባቸው። በጦርነት፤ በማስወገድ፤ በማባረር፤ በመወገን ሳይሆን በንስሃ፤ በመስማማት፤ በመከባበር፤ በመቻቻል ነው።
በየቦታው እየዞሩ ያሉ ክፉ ስራ የሚሰሩ ክፉ ሰዎች ቢኖሩና እነሱን ከኛ መለየትና ማጥፋት ብቻ ቢሆን ኖሮ እንዴት ቀላል ነበር? ግን ጥሩና ክፉን የሚለየው መስመር ከያንዳንዱ የሰው ልጅ ልብ መካከል ነው የሚያልፈውና ማን አለ ከራሱ ልብ ቁራጭ ቆርጦ ለማጥፋት ፈቃደኛ ይሆነ?
ይህ ሩሲያዊ ሶልዠኒትሲን የዘመኑን «ጭቋኝና ተጨቋኝ» አስተሳሰብን ትተው የእውነትን ባህላዊ የኢትዮጵያዊ አስተሳሰብ ነው የገለጹት። ሩሲያዊው ኦርቶዶክስ ባህላችንን ያስታውሱን። ለምንናውም የኢትዮጵያ ባህል፤ ማንኛውም ሃይማኖት፤ ይህ የ«ጨቋኝና ተጨቋኝ» ርእዮተ ዓለም በአድ ነው። በአድ ነው። ሚስኪኖቹ የጃንሆይ ተመሪዎች ወደ ሃገራችን ከምእራብ ሃገራት ያመጡት መርዝ ነው። መርዙን እናውጣው። ወደ እራሳችን እንመለስ።
Thursday, 15 February 2018
ቤተ ክርስቲያን መቅደም አለባት!
ከትላንት ወድያ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ዙርያ ያልጠበቅናቸው መልካም አሳቢዎች እንደ ለማ መገርሳና አቢይ አህመድ ብቅ ማለት ጀመሩ። ትላንትና መንግስት ለረዥም ዓመታት የሚለመነውን ነገር አደረገ፤ ያለጥፋት የታሰሩትንና የተሰቃዩትን በርካታ እስረኞችን ፈታ። ዛሬ ደግሞ ጠቅላይ ሚኒስቴራችን ኃይለማርያም ደሳለኝ በፈቃደኝነታቸው ስልጣናቸውን ከቀቁ። መልካ ለውጦች ይታያሉ፤ እግዚአብሔር መጨረሻውን ያሳምርልን።
ግን ከፖለቲካው ቤተ ክርስቲያናችን መቅደም አልነበረበትም? (ይህን ስል እኔም እንደ አንድ ምእመናን እራሴን እየወቀስኩኝ ነው።) የኛ ለማ መገርሳዎች፤ በትህትና አለመፍረድ፤ በፍቅርና በምሳሌ፤ የሚናገሩት የት አሉ? እርግጥ አሉ፤ ግን በሌሎቻችን ተከበው ድምጻቸው በአግባቡ አይሰማም። እስረኞችንን መቼ ነው የምንፈታው? በርካታ እስረኞች አሉን፤ ፍቅር፤ ሃላፊነት፤ እርቅ፤ ትህትና፤ ሰላም። እነዚህንንሁሉ አስረን ቁጭ ብለናል። መቼ ነው የምንፈታቸው? ደግሞ መቼ ነው ሃላፊነት ወስደን እራሳችንን ህዝብ ፊት ዝቅ የምናደርገው። እንዲህ የሚያደርጉ አሉ ግን በኔ አይነቱ ተከበው አይታዩም። እንቅፋትም ሆነናቸዋል።
ቤተ ክርስቲያናችን እንደ አቡነ ጴጥሮስ መምራት መጀመር አለባት። በፖለቲካው መመራት ወይም መቀደም እፍረት ነው። አሁን ከቤተ ክርስቲያን እርቅ በፊት በሃገራችን ፖለቲካ እርቅ ቢመጣ ታላቅ እፍረት አይደለም? ከዛ በሗላ መጀመሪያውኑ ፖለቲካ ነው ያስቸገረን ብለን ልናሳብብ ነው? እነ ቅዱስ ጴጥሮስ በሮሜ ፖለቲካ እየተሰውዉ ደፍሮ ያላሉትን ልንል ነው?! ይህ ቢሆን እጅግ አሳሳዛኝ ነው።
ስለዚህ እንምራ! በሃገር ውስጥና በውጭ ያሉት ስይኖዶስ መካከል ፈጥነን እርቅ እናምጣ። ለኢትዮጵያ ህዝብ ምሳሌ እንሁን። ፈተናው ብዙ ነው። ገና እየበዛ ይሄዳል። ግን እግዚአብሔር ሁልጊዜ በሁሉም ቦታ ከኛ ጋር ነው። ይህን ካመንን ለፍቅር እንድፈር፤ አንፍራ!
ግን ከፖለቲካው ቤተ ክርስቲያናችን መቅደም አልነበረበትም? (ይህን ስል እኔም እንደ አንድ ምእመናን እራሴን እየወቀስኩኝ ነው።) የኛ ለማ መገርሳዎች፤ በትህትና አለመፍረድ፤ በፍቅርና በምሳሌ፤ የሚናገሩት የት አሉ? እርግጥ አሉ፤ ግን በሌሎቻችን ተከበው ድምጻቸው በአግባቡ አይሰማም። እስረኞችንን መቼ ነው የምንፈታው? በርካታ እስረኞች አሉን፤ ፍቅር፤ ሃላፊነት፤ እርቅ፤ ትህትና፤ ሰላም። እነዚህንንሁሉ አስረን ቁጭ ብለናል። መቼ ነው የምንፈታቸው? ደግሞ መቼ ነው ሃላፊነት ወስደን እራሳችንን ህዝብ ፊት ዝቅ የምናደርገው። እንዲህ የሚያደርጉ አሉ ግን በኔ አይነቱ ተከበው አይታዩም። እንቅፋትም ሆነናቸዋል።
ቤተ ክርስቲያናችን እንደ አቡነ ጴጥሮስ መምራት መጀመር አለባት። በፖለቲካው መመራት ወይም መቀደም እፍረት ነው። አሁን ከቤተ ክርስቲያን እርቅ በፊት በሃገራችን ፖለቲካ እርቅ ቢመጣ ታላቅ እፍረት አይደለም? ከዛ በሗላ መጀመሪያውኑ ፖለቲካ ነው ያስቸገረን ብለን ልናሳብብ ነው? እነ ቅዱስ ጴጥሮስ በሮሜ ፖለቲካ እየተሰውዉ ደፍሮ ያላሉትን ልንል ነው?! ይህ ቢሆን እጅግ አሳሳዛኝ ነው።
ስለዚህ እንምራ! በሃገር ውስጥና በውጭ ያሉት ስይኖዶስ መካከል ፈጥነን እርቅ እናምጣ። ለኢትዮጵያ ህዝብ ምሳሌ እንሁን። ፈተናው ብዙ ነው። ገና እየበዛ ይሄዳል። ግን እግዚአብሔር ሁልጊዜ በሁሉም ቦታ ከኛ ጋር ነው። ይህን ካመንን ለፍቅር እንድፈር፤ አንፍራ!
Wednesday, 7 February 2018
ሞኙ ህብረተሰብ
ከአባ ቲኾን (ሼቭኩኖቭ) መጸሃፍ Everyday Saints፤ «ሞኙ ህብረተሰብ»። ትርጓሜው የኔ አይደለም።
በአንድች ሰነፍና የተኛች ይቢዛንቲየም ከተማ: የጥሩውን እና የሽማግሌውን ጳጳስ ምክር ተቃውሞ እና ልመና ትንሽ እንኳን ሳይፈሩ የከተማው ሰዎች በሚሰሩት ግብረ ገብ መጣስና ህግ ማፍረስ ሀፍረተ ቢሶች ሆነዋል። እንደውም በጳጳሱ ላይ ሳቁበት በዕኩይ ስራቸውም ገፉት።
በመጨረሻም ሽማግሌው ጳጳስ ሞተ እና አዲስ ጳጳስ ተሾመላቸው። አዲሱ ተሿሚም የከተማው ሰዎች እስኪደነቁ እና እስኪያዝኑ ድረስ ስርዓት የሌለው በቅንጦት የሚኖር ጉቦኛ ሆነ እና ደጉን እና ሟቹን ጳጳስ እንዲናፍቁ አደረጋቸው ።
በተደጋጋሚ የሚፈጽመውን ጉቦኝነት ማዋረድ ድብደባ እና ከሁሉበላይ ደግሞ ማመን ያቃታቸው ለከት የሌለው ረብሻ መቋቋም ባለመቻላቸው በአንድነት ሆነው ወደ እግዚአብሔር «ጌታ ሆይ እንደዚህ አይነት ጭራቅ ለምን ላክህብን?» በማለት ጮሁ።
እንዴት እንደሚጸለይም አያውቁም ሰለነበር ዝም ብለው ጮሁ። ከብዙ ጩኸት በኋላ ጌታ ለአንዱ የከተማው አባት ተገልጾ «ከእሱ የከፋ ለማግኘት ሞከርኩ ነገር ግን ለማግኘት አልቻልኩም» አለው።
ሞኙ ህብረተሰብ
በአንድች ሰነፍና የተኛች ይቢዛንቲየም ከተማ: የጥሩውን እና የሽማግሌውን ጳጳስ ምክር ተቃውሞ እና ልመና ትንሽ እንኳን ሳይፈሩ የከተማው ሰዎች በሚሰሩት ግብረ ገብ መጣስና ህግ ማፍረስ ሀፍረተ ቢሶች ሆነዋል። እንደውም በጳጳሱ ላይ ሳቁበት በዕኩይ ስራቸውም ገፉት።
በመጨረሻም ሽማግሌው ጳጳስ ሞተ እና አዲስ ጳጳስ ተሾመላቸው። አዲሱ ተሿሚም የከተማው ሰዎች እስኪደነቁ እና እስኪያዝኑ ድረስ ስርዓት የሌለው በቅንጦት የሚኖር ጉቦኛ ሆነ እና ደጉን እና ሟቹን ጳጳስ እንዲናፍቁ አደረጋቸው ።
በተደጋጋሚ የሚፈጽመውን ጉቦኝነት ማዋረድ ድብደባ እና ከሁሉበላይ ደግሞ ማመን ያቃታቸው ለከት የሌለው ረብሻ መቋቋም ባለመቻላቸው በአንድነት ሆነው ወደ እግዚአብሔር «ጌታ ሆይ እንደዚህ አይነት ጭራቅ ለምን ላክህብን?» በማለት ጮሁ።
እንዴት እንደሚጸለይም አያውቁም ሰለነበር ዝም ብለው ጮሁ። ከብዙ ጩኸት በኋላ ጌታ ለአንዱ የከተማው አባት ተገልጾ «ከእሱ የከፋ ለማግኘት ሞከርኩ ነገር ግን ለማግኘት አልቻልኩም» አለው።
Subscribe to:
Posts (Atom)