Wednesday 27 June 2018

ችኮላ

ጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ ለውጦችን በአስገራሚ ፍጥነት ነው እያመጡ ያሉት። መቼም አንዳችን በዚህ ፍጥነት ለውጦች ይመጣሉ ብለን ገምተን ነበር የሚል ካለ ይገርመኛል። እርገጥ ኤርሚያስ ለገሰ አብይ አህመድን ስኬታማ ለመሆን ፍጠን ብሏቸው ነበር ግን እርግጠኛ ነኝ እሱም እንደዚህ ይፈጥናሉ ብሎ አልጠበቀም። አንዳችንም አልጠበቅነውም ብለን በትህትና ብናምን ጥሩ ይመስለኛል!

ፈጥኗል ግን ከመጠን በላይ ፈጥኖ ይሆን? ጥሩ ጥያቄ ነው መልሱንም አላውቅም። ከሁላችንም በላይ ከፖለቲካ ጦርነት ውስጥ ያሉት አብይ እና ቡድኑ ነው ያሚያውቁት። ከመጠን በልይ መፍጠን እንደሚቻል ግን ይታወቃል። «ዴሞክራሲ ይስፈን»፤ «ፍትህ ይኑር»፤ «ያለፉት የፖለቲካ እና ሰብዓዊ ወንጀሎች ይጣሩ»፤ «የፖለቲካ ወንጀለኞች ይፈረድባቸው»፤ «ህገ መንግስቱ ይቀየር»፤ «ሀገ መንግስቱ በትክክሉ ይፈጸም» ወዘተ መፈክሮች ምአት ናቸው። የምንፈልገውን በሙሉ አሁኑኑ ይደረግልን የሚሉ አሉ።

ግን የ27፤ የ40፤ የ50፤ የ100 ወዘተ ዓመታት ችግሮች በአንዴ አይፈቱም፤ ይህንን ሁላችንም እናውቃለን። ከብዙ ሰዎች ይህን ጥሩ ምሳሌ ሰምችአለሁ፤ ሀገራችን እንደ ማንኛውም የከባድ በሽታ ህመምተኛ ለህልውናው የሚያሰጋው እና በውቅቱ መታከም የሚችሉ ቁስሎችን ነው በጀመርያ መታከም ያለበት። እነዚህ ህመሞች ሲድኑ ወደሚቀጥሉት መሄድ ነው። የህቅምናውን ቀደም ተከተል በደምብ የሚአቁት ከህመምተኛው ቅርብ ያሉት የሚያክሙት ሐኪሞች ናቸው። ግን እኛ ኢትዮጵያዊዎች ለሐኪሞቹ ተሽሎናል አልተሻለንም ብለን ምልክት መስጠት አለብን። ስለዚህ መፈክሮቹ ጥያቄዎቹ መቀጠል አለባቸው። ግን የነ ጠ/ሚ አብይንም አቅም እና የፖለቲካው ጠቅላላ ሁኔታ መረዳት አለብን። ቢያንስ ለራሳችን ብለን የማይሆን ነገር መጠበቅ የለብንም።

እርግጥ መጠበቅ ከባድ ነው ትእግስት ከባድ ነው። አንድ የሚያቀለው ነገር ግን ስራ ነው። ለለውጥ እንስራ! ጠ/ሚ አብይ ጋብዞናል። ከሰፈራችን፤ ከመስርያቤታችን፤ ከሃይማኖት ስፍራችን ወዘተ ሰላምን እናምጣ። ፍቅር እናምጣ። ሙስናን እና ተመሳሳይ ጎጂ ባህሎችን እንታገል። ከጎረቤታችን ጋር እንፋቀር (http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2016/09/blog-post_14.html)። ድሆችን እንርዳ። ብዙ ብዙ ስራ አለ። ጥያቄ ማብዛት ስራ አይደለም፤ ያንንማ ሁላችንም በቀላሉ እናደርገዋለን። እነዚህ የፍቅር ስራዎች ናቸው ከባድ። እነዚህን ስራዎች ብንሰራ ጥያቄዎቻችን እንዲመለሱ ያፈጥናሉ ትእግስትም ይኖረናል!



No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!