ዓመት በፊት ማንኛውም ኢትዮጵያዊን ምን አይነት የፖለቲካ ለውጥ ትፈልጋለህ ቢባል፤ «ዴሞክራሲ፤ ነፃነት፤ ፍትህ፤ እኩልነት» ይል ነበር። ጠ/ሚ አብይ ስልጣን ሲይዙ እንደዚህ አይነት መልእክቶች እና መፈክሮች ነበር የሚጠበቅባቸው። ግን እሳቸው «ፍቅር፤ ሰላም፤ ይቅር ማለት» አሉ። መንፈሳዊ መረጋጋትን ከፖለቲካ መረጋጋት አስቀደሙ። ይህን የድሮ ሰው ብቻ ነው የሚለው፤ የዘመኑ ሰዎች ምን ማለት እንደሆነም ሊገባን ያስቸግረናል።
ጠ/ሚ አብይ የፖለቲካ ለውጡን ሲጀምሩ በሀገራችን መልካም አስተዳደር እና ብልጽግና እንዴት እንደሚያመጡ ይነግሩናል ብለን ሁላችንም እንጠብቅ ነበር። በነዚህ ጉዳዮች ሲናገሩ ግን እኛ ካሰብነው አልፎ ሄዱ። እሳቸው እንኳን ለኢትዮጵያ ለምስራቅ አፍሪካ ቀጥሎም ለጠቅላላው አፍሪካ ምሳሌ የሚሆን እና የሚያስተምር መልካም አስተዳደር እና ብልጽግና እናመጣለን አሉ! እኛ ስለሀገራችን ኢትዮጵያ ብቻ ነው ያሰብነው። በዛሬ ዝቅተኛ ሞራላችን ከሀገራችን ውጭ ምሳሌ መሆን እንደምንችል በፍጹም አናስብም። ጠ/ሚ አብይ ግን ዛሬ የጊዜያዊ ድክመቶች ቢኖራትም ኢትዮጵያ የአፍሪካ መሪ ናተና ይህንን ተእልኮዋን አንረሳም ብቻ ሳይሆን እናሟላለን አሉ። እንዲህ ሲሉ 60 ዓመት በፊት የነበሩ ጀግና የኢትዮጵያ ልሂቃን የማዳምጥ መሰለኝ!
ጠ/ሚ አብይ አብዛኞቻቸው ትንተናቸውን የሚጀምሩት የኢትዮጵያ ታሪክ እና ወግ በመጥቀስ ነው። ለምሳሌ ስለ «ፍቅር፤ ሰላም፤ ይቅርታ» ሲያወሩ ወጋችን ነው ብለው ነው። ታሪካችን ጥላቻ፤ ጦርነት፤ እና ቂም በደምብ እንዳለበት አልተሳኑም ግን የታሪክ እና ወጋችን የመጨረሻ ግብ እና ፍጻሜ ፍቅር፤ ሰላም እና ይቅርታ እንደሆነ ያውቃሉ። በድክመታችን ላይ ሳይሆን በጥሩ ጎናችን ያቶኩራሉ። በዚህ ዘመን ማን እንዲህ ይላል? በዚህ ዘመን ብዙዎቻችን በዝቅተኛ መንፈስ የተሞላን ስለሆነን ከታሪክ እና ወጋችን ጥሩ ነገር አይታየንም። ግን ጠ/ሚ አብይ ታሪክ እና ወጋቸውን በሚገባው በእውነተኛ ፍቅር ነው የሚያዩት።
በኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ሁላችንም የጠበቅነው ጠ/ሚ አብይ መንግስት ካሁን ወድያ በቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ጣልቃ እንዳይገባ ያደርጋሉ ነው። ምናልባትም ይህን በይፋ ለህዝብ ይናገራሉ ነው። ግን እሳቸው እንደገና ከጠበቅነው አልፈው ቤተ ክርስቲያንን ነፃ መተው ብቻ ሳይሆን ወደ መርዳት ገቡ! መንግስት ላበላሸው ሃላፊነት አለበት ማስተካከል አለበት ብለው በሲኖዶሶቹ እርቅ እንዲኖር ምኞታቸውን ተናገሩ። መናገር ብቻ ሳይሆን ስልጣናቸውን እንደ ህሊና ግፊት በመጠቀም እርቁ እንደፈጸም አስተዋጾ አደረጉ። ጭራሽ ካልሆነ እግራችሁ ላይ ወድቄ እንድትታረቁ እለምናችኋለሁ አሉ! ማናችንም ይህን አልጠበቅንም።
ጠ/ሚ አብይ ለሀገራችን ባህላዊ ሃይማኖቶች ታላቅ ክብር አላቸው። እኛ የዘመኑ ሰዎች እንዚህን መዋቅሮች ከፖለቲካ ውጭ የሆኑ ኋላ ቀር ነገሮች ይመስሉናል። እሳቸው ግን ለሀገራችን ደህንነት እና ጤንነት አስፍላጊ እና መሰረታዊ እንደሆኑ ይገባቸዋል። እነሱን ትቶ ኢትዮጵያዊነት በአሸዋ የተመሰረተ ቤት እንድሆነች ያውቃሉ ይናገራሉ ያስተምራሉ። እንደዚህ አይነት አስተሳሰብ ከልሂቃኖቻችን ድሮ ነው የጠፋው።
ጠ/ሚ ዱባይ ሄደው ከአረብ ህብረት መሪ ጋር ሲወያዩ አረቡ ልንረዳችሁ አስበናል ምናልባትም ትምሕርት ቤቶች በኢትዮጵያ ለማቋቋም እያሰብን ነው አሉ። ጠ/ሚ አብይ እሺ አላሉም። ወይንም ጥሩ ነው ግን የኤኮኖሚ ኢንቬስትሜንት ይሻለናል አላሉም። እናንተ እምነታችሁን እያጣችሁ ስለሆነ እኛ አረብኛ ተምረን ሃይማኖትን መልሰን እናስተምራችኋለን አልዋቸው (https://www.youtube.com/watch?v=b3GUI1rD9-M)! እዩ በራሳቸው እና በሀገራቸው ምን ያህል እንደሚተማመኑ። ማናችን በዚህ ዘመን ያለነው ኢትዮጵያዊ እንደዚህ እናስባለን? ይህ የጠ/ሚ አብይ ንግግር ኢትዮጵያን በትክክለኛ በሚገባት ቦታ የሚያስቀምጥ ነው። እውነትም ነው። ግን ስንቶቻችን እንደዚህ አይነት አስተሳሰብ ከልባችን ይገባን ይሆን?
ጠ/ሚ አብይ መንግስታቸው ለፈጸማቸው በደሎች በቡድናቸው በኢህአዴግ ስም ሳይሆን በግላቸው ይቅርታ ጠይቀዋል። ይቅርታ የሚጠይቅ ሰው በራሱ የሚተማመን ነው (http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/07/blog-post.html)። በራሱ የማይተማመን ሰው ወይንም የዝቅተኛ መንፈስ ያለው ሰው ይቅርታ ማለት ድክመቱን ለሁሉም የሚገልጥ ይመስለዋል። ጠ/ሚ አብይ ግን ትንሽ ይቅርታ ሳይሆን ለኢህአዴግ ኃጢአት በሙሉ ግዙፍ ይቅርታ ጠየቁ።
ከዚም አልፎ ከተለያዩ በአንድ ወቅት እንደ ጠላት የሚቆጠሩ ሰዎች ጋር በሂሊና ነፃነት ይገናኛሉ ይወያያሉ። ከኢሳያስ አፈዎርቂ፤ አብዴል እል-ሲሲ፤ ግንቦት ሰባት፤ ታማኝ በየነ፤ ጀዋር መሃመድ፤ የተለያዩ የህወሓት ሹማምንት ወዘተ በሰላም ተገናኝተው በህዝብ ፊት አብሮ ይቀርባሉ። ከነዚህ ጋር አብሮ መታየቴ እና መወያየቴ ማንነቴን በግምት ያስገባዋል እና አጉል እተቻለሁ ብለው አያስቡም። ይህም በራስ የመተማመን ምልክት ነው። ምንም አይበረግገዋቸውም። ከማንም ጋር መነጋገር እችላለሁ "on my own terms" ነው አስተሳሰባቸው።
ጠ/ሚ አብይ በራሳቸው የሚተማመኑት በሰው ልጅነታቸው ብቻ ሳይሆን ከፖለቲካ አንጻር በኢትዮጵያዊነታቸው ሙሉ በሙሉ ስለሚኮሩ ነው። በዚህ በኩል የድሮ ሰው ናቸው። እንደ በምኒልክ ዘመን የነበሩት ከአውሮፓዊያን ጋር በእኩልነት ሳይ በበላይነት ስሜት የሚደራደሩ። እንደ በኃይለ ሥላሴ ዘመን ለኢትዮጵያ በዓለም ደረጃ እንደሚደራደሩት አልፎ ተርፎ ለአፍሪካ የሚዋጉት። የሰለባነት አስተሳሰብ (victim mentality)፤ በዝቅተኝነት መንፈስ (inferiority complex)፤ በልመና፤ ሌሎችን መለመን ወይንም እንደ ሌሎች መሆን መፈለግ የለም። ይህ አስተሳሰብ ድንቅ ነው በአሁኑ ዘመን ከሀገራችን ብዙ የማይገኝ ነው። ግን ኢትዮጵያ እንደገና እንደዚህ አይነት እንደ ጠ/ሚ አብይ አይነቱን ሰው ማፍረት መቻሏ ተመስገን ነው። ሁላችንም የሳቸውን አስተሳሰብ (mindset) ያኑርብን። የሀገራችን ብጎ ህልውና ከዚህ ነው የምጀረውና።
የሰላም ክፍሌ ይትባረክ ብሎግ፤ ስለ ሀገራችን ኢትዮጵያ ያለኝን ትናንሽ ሀሳቦች በትህትና አቀርባለሁ። ለስሕተቶቼም በቅድሚያ ይቅርታ እጠይቃለሁ
Showing posts with label አብይ አህመድ. Show all posts
Showing posts with label አብይ አህመድ. Show all posts
Friday, 10 August 2018
Friday, 3 August 2018
የበታችነት ስሜት
ሰላሳ አርባ ዓመታት በፊት ከሀገሩ የሚሰደድ ኢትዮጵያዊ ወደ ምዕራብ ሀገር ሲሄድ ከሀገሩ ይበልጥ «የሰለጠነ» እና «የበለጸገ» ሀገር አግኝቻለሁ ብሎ ያስቡ ነበር። የምዕራብ ሀገሮች በሀብት፤ በብልጽግና፤ በግብረ ገብነት፤ በቅልትፍና (efficiency)፤ በንፅህና ወዘተ ከኢትዮጵያ የላቁ መሆናቸው አብዛኛው ኢትዮጵያዊ ያምን ነበር።
ሆኖም ግን ስደተኛው ምዕራብ ሀገሮችን ቢያደንቅም የሚተችባቸው ጉዳዮች ነበሩ። ለምሳሌ «ዘረኝነትን ያራምዳሉ» ይላል። በአዲስ ቅኝ ግዛት ታዳጊ ሀገራትን ያጠቃሉ ይዘርፋሉ። ኢትዮጵያ ለቅኝ ግዛት ስለማትመች እነ አሜሪካ ካዷት እና በደርግ አይነቱ አረመኔ መንግስት በማርክሲዝም እንድትገዛ አደረጉ። በተለያዩ ሀገራት ሕጋዊ የሆኑ መንግስታትን ይገለብጣሉ። ወዘተ። ኢትዮጵያዊ ስደተኛው ልሂቃኑም የምዕራብ ሀገሮችን በዚህ መልኩ ይከሱ ነበር።
በርካታ ስደተኞች እንደዚህ በማለት የምዕራብ ሀገሮችን ተችተው ሀገራቸው ኢትዮጵያ ችግሮች ቢኖሯትም ከነዚህ ሀገሮች በማንነት ደረጃ አታንስም ብለው ያምኑ ነበር። በዚህ ምክንያት የሀገር የማንነት የበታችንነት ስሜት (inferiority complex) ገና ብዙ አላደረባቸውም። በኢትዮጵያዊነቱ ያለው ኩራት ብዙ አልተቦረቦረም ነበር።
ግን ጊዜው ባለፈ ቁጥር ኢትዮጵያ «አልሻሻል» ስትል ባንጻሩ የምዕራብ ሀገሮች በብልጽግና እይናሩ እና አንዳንድ ልውጦች ሲያደርጉ የፕሮፓጋንዳ ስልታቸውም እየዳበረ ሲሄድ ኢትዮጵያዊ ስደተኛው በአሙሮው የምዕራቡን ዓለም እያበለጠ ሀገሩ ኢትዮጵያን እያሳነሰ ሄደ። ቀስ በቀስ የበታችነት ስሜት (inferiority complex) እያደረበት ሄደ። የህ የበታችነት ስሜት ወደ ሀገር ቤትም ገባ።
ወደ ምዕራብ ሀገር የተሰደደ ኢትዮጵያዊ ደህና ገቢ ማግኘት እና ሃብት ማከማቸት ቻለ። ስደተኛው ድሮ ቢገጥመውም ባይገጥመውም የሚያማርረው ዘረኝነቱ እየቀነሰ ሲሄድ አየ። ለነገሩ ዘረኝነቱ ድሮም ኑሮውን ከማሻሻል አልከለከለውም ነበር። አህን ግን ጭራሽ በጥቁርነቱ ስራ ከማጣት ማግኘት ጀመረ! ባሜሪካ ልጆቹ በጉብዝናቸው ብቻ ሳይሆን የጭቁን (ጥቅር) ዘር በመሆናቸው ስኮላርሺፕ ማግኘት ጀመሩ። የአሜሪካ ኑሮ ከድሮም ይበልጥ እየተመቸ ሄደ።
ይህ ስደተኛ ኑሮው «እየተሳካለት» በሄደ ቁጥር አሜሪካ በሱ አይን ይበልጥ እያማረች ሄደች። ፍትሐዊና መሐበራዊ ስነ ሥርዐቱን ከድሮም ይበልጥ ማደነቅ ጀመረ። ለሴቶች፤ ለልጆች፤ ለጥቁሮች ወዘተ ያለው «መብት» እና ጥንቃቄ ከኢትዮጵያ ጋር ሲያነጻጽረው ይገርመዋል። በፖለቲካ ደረጃ «ዴሞክራሲ» አምላኩ ሆነ «ሲኤንኤን» (CNN) መላዕክቱ ሆነ። በአንጻሩ ኢትዮጵያ በስደተኛው አይን እየቀነሰች እየወረደች ሄደች። አልሻሻል አለች እየባሰችም ሄደች። ስደተኛው ሀገሩን በጎበኛት ቁጥር ከአሜሪካ ጋር እያንጻጸረ ዘመዶቹን ያደነቁራል። በአሜሪካ እና ኢትዮጵያ ያለውን ልዩነት ለማሳየት ያህል ዘመዱን ከ«ሀገር ቤት» ለመውጣት በርካታ አስር ሺዎች ዶላር ይከፍላል።
ዛሬ በኛ በኢትዮጵያውያን የዝቅተኘት መንፈስ በደምብ አድሮብናል ማለት ከእውነት የራቀ አይመስለኝም። ግን ይህ መንፈስ እውነትን ነው የሚያንጸባርቀው? እውነት ዝቅተኛ ህብረተሰብ ነን? ወይም ሀገራችን ዝቅተኛ ነው? ይበልጥ ታላቅ የሆነው ጥያቄ ሙሉ ሰው ለመሆን ወይንም በዘመኑ ቋንቋ «መሻሻል» ከፈለግን እንደ ምዕራቡ ዓለም መሆን ይኖርብናል? ምናልባት ዘፈናችን ጭፈራችን ምግባችንን ለትዝታ ብለን ጠብቀን በሌላው በሙሉ እንደነሱ እንደ ምዕራባዊያን መሆን ይኖርብን ይሆን?
እዚህ ላይ በቀለም ትምሕርት ከምንማረው በሚዲያ ከምንሰማው ፕሮፓጋንዳና ተራ «እውቀት» ወጥተን እናስብ። በአዲሱ ቅን ግዛት የተገዛውን አእምሮአችንን ነፃ እናውጣው የብዥታ መነጽራችንን እንጣል። በመጀመርያ እስቲ ምንድነው «ስልጣኔ» ብለን እንጀምር። ጥያቄውን በምሳሌ ኃይል ለመመርመር ታዋቂውን የሮሜን ስልጣኔን እንመልከት።
በክርስቶስ ዘመን በርካታ አይሁዶች ወደ ሀገራቸውን ወርሮ የገዛው ሮሜ ይፈልሱ ነበር። አንድ አይሁድ ወደ ሮሜ ሲሄደ ዛሬ ኢትዮጵያዊ ከሀገሩ ወደ አሜሪካ እንደመሄድ እናመሳስለው። ሮሜ ሀብታም ነበረች። «ስደተኞችን» መጤዎችን ትቀበላለች ታስተናግዳለች ታበለጽጋለች። ውጣ ውረድ ቢኖረውም መጤዎች የሮሜ ዜጋ የመሆን እድል አላቸው። የሮሜ ዜግነት አንደ ይሁዳ ዜግነት በጎሳ በብሄር በደም የተወሰነ አይደለም ማንም የሮሜ ዜጋ መሆን ይችላል። የሮሜ ፍርድ ቤቶች በደምብ ይሰራሉ በተለይ ለሮሜ ዜጎች እውነተኛ ፍትሕ ይሰጣሉ። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ችግር ባጋጠመው ቁጥር አይሁዶች ሲገሱት ሲሉ የሮሜ ዜግነቱን ተጠቅሞ ፍርድ ይጠይቃል! በሮሜ ፍርድ ቤት ትክክለኛ የፍርድ ሂደት እንደሚጠብቀው ስለሚያውቅ ነው። የሮሜ መንግስታዊ አስተዳደር ፍፁም ባይሆንም ከሌሎች አንጻር «የሰለጠነ» ነበር። «ዴሞክራሲ» አይነት ከነ ምክር ቤት አለው። በሮሜ የማሕበራዊ ብረ ገብ አለ። የሴቶች «መብቶች» ከሌሎች ሀገሮች ከይሁዳ ይልቅ የተከበሩ ናቸው። በስነ ሥርዓት በኩልም ሮሜ የስለጠነች ናት። መንገዶቿ ንፁ ናቸው። መንገደኛ ለመንገደኛ ጎረቤት ለጎረቤት አገልጋይ ለባለጉዳይ ያለው ግንኙነት በጥቅም የተሳሰረ ሰላማዊና የተቀላጠፈ (efficient) ነው። የድሮ «ሮሜ» ስልጣኔ እንደዚህ ይመስላል።
ለዚህም ነው አይሁዶችም ሌሎችም ወደ ሮሜ የሚፈልሱት ሃብቱን እና ስልጣኔውን ፈልገው። ልክ እንደ ኢትዮጵያውያን ወደ አሜሪካ እንደምንፈልሰው «ህይወትን ለማሻሻል» ወደ በአድ ሀገር ይሄዱ ነበር። ግን ሮሜ የይሁዳ ቅኝ ገዥ ነበረች! አይሁዶች ወደ የሚገዛቸው ሀገር ነበር የሚሄዱት። ወደ ዓለምን በሙሉ በጉልበቷ የተቆጣጠረቹ ሮሜ ነበር ለተሻለ ኑሮ ብለው የሚሄዱት። ግን አይሁዶቹንም ሌሎች መጤዎችንም የሮሜ ስልጣኔ ክፋነቷን እንዳያዩ አድርጓቸዋል አሳውራቸው። ለነሱ ሮሜ የብልጽግና ሀገር እንጂ የክፋት ሀገር አልነበረትም። ሮሜ ሀገራቸው ይሁዳ የሌላት ነገሮች ሁሉ አላት። በዚህ ምክንያት በራሳቸው ባህልና ማንነት ዝቅጠኝነት ተሰማቸው እንደ ሮሜዎች መሆነ ፈለጉ ወደ ሮሜ ህብረተሰብ ተቀላቀሉ።
ይህ ምሳሌ ስለ «ስልጣኔን» ምን ያስተምረናል? ለብዙዎቻችን ስልጣኔ ሀብት ማለት ነው። ሀብት ካለ ሌሎች ጉድለቶች አያታዩንም። ስልጣኔ «ቴክኖሎጂ» ይመስለናል። የሮሜ የከተማው ቧምቧ እና ፍሳሽ ስራ አይሁዶችን ይገርማቸው ነበር። ስልጣኔ ቅልጥፍና (efficiency) ይመስለናል። የሮሜ የመነግስት መዋቅሮች በተለይ ጦር ሰራዊቱ ግቡን በቀላሉ ያስፈጽም ነበር። ስልጣኔ ፍትሕ ነው። ስልጣኔ ግብረ ገብ እና ስነ መግባር ነው።
እነዚህን ሁሉ ስንመለከት ግን ባጭሩ ስልጣኔ ማለት ነግ በኔን በደምብ ማወቅ ነው። አካባቢዬን አላቆሽሽም ሌሎችን መንገደኞችን ውድጅያቸው ሳይሆን ንፁ አካባቢ ስለሚበጀኝ እኔ ካላቆሸሽኩኝ ሌሎችም ስለማያቆሽሹ ነው። እኔ መኪና የማሽከረክረው ሕግ አክብሬ ነው ሌሎች የመንገድ ተጠቃሚዎችን ስለምወዳቸው ሳይሆን ሁላችንም በትክክል ካሽከረከርን ሁላችንም በፍጥነንት እና በሰላም የምንፈልግበት ቦታ ለመድረስ ስለሚያመችን ነው። መንግስቴ ለደሆች እርዳታ እንዲያደርግ እወዳለሁ ሰላምን ለመጠበቅ እኔም ነገ ብወድቅ እርዳታ እንዳገኝ። ወዘተ። ይህ ነው ስልጣኔ ባጭሩ። ሮሜም አሜሪካም የትም ህዝብ ሰላምና ሀብት እያገኘ ሲሄድ ለራሱ ለግል ምቾቱ የሚሆን አሰራሮች ስነ ምግባሮች እየገባው በተግባር መዋል ይጀምራል።
ግን ይህ ስልጣኔ ከጥሩነት፤ በጎነት፤ ሰላም ወዳድነት እና ከፍቅር ጋር አይገናኝም። ነግ በኔ በጎነትም ፍቅርም አይደለም። «የሰለጠነ» ራስ ወዳድነት ነው። ማንም ከጊዜ በሚያመጣው ልምድ በኋላ የሚደርስበት ነው። ማንም ደግሞ ችግሮች ሲያጋጥሙት ካልተመቸው የሚተወው ነው። ሮሜ ለራሷ የሰለጠነች ነበር ለሌሎች ሀገሮች ግን የክፋት መዓበል ነበረች። ዛሬ አሜሪካም አውሮፓም ሌሎችም ለራሳቸው የሰለጠኑ ናቸው ግን ከጠረፍ ውጭ አይደሉም።
ስለዚህ ይህ ሀገር የሰለጠነ ነው የኔ ሀገር አይደለም ብለን የበታችነት ስሜት ሊኖረን ይግባል? በፍፁም! ስልጣኔ ማንንነት አይደለም። ስልጣኔ ይመጣል ይሄዳል በዓለም ታሪክ በተለያዩ ቦታዎች ተገንብቷል ፈርሷል። ስልጣኔ ከፍቅርና በጎነት አይገናኝም። የሰው ማንነት ግን በጎነት፤ ፍቅር፤ ሰላም ወዘተ ነው። ስለዚህ የሰው ልጅ እነዚህን የሚሽህ እስከሆነ መቼም የበታችነት ሊሰማው አይገባም! ከፍቅር ይልቅ «ብልጭልጭን» ሲያመልክ ነው ችግሩ የሚመጣው።
ይህን ተክትሎ እንደ ምዕራቡ ዓለም መሆን አለብን ብሎ ማሰቡም ተገቢ አይደለም። ለምን ብትሉ የምዕራባዊያን ርዕዮት ዓለም ከኢትዮጵያዊነት ትውፊትና ማንነት 180 ዲግሪ የተቃረነ ነው። የምዕራባዊ አስተሳሰብ የሰው ልጅ የዓለም ቁንጮ አድርጎ ያስቀምጠዋል። እግዚአብሔር የለም ወይንም ምንም ሚና አይጫወትም ይላል። ኢትዮጵያዊ ግን በትውፊታችን ፈጣሪ ነው በአምሳሉ የፈጠረን ብለን እናምናለን ሁሉ ነገራችንም ከዛ ይከተላል። ለዚህም ነው የጠ/ሚ አብይ አህመድ የይቅርታ፤ ፍቅር እና ሰላም መልዕክቶችን በደስታ እና ጉጉት የምንቀበለው። እንደዚህ አይነቱ መልዕክት የተም ምዕራብ ሀገር እንደ ህፃንነት ነበር የሚታየው። ስለ ልማት፤ ነፃነት፤ መብት ነው የምዕራብ ሀገር ውይይት። እግዚአብሔር የለምና።
ታሪክ ረዥም ነው። 500 ዓመት በፊት ቻይና ከሁሉም «የሰለጠነች» ነበር። 60 ዓመት በፊት ቻይና ወደ 40 ሚሊዮን ህዝቦቿን ገደለች ግማሽ ሀገሪቷ በርሃብ እየተሰቃየ ነበር። 2000 ዓመት በፊት ስሜን አውሮፓ በሮሜዎች ዘንድ የያልሰለጠና የአረመኔ ስፍራ ነበር። ዛሬ ደግሞ ከዓለም በሙሉ የሰለጠው ጎራ ይባላል። 60 ዓመት በፊት ኢትዮጵያ በዓለም ደረጃ ታላቅ ክብር ነበራት። ዛሬ እንደ ለማኝ ትታያለች። እኛ ኢትዮጵያዊያን ይህንን ብናስታውስ ጥሩ ይመስለኛል።
እውነት ስልጣኔ ፍቅር እና ሰላም ነው። የኛ የኢትዮጵያዊያን በዚህ ረገድ ከማንም ልናንስም ልንበልጥም እንችላለን የኛ ፋንታ ነው። ግን የሰው ልጅ በመሆናችን ከማንም አናንስም አንበልጥምም። የዝቅተኛ ስሜታችንም በምንም መለክያ ተገቢ አይደለም። እጅግ ጎጂም ነው። ሌላውን ምዕራባዊያንም ለመገልበጥ መሻህ ዋጋ የለውም ጎጂ ነው። ማንነታች ከፈጣሪያችን የተሰጠን ነውና ምንም የምናፍርበት ሊሆን አይገባም። እርግጥም ለሌሎች ምሳሌ ሆነን መገኘት ነው ያለብን ድሮ ሆነን እናውቃለን አሁንም የማንሆንበት ምክንያት የለም።
ሆኖም ግን ስደተኛው ምዕራብ ሀገሮችን ቢያደንቅም የሚተችባቸው ጉዳዮች ነበሩ። ለምሳሌ «ዘረኝነትን ያራምዳሉ» ይላል። በአዲስ ቅኝ ግዛት ታዳጊ ሀገራትን ያጠቃሉ ይዘርፋሉ። ኢትዮጵያ ለቅኝ ግዛት ስለማትመች እነ አሜሪካ ካዷት እና በደርግ አይነቱ አረመኔ መንግስት በማርክሲዝም እንድትገዛ አደረጉ። በተለያዩ ሀገራት ሕጋዊ የሆኑ መንግስታትን ይገለብጣሉ። ወዘተ። ኢትዮጵያዊ ስደተኛው ልሂቃኑም የምዕራብ ሀገሮችን በዚህ መልኩ ይከሱ ነበር።
በርካታ ስደተኞች እንደዚህ በማለት የምዕራብ ሀገሮችን ተችተው ሀገራቸው ኢትዮጵያ ችግሮች ቢኖሯትም ከነዚህ ሀገሮች በማንነት ደረጃ አታንስም ብለው ያምኑ ነበር። በዚህ ምክንያት የሀገር የማንነት የበታችንነት ስሜት (inferiority complex) ገና ብዙ አላደረባቸውም። በኢትዮጵያዊነቱ ያለው ኩራት ብዙ አልተቦረቦረም ነበር።
ግን ጊዜው ባለፈ ቁጥር ኢትዮጵያ «አልሻሻል» ስትል ባንጻሩ የምዕራብ ሀገሮች በብልጽግና እይናሩ እና አንዳንድ ልውጦች ሲያደርጉ የፕሮፓጋንዳ ስልታቸውም እየዳበረ ሲሄድ ኢትዮጵያዊ ስደተኛው በአሙሮው የምዕራቡን ዓለም እያበለጠ ሀገሩ ኢትዮጵያን እያሳነሰ ሄደ። ቀስ በቀስ የበታችነት ስሜት (inferiority complex) እያደረበት ሄደ። የህ የበታችነት ስሜት ወደ ሀገር ቤትም ገባ።
ወደ ምዕራብ ሀገር የተሰደደ ኢትዮጵያዊ ደህና ገቢ ማግኘት እና ሃብት ማከማቸት ቻለ። ስደተኛው ድሮ ቢገጥመውም ባይገጥመውም የሚያማርረው ዘረኝነቱ እየቀነሰ ሲሄድ አየ። ለነገሩ ዘረኝነቱ ድሮም ኑሮውን ከማሻሻል አልከለከለውም ነበር። አህን ግን ጭራሽ በጥቁርነቱ ስራ ከማጣት ማግኘት ጀመረ! ባሜሪካ ልጆቹ በጉብዝናቸው ብቻ ሳይሆን የጭቁን (ጥቅር) ዘር በመሆናቸው ስኮላርሺፕ ማግኘት ጀመሩ። የአሜሪካ ኑሮ ከድሮም ይበልጥ እየተመቸ ሄደ።
ይህ ስደተኛ ኑሮው «እየተሳካለት» በሄደ ቁጥር አሜሪካ በሱ አይን ይበልጥ እያማረች ሄደች። ፍትሐዊና መሐበራዊ ስነ ሥርዐቱን ከድሮም ይበልጥ ማደነቅ ጀመረ። ለሴቶች፤ ለልጆች፤ ለጥቁሮች ወዘተ ያለው «መብት» እና ጥንቃቄ ከኢትዮጵያ ጋር ሲያነጻጽረው ይገርመዋል። በፖለቲካ ደረጃ «ዴሞክራሲ» አምላኩ ሆነ «ሲኤንኤን» (CNN) መላዕክቱ ሆነ። በአንጻሩ ኢትዮጵያ በስደተኛው አይን እየቀነሰች እየወረደች ሄደች። አልሻሻል አለች እየባሰችም ሄደች። ስደተኛው ሀገሩን በጎበኛት ቁጥር ከአሜሪካ ጋር እያንጻጸረ ዘመዶቹን ያደነቁራል። በአሜሪካ እና ኢትዮጵያ ያለውን ልዩነት ለማሳየት ያህል ዘመዱን ከ«ሀገር ቤት» ለመውጣት በርካታ አስር ሺዎች ዶላር ይከፍላል።
ዛሬ በኛ በኢትዮጵያውያን የዝቅተኘት መንፈስ በደምብ አድሮብናል ማለት ከእውነት የራቀ አይመስለኝም። ግን ይህ መንፈስ እውነትን ነው የሚያንጸባርቀው? እውነት ዝቅተኛ ህብረተሰብ ነን? ወይም ሀገራችን ዝቅተኛ ነው? ይበልጥ ታላቅ የሆነው ጥያቄ ሙሉ ሰው ለመሆን ወይንም በዘመኑ ቋንቋ «መሻሻል» ከፈለግን እንደ ምዕራቡ ዓለም መሆን ይኖርብናል? ምናልባት ዘፈናችን ጭፈራችን ምግባችንን ለትዝታ ብለን ጠብቀን በሌላው በሙሉ እንደነሱ እንደ ምዕራባዊያን መሆን ይኖርብን ይሆን?
እዚህ ላይ በቀለም ትምሕርት ከምንማረው በሚዲያ ከምንሰማው ፕሮፓጋንዳና ተራ «እውቀት» ወጥተን እናስብ። በአዲሱ ቅን ግዛት የተገዛውን አእምሮአችንን ነፃ እናውጣው የብዥታ መነጽራችንን እንጣል። በመጀመርያ እስቲ ምንድነው «ስልጣኔ» ብለን እንጀምር። ጥያቄውን በምሳሌ ኃይል ለመመርመር ታዋቂውን የሮሜን ስልጣኔን እንመልከት።
በክርስቶስ ዘመን በርካታ አይሁዶች ወደ ሀገራቸውን ወርሮ የገዛው ሮሜ ይፈልሱ ነበር። አንድ አይሁድ ወደ ሮሜ ሲሄደ ዛሬ ኢትዮጵያዊ ከሀገሩ ወደ አሜሪካ እንደመሄድ እናመሳስለው። ሮሜ ሀብታም ነበረች። «ስደተኞችን» መጤዎችን ትቀበላለች ታስተናግዳለች ታበለጽጋለች። ውጣ ውረድ ቢኖረውም መጤዎች የሮሜ ዜጋ የመሆን እድል አላቸው። የሮሜ ዜግነት አንደ ይሁዳ ዜግነት በጎሳ በብሄር በደም የተወሰነ አይደለም ማንም የሮሜ ዜጋ መሆን ይችላል። የሮሜ ፍርድ ቤቶች በደምብ ይሰራሉ በተለይ ለሮሜ ዜጎች እውነተኛ ፍትሕ ይሰጣሉ። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ችግር ባጋጠመው ቁጥር አይሁዶች ሲገሱት ሲሉ የሮሜ ዜግነቱን ተጠቅሞ ፍርድ ይጠይቃል! በሮሜ ፍርድ ቤት ትክክለኛ የፍርድ ሂደት እንደሚጠብቀው ስለሚያውቅ ነው። የሮሜ መንግስታዊ አስተዳደር ፍፁም ባይሆንም ከሌሎች አንጻር «የሰለጠነ» ነበር። «ዴሞክራሲ» አይነት ከነ ምክር ቤት አለው። በሮሜ የማሕበራዊ ብረ ገብ አለ። የሴቶች «መብቶች» ከሌሎች ሀገሮች ከይሁዳ ይልቅ የተከበሩ ናቸው። በስነ ሥርዓት በኩልም ሮሜ የስለጠነች ናት። መንገዶቿ ንፁ ናቸው። መንገደኛ ለመንገደኛ ጎረቤት ለጎረቤት አገልጋይ ለባለጉዳይ ያለው ግንኙነት በጥቅም የተሳሰረ ሰላማዊና የተቀላጠፈ (efficient) ነው። የድሮ «ሮሜ» ስልጣኔ እንደዚህ ይመስላል።
ለዚህም ነው አይሁዶችም ሌሎችም ወደ ሮሜ የሚፈልሱት ሃብቱን እና ስልጣኔውን ፈልገው። ልክ እንደ ኢትዮጵያውያን ወደ አሜሪካ እንደምንፈልሰው «ህይወትን ለማሻሻል» ወደ በአድ ሀገር ይሄዱ ነበር። ግን ሮሜ የይሁዳ ቅኝ ገዥ ነበረች! አይሁዶች ወደ የሚገዛቸው ሀገር ነበር የሚሄዱት። ወደ ዓለምን በሙሉ በጉልበቷ የተቆጣጠረቹ ሮሜ ነበር ለተሻለ ኑሮ ብለው የሚሄዱት። ግን አይሁዶቹንም ሌሎች መጤዎችንም የሮሜ ስልጣኔ ክፋነቷን እንዳያዩ አድርጓቸዋል አሳውራቸው። ለነሱ ሮሜ የብልጽግና ሀገር እንጂ የክፋት ሀገር አልነበረትም። ሮሜ ሀገራቸው ይሁዳ የሌላት ነገሮች ሁሉ አላት። በዚህ ምክንያት በራሳቸው ባህልና ማንነት ዝቅጠኝነት ተሰማቸው እንደ ሮሜዎች መሆነ ፈለጉ ወደ ሮሜ ህብረተሰብ ተቀላቀሉ።
ይህ ምሳሌ ስለ «ስልጣኔን» ምን ያስተምረናል? ለብዙዎቻችን ስልጣኔ ሀብት ማለት ነው። ሀብት ካለ ሌሎች ጉድለቶች አያታዩንም። ስልጣኔ «ቴክኖሎጂ» ይመስለናል። የሮሜ የከተማው ቧምቧ እና ፍሳሽ ስራ አይሁዶችን ይገርማቸው ነበር። ስልጣኔ ቅልጥፍና (efficiency) ይመስለናል። የሮሜ የመነግስት መዋቅሮች በተለይ ጦር ሰራዊቱ ግቡን በቀላሉ ያስፈጽም ነበር። ስልጣኔ ፍትሕ ነው። ስልጣኔ ግብረ ገብ እና ስነ መግባር ነው።
እነዚህን ሁሉ ስንመለከት ግን ባጭሩ ስልጣኔ ማለት ነግ በኔን በደምብ ማወቅ ነው። አካባቢዬን አላቆሽሽም ሌሎችን መንገደኞችን ውድጅያቸው ሳይሆን ንፁ አካባቢ ስለሚበጀኝ እኔ ካላቆሸሽኩኝ ሌሎችም ስለማያቆሽሹ ነው። እኔ መኪና የማሽከረክረው ሕግ አክብሬ ነው ሌሎች የመንገድ ተጠቃሚዎችን ስለምወዳቸው ሳይሆን ሁላችንም በትክክል ካሽከረከርን ሁላችንም በፍጥነንት እና በሰላም የምንፈልግበት ቦታ ለመድረስ ስለሚያመችን ነው። መንግስቴ ለደሆች እርዳታ እንዲያደርግ እወዳለሁ ሰላምን ለመጠበቅ እኔም ነገ ብወድቅ እርዳታ እንዳገኝ። ወዘተ። ይህ ነው ስልጣኔ ባጭሩ። ሮሜም አሜሪካም የትም ህዝብ ሰላምና ሀብት እያገኘ ሲሄድ ለራሱ ለግል ምቾቱ የሚሆን አሰራሮች ስነ ምግባሮች እየገባው በተግባር መዋል ይጀምራል።
ግን ይህ ስልጣኔ ከጥሩነት፤ በጎነት፤ ሰላም ወዳድነት እና ከፍቅር ጋር አይገናኝም። ነግ በኔ በጎነትም ፍቅርም አይደለም። «የሰለጠነ» ራስ ወዳድነት ነው። ማንም ከጊዜ በሚያመጣው ልምድ በኋላ የሚደርስበት ነው። ማንም ደግሞ ችግሮች ሲያጋጥሙት ካልተመቸው የሚተወው ነው። ሮሜ ለራሷ የሰለጠነች ነበር ለሌሎች ሀገሮች ግን የክፋት መዓበል ነበረች። ዛሬ አሜሪካም አውሮፓም ሌሎችም ለራሳቸው የሰለጠኑ ናቸው ግን ከጠረፍ ውጭ አይደሉም።
ስለዚህ ይህ ሀገር የሰለጠነ ነው የኔ ሀገር አይደለም ብለን የበታችነት ስሜት ሊኖረን ይግባል? በፍፁም! ስልጣኔ ማንንነት አይደለም። ስልጣኔ ይመጣል ይሄዳል በዓለም ታሪክ በተለያዩ ቦታዎች ተገንብቷል ፈርሷል። ስልጣኔ ከፍቅርና በጎነት አይገናኝም። የሰው ማንነት ግን በጎነት፤ ፍቅር፤ ሰላም ወዘተ ነው። ስለዚህ የሰው ልጅ እነዚህን የሚሽህ እስከሆነ መቼም የበታችነት ሊሰማው አይገባም! ከፍቅር ይልቅ «ብልጭልጭን» ሲያመልክ ነው ችግሩ የሚመጣው።
ይህን ተክትሎ እንደ ምዕራቡ ዓለም መሆን አለብን ብሎ ማሰቡም ተገቢ አይደለም። ለምን ብትሉ የምዕራባዊያን ርዕዮት ዓለም ከኢትዮጵያዊነት ትውፊትና ማንነት 180 ዲግሪ የተቃረነ ነው። የምዕራባዊ አስተሳሰብ የሰው ልጅ የዓለም ቁንጮ አድርጎ ያስቀምጠዋል። እግዚአብሔር የለም ወይንም ምንም ሚና አይጫወትም ይላል። ኢትዮጵያዊ ግን በትውፊታችን ፈጣሪ ነው በአምሳሉ የፈጠረን ብለን እናምናለን ሁሉ ነገራችንም ከዛ ይከተላል። ለዚህም ነው የጠ/ሚ አብይ አህመድ የይቅርታ፤ ፍቅር እና ሰላም መልዕክቶችን በደስታ እና ጉጉት የምንቀበለው። እንደዚህ አይነቱ መልዕክት የተም ምዕራብ ሀገር እንደ ህፃንነት ነበር የሚታየው። ስለ ልማት፤ ነፃነት፤ መብት ነው የምዕራብ ሀገር ውይይት። እግዚአብሔር የለምና።
ታሪክ ረዥም ነው። 500 ዓመት በፊት ቻይና ከሁሉም «የሰለጠነች» ነበር። 60 ዓመት በፊት ቻይና ወደ 40 ሚሊዮን ህዝቦቿን ገደለች ግማሽ ሀገሪቷ በርሃብ እየተሰቃየ ነበር። 2000 ዓመት በፊት ስሜን አውሮፓ በሮሜዎች ዘንድ የያልሰለጠና የአረመኔ ስፍራ ነበር። ዛሬ ደግሞ ከዓለም በሙሉ የሰለጠው ጎራ ይባላል። 60 ዓመት በፊት ኢትዮጵያ በዓለም ደረጃ ታላቅ ክብር ነበራት። ዛሬ እንደ ለማኝ ትታያለች። እኛ ኢትዮጵያዊያን ይህንን ብናስታውስ ጥሩ ይመስለኛል።
እውነት ስልጣኔ ፍቅር እና ሰላም ነው። የኛ የኢትዮጵያዊያን በዚህ ረገድ ከማንም ልናንስም ልንበልጥም እንችላለን የኛ ፋንታ ነው። ግን የሰው ልጅ በመሆናችን ከማንም አናንስም አንበልጥምም። የዝቅተኛ ስሜታችንም በምንም መለክያ ተገቢ አይደለም። እጅግ ጎጂም ነው። ሌላውን ምዕራባዊያንም ለመገልበጥ መሻህ ዋጋ የለውም ጎጂ ነው። ማንነታች ከፈጣሪያችን የተሰጠን ነውና ምንም የምናፍርበት ሊሆን አይገባም። እርግጥም ለሌሎች ምሳሌ ሆነን መገኘት ነው ያለብን ድሮ ሆነን እናውቃለን አሁንም የማንሆንበት ምክንያት የለም።
Wednesday, 27 June 2018
ችኮላ
ጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ ለውጦችን በአስገራሚ ፍጥነት ነው እያመጡ ያሉት። መቼም አንዳችን በዚህ ፍጥነት ለውጦች ይመጣሉ ብለን ገምተን ነበር የሚል ካለ ይገርመኛል። እርገጥ ኤርሚያስ ለገሰ አብይ አህመድን ስኬታማ ለመሆን ፍጠን ብሏቸው ነበር ግን እርግጠኛ ነኝ እሱም እንደዚህ ይፈጥናሉ ብሎ አልጠበቀም። አንዳችንም አልጠበቅነውም ብለን በትህትና ብናምን ጥሩ ይመስለኛል!
ፈጥኗል ግን ከመጠን በላይ ፈጥኖ ይሆን? ጥሩ ጥያቄ ነው መልሱንም አላውቅም። ከሁላችንም በላይ ከፖለቲካ ጦርነት ውስጥ ያሉት አብይ እና ቡድኑ ነው ያሚያውቁት። ከመጠን በልይ መፍጠን እንደሚቻል ግን ይታወቃል። «ዴሞክራሲ ይስፈን»፤ «ፍትህ ይኑር»፤ «ያለፉት የፖለቲካ እና ሰብዓዊ ወንጀሎች ይጣሩ»፤ «የፖለቲካ ወንጀለኞች ይፈረድባቸው»፤ «ህገ መንግስቱ ይቀየር»፤ «ሀገ መንግስቱ በትክክሉ ይፈጸም» ወዘተ መፈክሮች ምአት ናቸው። የምንፈልገውን በሙሉ አሁኑኑ ይደረግልን የሚሉ አሉ።
ግን የ27፤ የ40፤ የ50፤ የ100 ወዘተ ዓመታት ችግሮች በአንዴ አይፈቱም፤ ይህንን ሁላችንም እናውቃለን። ከብዙ ሰዎች ይህን ጥሩ ምሳሌ ሰምችአለሁ፤ ሀገራችን እንደ ማንኛውም የከባድ በሽታ ህመምተኛ ለህልውናው የሚያሰጋው እና በውቅቱ መታከም የሚችሉ ቁስሎችን ነው በጀመርያ መታከም ያለበት። እነዚህ ህመሞች ሲድኑ ወደሚቀጥሉት መሄድ ነው። የህቅምናውን ቀደም ተከተል በደምብ የሚአቁት ከህመምተኛው ቅርብ ያሉት የሚያክሙት ሐኪሞች ናቸው። ግን እኛ ኢትዮጵያዊዎች ለሐኪሞቹ ተሽሎናል አልተሻለንም ብለን ምልክት መስጠት አለብን። ስለዚህ መፈክሮቹ ጥያቄዎቹ መቀጠል አለባቸው። ግን የነ ጠ/ሚ አብይንም አቅም እና የፖለቲካው ጠቅላላ ሁኔታ መረዳት አለብን። ቢያንስ ለራሳችን ብለን የማይሆን ነገር መጠበቅ የለብንም።
እርግጥ መጠበቅ ከባድ ነው ትእግስት ከባድ ነው። አንድ የሚያቀለው ነገር ግን ስራ ነው። ለለውጥ እንስራ! ጠ/ሚ አብይ ጋብዞናል። ከሰፈራችን፤ ከመስርያቤታችን፤ ከሃይማኖት ስፍራችን ወዘተ ሰላምን እናምጣ። ፍቅር እናምጣ። ሙስናን እና ተመሳሳይ ጎጂ ባህሎችን እንታገል። ከጎረቤታችን ጋር እንፋቀር (http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2016/09/blog-post_14.html)። ድሆችን እንርዳ። ብዙ ብዙ ስራ አለ። ጥያቄ ማብዛት ስራ አይደለም፤ ያንንማ ሁላችንም በቀላሉ እናደርገዋለን። እነዚህ የፍቅር ስራዎች ናቸው ከባድ። እነዚህን ስራዎች ብንሰራ ጥያቄዎቻችን እንዲመለሱ ያፈጥናሉ ትእግስትም ይኖረናል!
ፈጥኗል ግን ከመጠን በላይ ፈጥኖ ይሆን? ጥሩ ጥያቄ ነው መልሱንም አላውቅም። ከሁላችንም በላይ ከፖለቲካ ጦርነት ውስጥ ያሉት አብይ እና ቡድኑ ነው ያሚያውቁት። ከመጠን በልይ መፍጠን እንደሚቻል ግን ይታወቃል። «ዴሞክራሲ ይስፈን»፤ «ፍትህ ይኑር»፤ «ያለፉት የፖለቲካ እና ሰብዓዊ ወንጀሎች ይጣሩ»፤ «የፖለቲካ ወንጀለኞች ይፈረድባቸው»፤ «ህገ መንግስቱ ይቀየር»፤ «ሀገ መንግስቱ በትክክሉ ይፈጸም» ወዘተ መፈክሮች ምአት ናቸው። የምንፈልገውን በሙሉ አሁኑኑ ይደረግልን የሚሉ አሉ።
ግን የ27፤ የ40፤ የ50፤ የ100 ወዘተ ዓመታት ችግሮች በአንዴ አይፈቱም፤ ይህንን ሁላችንም እናውቃለን። ከብዙ ሰዎች ይህን ጥሩ ምሳሌ ሰምችአለሁ፤ ሀገራችን እንደ ማንኛውም የከባድ በሽታ ህመምተኛ ለህልውናው የሚያሰጋው እና በውቅቱ መታከም የሚችሉ ቁስሎችን ነው በጀመርያ መታከም ያለበት። እነዚህ ህመሞች ሲድኑ ወደሚቀጥሉት መሄድ ነው። የህቅምናውን ቀደም ተከተል በደምብ የሚአቁት ከህመምተኛው ቅርብ ያሉት የሚያክሙት ሐኪሞች ናቸው። ግን እኛ ኢትዮጵያዊዎች ለሐኪሞቹ ተሽሎናል አልተሻለንም ብለን ምልክት መስጠት አለብን። ስለዚህ መፈክሮቹ ጥያቄዎቹ መቀጠል አለባቸው። ግን የነ ጠ/ሚ አብይንም አቅም እና የፖለቲካው ጠቅላላ ሁኔታ መረዳት አለብን። ቢያንስ ለራሳችን ብለን የማይሆን ነገር መጠበቅ የለብንም።
እርግጥ መጠበቅ ከባድ ነው ትእግስት ከባድ ነው። አንድ የሚያቀለው ነገር ግን ስራ ነው። ለለውጥ እንስራ! ጠ/ሚ አብይ ጋብዞናል። ከሰፈራችን፤ ከመስርያቤታችን፤ ከሃይማኖት ስፍራችን ወዘተ ሰላምን እናምጣ። ፍቅር እናምጣ። ሙስናን እና ተመሳሳይ ጎጂ ባህሎችን እንታገል። ከጎረቤታችን ጋር እንፋቀር (http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2016/09/blog-post_14.html)። ድሆችን እንርዳ። ብዙ ብዙ ስራ አለ። ጥያቄ ማብዛት ስራ አይደለም፤ ያንንማ ሁላችንም በቀላሉ እናደርገዋለን። እነዚህ የፍቅር ስራዎች ናቸው ከባድ። እነዚህን ስራዎች ብንሰራ ጥያቄዎቻችን እንዲመለሱ ያፈጥናሉ ትእግስትም ይኖረናል!
Friday, 22 June 2018
ኤርትራ
የ1991 ኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ስለ ባድሜ ወይንም ድንበር አልነበረም። ጉዳዩ የስልጣን የበላይነት ነበር ተፎካካሪዎቹ ሻዕብያ እና ህወሓት ነበሩ።
ደርግ ከስልጣን ሲወርድ ጀምሮ ለሰባት ዓመት ህወሓት እና ሻዕብያ ከሞላ ጎደል አብረው ኢትዮጵያን ገዝተዋታል። አዎን የኢትዮጵያ መንግስት በህወሓት ነበር የሚመራው ግን በህውሓት ፈቃድ እና ድጋፍ ሻዕብያ እንደ «ሁለተኛ መንግስት» ይንቀሳቀስ ነበር። የኤርትራ መንግስት አካላት ከነ ደህንነት ክፍሉ ኢትዮጵያ ውስጥ በይፋም በስውርም ይሰራ ነበር ስልጣንም ነበረው። የኤርትራ መንግስት እና ባለ ሃብቶች በኢትዮጵያ መንግስት ፖሊሲዎች ታላቅ ሚና ይጫወቱ ነበር። ኤርትራ ከብሄራዊ ባንክ ገንዘብ ታገኛ ነበር። ኤርትራዊ ባለ ሃብቶች በምስና የባንክ ብድር፤ የምንግስት ኮንትራት፤ የቀረጥ ነጻ መብት ወዘተ ያገኙ ነበር። ኤርትራዊያን ቡና አለቀረጥ ከኢትዮጵያ ገዝተው ወደ ውጭ ሀገር ይሸጡ ነበር። ወዘተ፤ ምሳሌዎቹ ማስረጃዎቹ በርካታ ናቸው ተመዝግበዋል በአዲሱ የመንግስት ግልጽነት አካሄድ ደግሞ ይበልጥ ወደ ይፋ ይወጣሉ። ድምዳሜው ግን ከ1983 እስከ 1991 የኤርትራ መንግስት እና ኤርትራዊያን ባለ ሃብቶች ኢትዮጵያ ውስጥ አግባብ ያልሆነ ተጽኖ እና ስልጣን ነበራቸው።
ግን ይህ ሁኔታ ሊቀጥል አይችልም ነበር። ምክንያቱም የሀገር ገዥ የነበረው ህወሓት ኢትዮጵያን ሙሉ በሙሉ መቆጣጠር ይፈልግ ነበር። የሀገር መንግስት ሆኖ ልምንድነው ሌላው ሁለተኛ ምነግስት የሚያስተናግደው? ህወሓት የኢትዮጵያን ስልጣንን እና ከኢትዮጵያ የሚገኘውን ጥቅም ለራሱ ይፈልግ ነበር። ኢህአዴግ ውስጥ ያሉት አጋር ፓርቲዎችም እንዲሁም ኢትዮጵያ ከኤርትራ ተጽኖ ነጻ መሆን አለበት እራሳችን ሙሉ በሙሉ መግዛት አለብን የሚል አቋም ነበራቸው። በዛው መጠን ሻዕብያ በኢትዮጵያ ያለውን ጥቅም እና ስልጣን መልቀቅ አልፈለገም። በዚህ ጉዳይ መደራደር አልተፈለገም ተፎካካሪዎቹ በጡንቻ መጋጠም ወሰኑ። በአጭሩ ይህ ነበር የህወሓት እና የሻዕብያ ግጭት እና የጦርነቱ ምንጭ።
ከጦርነቱ በኋላ በህወሓት እና ኢህአዴግ ክፍፍል ምክንያት ወደ «ጦርነትም ሰላምም የለም» ("no war no peace") ዘመን ገባን። ለምን እስከ መጨረሻ ሄደን አሰብን አልወሰድንም ሻዕብያን አላፈርሰንም የሚሉ ነበሩ። ስለዚህ የህወሓት የፖለቲካ ስምምነት ያንን ባናደርግም ኤርትራን በማግለል ሻዕብያን እንጎዳለን ሆነ። ሻዕብያ በኢትዮጵያ አሳቦ የሀገራቸውን ኤኮኖሚ እና የህዝብ ሞራል ይገላል እና ቀስ ብሎ ይወድቃል ነበር በኢትዮጵያ መንግስት የነበረው አስተሳሰብ። ከዛ በኋላ ከኢትዮጵያ ጋር በተሻለ መልኩ ለመደራደር ዝግጁ የሆነ መንግስት ኤርትራ ውስጥ ስልጣን ይይዝ እና ከነሱ ጋር እንደራደራለን ነበር የኢህአዴግ አቋም።
ስለዚህ ባጭሩ የ«ጦርነትም ሰላምም የለም» ፖሊሲ ሁለት አላማ ነበረው፤ 1) ሻዕብያን ከስልጣን ማውረድ ለኢትዮጵያ ወይንም ለህወሓት የሚመች መንግስት እንዲመጣ እና 2) ኤርትራ እንደ ሀገር ኃይሏ ከኢትዮያ አንጻር እንዲመነምን እና በዚህ ምክንያት ለኢትዮጵያ አመቺ የሆነ የድርድር ሁኔታ እንዲፈጠር።
ዛሬ አንደኛው ግብ አልተመታም ግን ሁለተኛው ተመቷል ወይንም ከዚህ በላይ ሊመታ አይችልም። ማለተም ካሁን ወድያ ኤርትራን ለማድከም ተብሎ ይህ ፖሊሲ ቢቀጥል ጉዳቱ ከጥቅሙ ይበልጣል። ሻዕብያ እና ኤርትራ የሚማሩት ትምሕርትሮች ከነበሩ ተምረውታል። የኤኮኖሚ ችግር በቂ አይተውታል። ሻዕብያ መሪው ኢሳያስ አፈወርቂ ከህውየት እስኪለዩ መግዛት መቀጠሉ ግልጽ ሆኗል። ከዛ በኋላ ደግሞ ትርምስ የሚመጣ ይመስላል የሻዕብያን የመገንጠል ጦርነትን የማያስታውስ ጭቆና ብቻ የሚያስታውስ አዲስ ትውልድ ወደ ፊት እየመጣ ሲሄድ። ስለዚህ ነው የአብይ አህመድ መንግስት ይበቃል ወደ ሰላም እና ድርድር እንግባ ያለው። ትርምስ ሳይመጣ ጠላት ሀገሮች እጃቸውን አለ ቁጥጥር ኤርትራ ውስጥ መክተት ከሚጀምሩ በፊት ካሁኑኑ የቀረውን የወንድማማቾች ስሜትን ተጠቅመን እንደራደር ነው።
ይህ ጥሩ አካሄድ ይመስለኛል። እንዳልኩት የ «ጦርነትም ሰላምም የለም» ፖሊሲ በቂ ሰርቷል ምቀጠሉ ለኢትዮጵያ አይጠቅማትም። ከዚህ አልፎ ተርፎ የኤርትራ ችግር ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ የቅርብ የፖለቲካ ለውጦች የሁለቱን ሀገራት የኃይል ሚዛን እጅግ ወደ ኢትዮጵያ አመዝኖታል። በህወሓት ዘመን የኢትዮጵያ ህዝብ የሚጠላው ከፋፋይ መንግስት ስለነበር ሀገሪቷን የተከፋፈለች ከሚገባት ደካማ ኃይል እንዲኖራት አድርጓል። በዛን ጊዜ ኢትዮጵያ ከኤርትራ ጋር ድርድር ብትገጥም ውጤቱ ደካማ ነበር የሚሆነው። አሁን ግን ህዝቡ በሙሉ አንድ ስለሆነ እነ አብይ አህመንድ ወደ ድርድር ሲገቡ ያንን ሁሉ ኃይል ይዘው ስለሚገቡ ታላቅ ድል ማድረስ ይችላሉ። እንደ ድሮ የሻዕብያን ብልጠት መፍራት የለም። እንደ ድሮ ኤርትራ እና ኢትዮጵያ እንደ እኩለኛማቾች አደሉም። ኢትዮጵያ ታላቅ፤ ግዙፍ እና ባለ ኃይል ናት ኤርትራ እንደሚገባት የኢትዮጵያ አንድ አስረኛ ናት። ይህ ለድርድር ጥሩ ሜዳ ነው። በእውነታ የተመሰረተ ትክክል እና ዘላቂ ስምምነት እንዲኖር የሚያደርግ ሜዳ ነው።
ባጭሩ የጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ የ«ጦርነትም ሰላምም የለም» የሚለውን ፖሊሲ ያቆመው ምክንያት ጥቅሙ ስላለቀ እና ለኢትዮጵያ አሁኑኑ ከኤርትራ ጋር ድርድር መግባት አዋጪ ስለሆነ ነው። እዚህ ላይ ማለት የምፈልገው አንድ ነገር አለ። ለኔ ኤርትራ እና ኢትዮጵያ አንድ ናቸው። የኤርትራ ህዝብ ኢትዮጵያዊ አይደለሁም ለማለት ሙሉ መብት አሉ በዚህ መብት አምናለሁ። ግን ለኔ ኤርትራኖች ሀገሬዎች ወንድሞቼ ናቸው። ከዛም አልፎ ከኢትዮጵያ የተገነጠሉት በኔ በኛ ጥፋት እንጂ በነሱ ክፋት አይደለም ብዬ ነው የማምነው። ስለዚህ ለኔ ይህ ድርድር ስለኤኮኖሚ ብቻ ሳይሆን ስለ ህዝባዊ ግንኙነተና ትሥስር ነው። የመለያየታችን ቁስሎች፤ ትዕቢቶች፤ ውሸቶች፤ ወዘተ የማስወገድ መጀመርያ ነው። እነ አብይ አህመድ ይህንን ለማድረግ እግዚአብሔር ይርዳቸው ይድራን!
ደርግ ከስልጣን ሲወርድ ጀምሮ ለሰባት ዓመት ህወሓት እና ሻዕብያ ከሞላ ጎደል አብረው ኢትዮጵያን ገዝተዋታል። አዎን የኢትዮጵያ መንግስት በህወሓት ነበር የሚመራው ግን በህውሓት ፈቃድ እና ድጋፍ ሻዕብያ እንደ «ሁለተኛ መንግስት» ይንቀሳቀስ ነበር። የኤርትራ መንግስት አካላት ከነ ደህንነት ክፍሉ ኢትዮጵያ ውስጥ በይፋም በስውርም ይሰራ ነበር ስልጣንም ነበረው። የኤርትራ መንግስት እና ባለ ሃብቶች በኢትዮጵያ መንግስት ፖሊሲዎች ታላቅ ሚና ይጫወቱ ነበር። ኤርትራ ከብሄራዊ ባንክ ገንዘብ ታገኛ ነበር። ኤርትራዊ ባለ ሃብቶች በምስና የባንክ ብድር፤ የምንግስት ኮንትራት፤ የቀረጥ ነጻ መብት ወዘተ ያገኙ ነበር። ኤርትራዊያን ቡና አለቀረጥ ከኢትዮጵያ ገዝተው ወደ ውጭ ሀገር ይሸጡ ነበር። ወዘተ፤ ምሳሌዎቹ ማስረጃዎቹ በርካታ ናቸው ተመዝግበዋል በአዲሱ የመንግስት ግልጽነት አካሄድ ደግሞ ይበልጥ ወደ ይፋ ይወጣሉ። ድምዳሜው ግን ከ1983 እስከ 1991 የኤርትራ መንግስት እና ኤርትራዊያን ባለ ሃብቶች ኢትዮጵያ ውስጥ አግባብ ያልሆነ ተጽኖ እና ስልጣን ነበራቸው።
ግን ይህ ሁኔታ ሊቀጥል አይችልም ነበር። ምክንያቱም የሀገር ገዥ የነበረው ህወሓት ኢትዮጵያን ሙሉ በሙሉ መቆጣጠር ይፈልግ ነበር። የሀገር መንግስት ሆኖ ልምንድነው ሌላው ሁለተኛ ምነግስት የሚያስተናግደው? ህወሓት የኢትዮጵያን ስልጣንን እና ከኢትዮጵያ የሚገኘውን ጥቅም ለራሱ ይፈልግ ነበር። ኢህአዴግ ውስጥ ያሉት አጋር ፓርቲዎችም እንዲሁም ኢትዮጵያ ከኤርትራ ተጽኖ ነጻ መሆን አለበት እራሳችን ሙሉ በሙሉ መግዛት አለብን የሚል አቋም ነበራቸው። በዛው መጠን ሻዕብያ በኢትዮጵያ ያለውን ጥቅም እና ስልጣን መልቀቅ አልፈለገም። በዚህ ጉዳይ መደራደር አልተፈለገም ተፎካካሪዎቹ በጡንቻ መጋጠም ወሰኑ። በአጭሩ ይህ ነበር የህወሓት እና የሻዕብያ ግጭት እና የጦርነቱ ምንጭ።
ከጦርነቱ በኋላ በህወሓት እና ኢህአዴግ ክፍፍል ምክንያት ወደ «ጦርነትም ሰላምም የለም» ("no war no peace") ዘመን ገባን። ለምን እስከ መጨረሻ ሄደን አሰብን አልወሰድንም ሻዕብያን አላፈርሰንም የሚሉ ነበሩ። ስለዚህ የህወሓት የፖለቲካ ስምምነት ያንን ባናደርግም ኤርትራን በማግለል ሻዕብያን እንጎዳለን ሆነ። ሻዕብያ በኢትዮጵያ አሳቦ የሀገራቸውን ኤኮኖሚ እና የህዝብ ሞራል ይገላል እና ቀስ ብሎ ይወድቃል ነበር በኢትዮጵያ መንግስት የነበረው አስተሳሰብ። ከዛ በኋላ ከኢትዮጵያ ጋር በተሻለ መልኩ ለመደራደር ዝግጁ የሆነ መንግስት ኤርትራ ውስጥ ስልጣን ይይዝ እና ከነሱ ጋር እንደራደራለን ነበር የኢህአዴግ አቋም።
ስለዚህ ባጭሩ የ«ጦርነትም ሰላምም የለም» ፖሊሲ ሁለት አላማ ነበረው፤ 1) ሻዕብያን ከስልጣን ማውረድ ለኢትዮጵያ ወይንም ለህወሓት የሚመች መንግስት እንዲመጣ እና 2) ኤርትራ እንደ ሀገር ኃይሏ ከኢትዮያ አንጻር እንዲመነምን እና በዚህ ምክንያት ለኢትዮጵያ አመቺ የሆነ የድርድር ሁኔታ እንዲፈጠር።
ዛሬ አንደኛው ግብ አልተመታም ግን ሁለተኛው ተመቷል ወይንም ከዚህ በላይ ሊመታ አይችልም። ማለተም ካሁን ወድያ ኤርትራን ለማድከም ተብሎ ይህ ፖሊሲ ቢቀጥል ጉዳቱ ከጥቅሙ ይበልጣል። ሻዕብያ እና ኤርትራ የሚማሩት ትምሕርትሮች ከነበሩ ተምረውታል። የኤኮኖሚ ችግር በቂ አይተውታል። ሻዕብያ መሪው ኢሳያስ አፈወርቂ ከህውየት እስኪለዩ መግዛት መቀጠሉ ግልጽ ሆኗል። ከዛ በኋላ ደግሞ ትርምስ የሚመጣ ይመስላል የሻዕብያን የመገንጠል ጦርነትን የማያስታውስ ጭቆና ብቻ የሚያስታውስ አዲስ ትውልድ ወደ ፊት እየመጣ ሲሄድ። ስለዚህ ነው የአብይ አህመድ መንግስት ይበቃል ወደ ሰላም እና ድርድር እንግባ ያለው። ትርምስ ሳይመጣ ጠላት ሀገሮች እጃቸውን አለ ቁጥጥር ኤርትራ ውስጥ መክተት ከሚጀምሩ በፊት ካሁኑኑ የቀረውን የወንድማማቾች ስሜትን ተጠቅመን እንደራደር ነው።
ይህ ጥሩ አካሄድ ይመስለኛል። እንዳልኩት የ «ጦርነትም ሰላምም የለም» ፖሊሲ በቂ ሰርቷል ምቀጠሉ ለኢትዮጵያ አይጠቅማትም። ከዚህ አልፎ ተርፎ የኤርትራ ችግር ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ የቅርብ የፖለቲካ ለውጦች የሁለቱን ሀገራት የኃይል ሚዛን እጅግ ወደ ኢትዮጵያ አመዝኖታል። በህወሓት ዘመን የኢትዮጵያ ህዝብ የሚጠላው ከፋፋይ መንግስት ስለነበር ሀገሪቷን የተከፋፈለች ከሚገባት ደካማ ኃይል እንዲኖራት አድርጓል። በዛን ጊዜ ኢትዮጵያ ከኤርትራ ጋር ድርድር ብትገጥም ውጤቱ ደካማ ነበር የሚሆነው። አሁን ግን ህዝቡ በሙሉ አንድ ስለሆነ እነ አብይ አህመንድ ወደ ድርድር ሲገቡ ያንን ሁሉ ኃይል ይዘው ስለሚገቡ ታላቅ ድል ማድረስ ይችላሉ። እንደ ድሮ የሻዕብያን ብልጠት መፍራት የለም። እንደ ድሮ ኤርትራ እና ኢትዮጵያ እንደ እኩለኛማቾች አደሉም። ኢትዮጵያ ታላቅ፤ ግዙፍ እና ባለ ኃይል ናት ኤርትራ እንደሚገባት የኢትዮጵያ አንድ አስረኛ ናት። ይህ ለድርድር ጥሩ ሜዳ ነው። በእውነታ የተመሰረተ ትክክል እና ዘላቂ ስምምነት እንዲኖር የሚያደርግ ሜዳ ነው።
ባጭሩ የጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ የ«ጦርነትም ሰላምም የለም» የሚለውን ፖሊሲ ያቆመው ምክንያት ጥቅሙ ስላለቀ እና ለኢትዮጵያ አሁኑኑ ከኤርትራ ጋር ድርድር መግባት አዋጪ ስለሆነ ነው። እዚህ ላይ ማለት የምፈልገው አንድ ነገር አለ። ለኔ ኤርትራ እና ኢትዮጵያ አንድ ናቸው። የኤርትራ ህዝብ ኢትዮጵያዊ አይደለሁም ለማለት ሙሉ መብት አሉ በዚህ መብት አምናለሁ። ግን ለኔ ኤርትራኖች ሀገሬዎች ወንድሞቼ ናቸው። ከዛም አልፎ ከኢትዮጵያ የተገነጠሉት በኔ በኛ ጥፋት እንጂ በነሱ ክፋት አይደለም ብዬ ነው የማምነው። ስለዚህ ለኔ ይህ ድርድር ስለኤኮኖሚ ብቻ ሳይሆን ስለ ህዝባዊ ግንኙነተና ትሥስር ነው። የመለያየታችን ቁስሎች፤ ትዕቢቶች፤ ውሸቶች፤ ወዘተ የማስወገድ መጀመርያ ነው። እነ አብይ አህመድ ይህንን ለማድረግ እግዚአብሔር ይርዳቸው ይድራን!
Subscribe to:
Posts (Atom)