Friday 8 June 2018

ሃይማኖታዊዋ ትግራይ እንዴት በፀረ ሃይማኖት ፓርቲ ትመራለች?

የትግዳይ ህዝብ ረዥም ታሪክ እንዳለው ወግ እና ትውፊቱን እንደሚወድ እንደሚአከብር ይታወቃል። ለምሳሌ ሃይማኖቶቻቸውን የሚአስቀድሙ እንደሚአጠብቁ ይነገራል ይታያል። በክብረ በአልም በዘውትር ጊዜም አክሱምን የጎበኘ ክርስቲያን ይህንን ሊመሰክር ይችላል። የህዝቡ አምልኮት ልዩ እና ጠንካራ መሆኑ ይታያል።

ታድያ እንደዚህ አይነቱ ህዝብ እንዴትቢሆን ነው በ ፀረ ሃይማኖት የሆነ የፖለቲካ ኃይል የሚገዛው እንዴት ይህን ኃይል ለዓመታት ከሌሎች ለይቶ ይደግፋል የሚለው ጥያቄ እንዴት ነው የማይጠየቀው። ፀረ ሃይማኖት ስል ከህወሓት አባላት መካከላማኞች የሉም ማለቴ ሳይሆን ግን የፓርቲው ርዕዮት ዓለም ፀረ ሃይማኖት መሆኑ ግልጽ ነው። አጀማመሩም እንደዚሁ ነው ዛሬም እንደዚህ ነው። አንድቀላል ምሳሌ ስለ ጎሰኝነት ያላቸው አመለካከት ቀትታ ከማርክሲዝም የመጣ ነው። የ «ጨቋኝ ተጨቋኝ» አመለካከታቸውም እንደዚሁም። እነዚህ «ከ ሃይማኖት ነፃ» የሆኑ አመለካከቶች ሳይሆኑ ፀረሃይማኖት ፀረ ትውፊት ናቸው።

እርግጥ ሃይማኖታዊ ትውፊት አክባሪ የሆነ ህብረተሰብ እንዴት በፀረ ሃይማኖት ወይም ሃይማ ኦት የለሽ ገዥ መደብ ወይም ልሂቃን ይመራል የሚለው ጥያቄ ትግራይን ብቻ ሳይሆን መላ ኢትዮጵያን ይመለከታል። ከኦርቶዶክስ ክርስቲያን አንፃር መልሱ ቀላል ነው፤ የህዝቡ የኛ ሐጢአት ነው ምክንያቱ። በጾቪዬት እስር ቤት የተሰቃዩት አለክሻንደር ሶልዠኒትሲን ከእስር ቤት ሆነው የጻፉትን እንደገና ልጥቀስ
ከእስርቤታችን አልጋ የሆነው የበሰበሰው ገለባ ላይ ጋደም ብዬ ነው ለመጀመርያ ከውስጤ የበጎ መንፈስ የተሰማኝ። ቀስ በቀስ መረዳት የጀመርኩት ይህ ነው፤ ጥሩና ክፉን የሚለየው መስመር በሀገሮች፤ መደቦች፤ የፖለቲካ ፓርቲዎችም መካከል አይደለም የሚያልፈው፤ ይህ መስመር የሚያልፈው በያንዳንዱ የሰው ልብ መኻል ነው። መስመሩእድሜአችን በሙሉ ከውስጣችን ወደፊት ወደኋላ ይላል። በክፉ የተሞሉ ልቦችም ቢያንስ ቅንጣት ያህል ጥሩነት ይኖራል፤ ከሁሉም ጥሩ ከሚባለውም ልብ ከአንድ ጥጓ ትንሽ ክፉነት ይኖራል።
በየቦታው እየዞሩ ያሉ ክፉ ስራ የሚሰሩ ክፉ ሰዎች ቢኖሩና እነሱን ከኛ መለየትና ማጥፋት ብቻ ቢሆን ኖሮ እንዴት ቀላል ነበር? ግን ጥሩና ክፉን የሚለየው መስመር ከያንዳንዱ የሰው ልጅ ልብ መካከል ነው የሚያልፈውና ማን አለ ከራሱ ልብ ቁራጭ ቆርጦ ለማጥፋት ፈቃደኛ ይሆነ?
እያንዳንዶቻችን ልብ ውስጥ ያለው ክፋት ተጠራቅሞ ነው በመሪዎቻችን ላይ የሚታየው።

ሆኖም አሁን የህወሓት ስልጣን በሚገባው እየመነመነ ስለሆነ የትቭራይ ህዝብ ስለማንነታቸው ስለ ሃይማኖት እና ትውፊታቸው ስለ ፀረ ሃይማኖት መሪዎቻቸው እራሳቸውን ለመመርመር ጥሩ ጊዜ ይመስለኛል። የትግራይ ህዝብ በመጀመርያ ኮሙዩ ኢስት ነው ወይንም ሃይማኖተኛ። ልጎቹ ሃይማኖት የለሽ ገንዘብ እና ስልጣን አምላኪዎች ሆነው እንዲያድጉ ነው የሚፈልጉት? መሪዎቻቸው እየወደቈየተነሱምቢሆን ሃይማኖታዊ ቢሆኗይሻልም ወይ። ይህ ነው ወይም ካርል ማርክስ ወዘተ ነው የ ትግራይ ትውፊት? እነዚህን ጥያቄዎችን ለመጠየቅ ትክክለኛው ጊዜ ይመስለኛል።

እኔ በትክክሉ ይር ትግራይ ሰው ባልሆንም እንደ ኢትዮጵያዊነቴ ይበልጥ እንደ ኦርቶዶክስ ክርስቲያን መሆኔ ይህ ጉዳይ የ ኤርትራም ተመሳሳይ በማርክሲስት ሻብያ መገዛቱ ጉዳይ እጅግ ያሳዝነኛል። እነዚህ ቦታዎች ለክርስትናችን ቁልፍ ምናልባትም ምንጭ ቦታዎች ናቸው። እንዴት ሐጢአተኞች ብንሆን ነው ወደ ፀረ ሃይማኖታዊ አገዛዝ የሸጥናቸው። እግዚአብሔር ይቅር ይበለን።

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!