Sunday, 10 March 2019

ለማ መገርሳ ልክ ነው፤ የዴሞግራፊ ለውጥ ግድ ነው

ከዚህ በፊት እንደጻፍኩት የጎሳ ብሄርተኝነትን ከፖለቲካችን ለመቀነስ እና ለማጥፋት የዴሞግራፊ ለውጦች ማምጣት ግድ ነው (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2016/09/curbing-ethnic-nationalism-via_26.html)። ምከንያቱ ባጭሩ እንዲህ ነው...

የጎሳ ብሄርተኝነት ህዝብ ውስጥ በተለይ የኦሮሞ ህዝብ ውስጥ በደምብ እንደገባ ሁላችንም ገብቶናል። በልሂቃን ደረጃ ብቻ ሳይሆን በብዙሃን ደረጃም። ይህን ጎሰኝነት በስብከት እና ልመና ማጥፋት አይቻልም። የተም ሀገር የጎሳ ብሄርተንኘት አንዴ ከሰፈነ የሚቅንሰው ነገር ፖለቲካዊ ድርድር ሳይሆን የዴሞግራፊያዊ ለውጥ ብቻ ነው። በኢትዮጵያ የሚያስፈልገው የዴሞግራፊ ለውጥ በኦሮሞ እና ሌላው ኢትዮጵያዊ መካከል መቅላቀል እና ውህደት (integration and assimilation) ነው። ህዝቡ ተቀላቅሎ ተጋብቶ ተዋልዶ የቅይጥ ባህል እና ህዝብ መጨመር አለበት። በዚህ መንገድ የጎሳ ብሄርተኛው ጎራ እያነሰ ይሄዳል የፖለቲካ ኃይሉም ይመነምናል። ይህን የሚያስፈጽም አንድ ፖሊሲ ኦሮምኛ የህገር ሙሉ ቋንቋ ማድረግ ነው። ይህ ኦሮሞዎች ከኦሮሚያ ወደ ሌላው ኢትዮጵያ እንዲፈልሱ ይጋብዛል። ለምሳሌ ኦሮምኛ ለማስተማር ወደ አማራ ክልል ይመጣሉ። ይህ ፈልስት መቀላቀልን እና መወሃድን ያመጣል። ከላይ የጠቀስኩት ጽሁፍ ባጭሩ ይህን ነው የሚለው።

በቅርቡ ለማ መገርሳ ስለኦሮሞ ህዝብ ወደ ከተማ መፍለስ እናለበት ያሉት ነገር ከዚህ ጋር አብሮ ይሄዳል። ለምሳሌ አዲስ አበባ ዙርያ የሚኖረው ባብዛኛው ኦሮሞ ነው። አዲስ አበባ ባደገች ቁጥር በሜትሮፖሊታን ከተማው ያለው የኦሮሞ ህዝብ ቁጥር እየጨመረ መሄዱ አይቀርም። ከላይ በጻፍኩት አንጻር ይህ የኦሮሞ ህዝብ በአዲስ አበባ መብዛት አይቀሬም ብቻ ሳይሆን እንደ ጥሩ ነገር ነው መታየት ያለበት። ከተማው ህዝቡን ይቀላቅለዋል እና ያዋህደዋል። ይህ ውህደት የጎሳ ብሄርተኝነትን ይቀንሳል። ስለዚህ ኦሮሞዎችን ወደ አዲስ አበባ እና ሌሎች ከተሞች እንዲፈልሱ ያለው የኦዴፓ እቅድ ጥሩ ነው ማለት ይቻላል።

አሁን ከኛ ከኢትዮጵያ ብሄርተኞች ጎራ የሚጠበቀው ይህ እቅድ በምንፈልገው በአውንታዊ መስመር እንዲካሄድ ነው። «የጎሳ ጌቶዎች» ወይንም የአንድ ጎሳ ሰፈሮች እንዳይፈጠሩ፤ እውነታዊ ውህደት እንዲኖር፤ ሌላው ህብረተሰብ ኦሮምኛ እንዲማር፤ አድሎዋዊነት እንዳይኖር፤ ወዘተ መስራት አለብን። ሌላው ከኛ የሚጠበቀው ነገር የኦሮሞዎች መብት እና ፍላጎት በአዲስ አበባ እንደሚከበረው የሌሎች ዜጎች መብት እና ፍላጎት በኦሮሚያ እንዲከበር መሟገት እና ማስፈጸም ነው። አልፎ ተርፎ ኦሮሙማ (የኦሮሞ ባህል) በአዲስ አበባ እና መላው ኢትዮጵያ እንዲንጸባረቅ በመስማማት in exchange የጎሳ ፌደራሊዝም ሀገ መንግስቱ እንዲቀየር መሟገት እና መደራደር አለብን። ይህን ለማድረግ ታላቅ አቅም እና መደራጀት ይጠበቅብናል።

ነገሮችን ሁሉ በአውንታዊ መልኩ እንደ opportunity ማየት የአሸናፊነት ምልክት ነው። ኦዴፓ ኦሮሞን ወደ አዲስ አበባ እንዲሄድ እናበረታታለን ሲል እኛ እሰየው ብለን በሂደቱ ተሳትፈን እኛ የምንፈልገው መልክ እንዲይዝ ማድረግ አለብን። ከውጭ እያየን በፍርሃት ከማልቀስ ጉዳይ ውስጥ ገብተን መምራት ነው ያለብን።

ስለዚህ ለማ መገርሳ ልክ ነው፤ የዴሞግራፊ ለውጥ ግድ ነው። በዚህ መንገግድ ብቻ ነው መቀላቀል እና መዋሃድ የሚመጣው። በዚህ መንገድ ብቻ ነው አሁን በህብረተሰባችን የሰፈነው ጎሰኝነት ከረዥም ዓመታት በኋላ እንዲቀንስ እና እንዲጠፋ ማድረግ የሚቻለው።

Saturday, 9 March 2019

የአዲስ አበባ ህዝብ መደራጀት ምን ይመስላል?

ይዽርጅጥ ጽም፤ «የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ድርጅት»

ተእልኮ፤ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች መብት እና ጥቅም ለማስከበር የሚሰራ ድርጅት።

መሰረታዊ አቋሞች፤ ፩) አዲስ አበባ በአዲስ አበባ ነዋሪዎች ነው መገዛት ያለበት ፪) አዲስ አበባ ከጎረቤት ኦሮሚያ ክልል በተገቢው መልካም እና ገንቢ ግንኙነት ሊኖረው ይገባል ፫) የአዲስ አበባ ህዝብ መብቶች መከበር አለበት ፬) መካከለኛው እና ለዘብተኛው መንገድ መቅደም አለበት፤ ጸንፈኝነት ለአዲስ አበባ ህዝብ ጎጂ ነው።

የአደረጃጀት ሂደት፤ ፩) 100 የአዲስ አበባ ባለሃብቶች ሰብስቦ ከያንዳንዱ 10 ሚሊዮን ሰብስቦ መሰረት ማድረግ ፪) ሰፊ የንቃት እና የአባል መለምለም ሂደት አካሄዶ አንድ ሚሊዮን አባላት ማግኘት ፫) አዲስ አበባን በአንድ ለአምስት አሰራር ሁሉንም የህብረተሰብ እና ኤኮኖሚ ክፍል መቆጣጠር።

ስልቶች፤ ፩) አንድነት፤ የሃሳብ ልዩነቶች በአግባቡ ተንሸራሽረው መፍትሄ ይገኛሉ። ድርጅቱ ጸብ፤ ቂም፤ ሹክሹክታ ወዘተ ይጸየፋል ፪) ግልጽነት፤ ሚስጥርነት ድክመትን ያመጣል። የድርጅቱ ስራ በሙሉ የግልጽነትን ፈተና መቋቋም አለበት፤ ሚስጥር ከወጣ የሚጎዳ ድርጅት መሆን የለበትም ፫) ተሳታፊነት፤ ድርጅቱ አባላት እንዲሳተፉ መጣር አለበት አባሉ የድርጅቱ ባለበትነት እንዲሰማው።

የሰለጠነ እና የሰከነ ፖለቲካ መንፈስ፤ ለቅዋሜ የሚይመች አቋም፤ ድርጅቱ ኢ-ስሜታዊ ሆኖ የሚወስደው አቋም እና የሚያንጸባርቀው ሃሳብ ማንኛውንም ፈተና የሚቋቋሙ መሆን አለበት። ምሳሌዎች፤

፩) ልዩ ጥቅም ጉዳይ፤ «እንዴት ለኦሮሞ/ኦሮሚያ ልዩ ጥቅም ይኑር ትላላችሁ» ከማለት ምንድነው ልዩ ጥቅም ብሎ ወደ ውይይት መግባት። የኦሮሚያ ልዩ ዞን ነዋሪዎች የአዲስ አበባ አገልግሎትን ማግኘት ይችላሉ፤ የኦሮሚያ ነጋዴዎች በአዲስ አበባ እንደ ነዋሪ መነገድ ይችላሉ፤ ወዘተ አይነቱ ልዩ ጥቅም እንደ ማንኛውም ሜትሮፖሊታን ከተማ ተገቢ ነው። እስቲ ሌላ ምን ልዩ ጥቅም አለ ብሎ መወያየት ነው የድርጅቱ መንገስ።

፪) ኦሮሙማ በአዲስ አበባ፤ ከቋንቋ በላይ ኦሮሙማ የለም። ስለሆንም አዲስ አበባ በኦሮሚያ ልዩ ዞኖች በመከበቧ ኦሮምኛ የከተማዋ ሁለተኛ ቋንቋ ብትሆን መልካም ነው። በኦሮሚያ ልዩ ዞኖች አማርኛ እንደሚሰራው በአዲስ አበባ ኦሮምኛ ሊሰራ ይገባል።

፫) «የአዲስ አበባ ባልቤት ኦሮሚያ ነው»፤ ይህ አባባል ኢ-ዴሞችራሲያዊ ነው። የማንኛውም ቦታ ባለቤት ነዋሪው ነው። አዲስ አበባም ይሁን ልዩ ዞኖቹ ነዋሪዎቻቸው ናቸው የፖለቲካ ባለቤቶቹ። አለበለዛ ወደ አምባገነነት ገባን ማለት ነው።

፬) ተፈናቃዮች፤ የኦሮሞ ገበሬም ሌሎች የአዲስ አበባ እና ዙርያ ተፈናቃዮች በሙሉ ጉዳያቸው ይታይ። ማን ተፈናቀለ ምን ያህል ካሳ ተሰጠው ማን ካድሬ/መሪ በምዝበራ ተጠቀመ። ከምርመራው በኋላ እርምቶች ይደረጉ። አልፎ ተርፎ መሬት የግል ይሁን የሚለውን አቋም ድርጅቱ ያራምድ። መሬት የግል ቢሆን ኖሮ መፈናቀል የሚባል አጸያፊ ነገር አይኖርም ነበር። አልፎ ተርፎ አዲስ አበባ ዙርያ ያለው ኦሮሞ እና ሌሎች ገበሬዎች እጅግ ሃብታም ይሆኑ ነበር መሬ ታቸውን በመሸጥ። መንግስት 100,000 ብር ካሳ የሚሰጠው ግለሰብ የገበያ ዋጋውን አንድ ሚሊዮን ብር ሊሰጠው ይችላል።

የአዲስ አበባ ህዝብ ማለት...

በሩን ከፍቶ የሚያድር ሰው ዘራፊው ሲመጣበት እባክህ አትዝረፈኝ ብሎ የሚለምን።

ሳያርስ ሳይዘራ የክረመ ገበሬ አዝመራ ሳይኖረው እግዚአብሔርን የሚያማርር።

አትንቶ የማያውቅ ተማሪ ፈተናውን ሲወድቅ አስተማሪውን የሚወቅስ።

ወዘተ።

የአዲስ አበባ ህዝብ (ከነ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ) ለዓመታት በትንሿ ህወሓት የተገዛው የራሱን የቤት ስራ ስላልሰራ ነው። ይህ የቤት ስራ ተደራጅቶ ለራስ መብት መቆም ነው።

ካሁን ወድያ የአዲስ ህዝብ ካልተደራጀ ለሚደርስበት ጉድ ከራሱ በቀር ማንም ጥጠያቂ አይኖርም። የአምስት ሚሊዮን ህዝብ ከተማ መቶ ሚሊዮን ብር በጀት፤ አንድ ሚሊዮን አባል ያለው ድርጅት ማቋቋም ካልቻለ በቅኝ ግዛት መገዛት ይገባዋል አይቀርለትምም።

Monday, 4 March 2019

ተረት ተረት፤ አዲስ አበባ የኦሮሞ ገቤሬዎችን አፈናቅሏል

1. የአዲስ አበባ ህዝብ ምንም ፖለቲካዊ ውሳኔ አድርጎ አያውቅም። በኢህአዴግ (ከነ ኦህዴድ) የተገዛ ህዝብ ነበር። ስለዚህ የአዲስ አበባ ህዝብ ማንንም አላፈናቀለም። አፈናቃይ ካለ ኢህአዴግ ከነ ኦህዴድ ነው።

2. ከአዲስ አበባ የተፈናቀሉት ባብዛኛው ኦሮሞ ቢሆንም የተወሰኑ አማሮች እና የሌላ ጎሳ አባላት ነበሩ።

3. ካአዲስ አበባ ውስጥ የተፈናቀሉት ደግሞ ከሁሉም ጎሳ ነበሩ። እነዚህ የአዲስ አበባ ተፈናቃዮች ከአዲስ አበባ ዙርያ የተፈናቀሉት ገበሬዎች ይበልጥ ተበድለዋል በደልን በገንዘብ ከተረጎምነው። ከካዛንቺስ 50 ካሪሜትር ቦታው የተፈናቀለው ምናልታብት ሁለት ሶስት ሚሊዮን ብር ነው ያጣው። ከቡልቡላ የተፈናቀለው ገበሬ የዚህ ሩብም አልከሰረም።

4. ገበሬዎች እና ሌሎች «ተፈናቀሉ» ስንል መንግስት የማይመጥን ትንሽ ካሳ ሰጥቷቸው በግድ ከመሬታቸው አስነሳቸው ነው። አድግራጊው የአዲስ አበባ ህዝብ ያልመረጠው የአዲስ አበባ መንግስት ውየንም አብዛኛው ጊዜ የኦህዴድ መንግስት ነው። ገበሬውን አነስተኛ ካሳ ሰጥቶት ለኢንቬስተር በከፍተኛ ዋጋ ሽጦ ትርፉን ኪስ አስገብቷል። ለዚህ የአዲስ አበባ ህዝብ ትጠያቂ አይደለም፤ ኢህአዴግ እና ኦህዴድ ናቸው።

5. ታላቁ ግን ማንም የማያነሳው ጉዳይ የሀገራችን የመሬት ፖሊሲ ነው። መሬት የመንግስት በመሆኑ ነው ገበሬዎችም ሌሎችም የሚፈናቀሉት እና «ተፈናቀሉ» የሚባለው። አዲስ አበባ ሲሰፋ (እንደ ከተማ ይሁን እንደ metropolis) ዙርያ ያሉት ገበሬዎች ዋና ተጠቃሚ ነበር መሆን ያለባቸው፤ ይሆኑም ነበር መሬት የግል ቢሆን። አዲስ አበባ ዙርያ ያሉት ገበሬዎች ከተማው እየሰፋ ስለሄደ መሬታቸውን በእጅግ ውድ ዋጋ ሊሸጡ እና ሊጠቀሙ ይችላሉ። ቡልጋ ያለው ገበሬ የመሬቱ ዋጋ አንድ ብር በካሬ ቢሆን ይው መሬት አዲስ አበባ ዙርያ መቶ ብር ሊሆን ይችላል። በዚህ መንገድ ነው የትም ሀገር ከተማ ሲሰፋ ዙራይ ያሉት ገበሬዎች ሎተሪ እንዳሸነፉ የሚቆጠረው። ግን ኢትዮጵያ ገበሬው መረቱን መሸት ስለማይፈቀድ እና መንግስት ሲፈልግ መንጠቅ ስለሚችል ከተማ ዙርያ ያለ ገበሬ ጭራሽ ይሰጋ! ስለዚህ በዚምህ ረገድ ጥፋቱ የአዲስ አበባ ህዝብ ሳይሆን የኢህአዴግ እና ኦህዴድ የመሬት ፖሊሲ ነው። አዲስ አበባ ዙርያ ያሉ ገበሬዎች በኢህአዴግ/ኦህዴድ ምክንያት በሚሊዮኖች የሚቆጥር ብር አጥቷልና!

የጎሳ ፌደራሊዝም ችግር አንድ ነው፤ የግጭት መንስኤ ነው!

ዛሬ አንድ ሁለት ውይይቶች ስለ ሀገራችን «የጎሳ ፌደራሊዝም» ተመልክቼ ነበር። ውይይቶቹ ያተኮሩት በጎሳ ፌደራሊዝም እንደ ጽንሰ ሃሳብ ነው። ተናጋሪዎቹ ታሪክን እና ርዕዮት ዓለምን ፈትሸው የጎሳ ፌደራሊዝም ለሀገራችን ይበጃል ወይንም አይበጅም ብለው ተከራከሩ። Of course ውይይት/ክርክሩ የትም አልደረስም። The participants, as usual, talked right past each other።

በመጀመርያ ደረጃ አንዱ የሌላውን ፍላጎት የማይረዳበት ውይይት ውይይት አይደለም። ስለ ጎሳ ፌደራሊዝም የሉን ውይይቶች እንዲህ ናቸው። እኛ አቋማችንን እንናገራለን ሌላውም እንዲሁ አንድ ሌላው አይገባውም ውይይቱም ባለመግባባት ያልቃል።

ይህ የሚሆንበት አንዱ ምክንያት የውይይት እና ቅራኔ መፍታት ስልት በማጣት ነው። ግን አሁን ማተኮር የምፈልገው እዚህ ላይ አይደለም። ሁለተኛው ምክንያት ነው፤ ይህ ደግሞ የጎሳ እና ማንነት ጉዳይ ስሜታዊ በመሆኑ ለውይይት አይመችም። አይሆምም ማለት ይቻላል። «እኔ መጀመርያ ኦሮሞ ነኝ ቀጥሎ (ምናልትባት) ኢትዮጵያዊ» ሲል አንዱ ሌላው «እንዴት እንዲህ ትላለህ» ብሎ ሁለቱም በስሜታቸው ይመራሉ። አንዱ ሌላውም ማሳመን አይችልም።

ለዚህ ነው በጎሳ ፌደራሊዝም ጉዳይ ታሪክን እና ርዕዮት ዓለምን ፈትሸን መከራከር የትም የማያደርሰን። በጎሳ ፌደራሊዝም የሚያምን እና የጎሳ ፌደራሊዝምን የሚጠላው ሁለቱም ምክንያቶች በመሰረቱ ስሜታዊ የማንነት ናቸው። እነዚህን በርዕዮት ዓለም እና ታሪክ (in the eye of the beholder) ማስታረቅ አይቻልም።

ሁለቱን ጎራዎች ለማግባበት ወደ ሌላ level መሄድ ያስፈልጋል። ይህ ደረጃ እንዲህ ነው፤ እኔ የጎሳ ፌደራሊዝም ለኢትዮጵያ አይሆንም የምልበት ምክንያት ታሪክ እና ርዕዮት ዓለም ሳይሆን በ evidence ምክንያት ነው። የ24 ዓመት ታሪክ ከነ ያለፈው አንድ ዓመት የለውጥ ዘመን ታሪክ የሚያሳየው የጎሳ ፌደራሊዝም የግጭት መንስኤ መሆኑ ነው። የጎሳ ፌደራሊዝም በጎሳዎች መካከል በርካታ ግጭቶች እንዲኖሩ አድርጓል። ሰዎች በጎሳቸው ምክንያት የሚጎዱበት ዘመን አምጥቷል። ይህ ጉዳት ለተወሰኑ ጎሳዎች ብቻ ሳይሆን በመላው ሀገሩ ነው። ለዚህ በርካታ የ25 ዓመት evidence አለ።

ለዚህ ነው የጎሳ ፌደራሊዝም መቀየር አለበት ብለን መከራከር ያለብን። የ24 ዓመት የጭቆና እና የአንድ ዓመት የአንጻራዊ ነጻነት መረጃ የሚያሳየን የጎሳ ፌደራሊዝም ህግ እና መንፈስ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎቻችንን እንደጎዳ ነው። ሶማሌ በሶማሌነቱ፤ ኦሮሞ በኦሮሞነቱ፤ ጊዴኦ በጊዴኦነቱ፤ አማራ በአማራነቱ፤ አንዋክ በአንዋክነቱ፤ ወላይታ በወላይታነቱ፤ ስዳማ በሲዳማነቱ፤ ወዘተ ተጎድቷል። የጉዳት ፈጻሚዎቹም እንዲሁ የተለያዩ ናቸው። «ህወሓት» ወይንም የህወሓት አሽከሮች ብቻ አይደሉም ጨቋኞቹ። ህዝቡ እራሱ ይጭቋቆናል። ለዚህ በርካታ መረጃ አለን።

አንድ ታካቅ መራጀ ደግሞ የሁሉም ጎራ ፖለቲከኞች «ካልተጠነቀቅን እርስ በርስ እንፋጃለን» ማለታቸው ነው (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/blog-post.html)! የጎሳ ፌደራልዚምን የሚደግፉትም የማይደግፉትም የጎሳ እልቂት is right around the corner ብለው ደጋግመው ይነግሩናል። ለጎሳ ፌደራሊዝም ከዚህ የባሰ indictment የለም!

ስለዚህ ለ«ዜግነት ፖለቲካ» ደጋፊዎች እና ሌሎች የዚህ የጎሳ ፖለቲካ የሚጠሉ ሰዎችን የምመክረው፤ ስሜትን በሃሳብ አትከራከሩ፤ የትም አትደርሱም። በመሰረቱ የጎሳ ፌደራሊዝም ሰውን የሚጎዳ ባይሆን ምን ችግር አለው? ምንም። የጎሳ ፌደራሊዝም ኢትዮጵያን በሰላም ቢያስተዳደር እኔ የሚጀመርያ ደጋፌው ሆን ነበር። ግን አይደለም። ሃቁ ይህ ነው። የጎሳ ፌደራሊዝም የምንጠላው የግጭት እና ጭቆና መንስኤ ስለሆነ ነው። ይህ ደግሞ በመረጃ የተመሰረተ statement ነው። ክርክራችን በታሪክ እና ርዕዮት ዓለም የተገደባ ሳይሆን ሙሉ በሙሉ መረጃ የተመሰረተ ነው። ይህ መከራከርያ መንገድ ነው አዋጪ ብዬ የማስበው።

Friday, 1 March 2019

የአዲስ አበባ ጉዳይ እና የሃላፊነት ፖለቲካ

በተለያዩ ጽሁፎቼ የኢትዮጵያ ፖለቲካ መሰረታዊ ችግር የ«ኢትዮጵያዊነት» ጎራው ለራሱ እጣ ፈንታ ሃላፊነት አለመውሰዱ ነው ብያለሁ። ላለፉት 50 ዓመታት ተደራጅቶ ፍላጎቶቹን አጣርቶ ከማስከበር ይልቅ ህልውናውን ለሌሎች ትቷል። ሃላፊነት ለሌሎች መታው ባህል አድርጎታል። ይህ አካሄድ የ«ለቅሶ ፖለቲካ» ብሄ ሰይምዬዋለሁ (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/blog-post_16.html)።

ይህ ሁኔታ ምክንያት አለው፤ የኢትዮጵያዊነት ጎራው በአብዮቱ ጀምሮ እርስ በርስ ተገዳድሎ ልሂቃኑ እራሱን አጥፍቶ እስካሁን አላገገመም። (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/1.htmlhttps://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/2.htmlhttps://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/3.htmlhttps://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/4.html)። ቢሆንም በዚህ አካሄድ መቀጠል አይቻልም። ሌሎችን «ፍላቶእ እና መብታችንን አስከብሩልን» ብለን እየለመንን መቀጠል አይቻልም።

አሁን የሚያስፈልገን ከ«ለቅሶ ፖለቲካ» ወጥተን፤ ከህጻንነት እና ብሽተኝነት ወትጠን ወደ «ሃላፊነት ፖለቲካ» መግባት አለብን። ግድ ነው፤ አማራጭ የለም። እነ ለማ ይሁን አቢይ ይሁን ህወሓት ይሁን ግንቦት 7 ይሁን አብን ወዘተ እንዲህ አድርጉልን ብለን መለመን አይቻልም። ካሁን በኋላ ሁላችንም «ይህ ይሁን»፤ «ይህ ይደረግ»፤ «እከለ ይውደም» ወዘተ ከማለት ወደ «እኔ ይህን አደርጋለው» የሚለው አመለካከት መግባት አለብን። ልመና በቃ፤ የራሴን እጣ ፈንታ እራሴ ወስነዋለው ወደሚለው መግባት አለብን።

የአዲስ አበባ ጉዳይ የዚህ የአስተሳሰብ እና ተግባር ለውጥ አስፈላጊነት በደምብ ይገልጻል (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/09/blog-post_97.html)። ልሂቃኖቻችን እስካሁን እነ ኢህአዴግን፤ ህወሓትን፤ ኦዴፓን፤ የኦሮሞ ብሄርተኞችን፤ አዴፓን፤ ጥ/ሚ አቢይን፤ ፕሬዚደንት ለማን፤ ወዘተ እባካችሁ እንዲህ እንዲያ አድርጉ አታድርጉ እያሉ ለው ዓመት ይጮሃሉ። ግን አንድ የሚባል የአዲስ አበባ ህዝብን ጥቅም የሚያንጸባርቅ እና ለማስከበር የሚሯሯት ድርጅት የለም? የአዲስ አበባ ህዝብ ህልውናውን ለሌሎች ሰጥቶ ሌሎቹ የሚፈልጉትን ሲአደርጉ ልሂቃኑ ያለቅሳል! ይህ ምን ማለት ነው? የአዲስ አበባ ህዝብ እራሱን አደራጅቶ ፍላጎቱን እና መብቱን ዘርዝሮ ማስከበር ካልቻለ እነዚህ የማይወክሉት ተቋሞች የፈለጉትን ያደርጋሉ። ይህ እኮ እጅግ basic የሆነ ነገር ነው።

እስከ ዛሬ የኛ ልሂቃን እና ሚዲያ ይህን መሰረታዊ ጉዳይ ትተው በማልቀስ እና መለመን ነው የዋሉት። የራሳችንን ጥፋት (አለመደራጀት) ላለማየት ትብሎ ህልውናችንን አደጋ ውስጥ ከትተናል! ይህ ሁሉ ችግር ስላልተደራጀን ነው እና እንደራጅ ከማለት ሌሎች ስለሚያደርጉት እናለቅሳለን። ይህ ለቅሶ ምንም ለውጥ አላመጣም አያመጣምም። ህዝባችን በንዴት እንዲደራጅ አላደረገም። ይባስ ሌሎች ላይ ጣት በመጠቆም የራሳችንን ጥፋት እንዳናይ ስበብ ሆኖናል። ጉርጓዳችንን ይበልጥ እንድንቆፍር አድርጎናል።

አሁን ግን አንዳንዶች መራራ የሆነውን መድሃኒት ውጠን ወደ ፊት መራመድ እንዳለብን የገባቸው ይመስላል።


ከዚህ ከኢሳት ዝግጅት የአዲስ አበባ ህዝብ መዋናነት መደራጀት አለበት ትባለ። ያለመደራጀታችን ጥፋታችንን አመንን ማለት ነው፤ ይህን ማመን ነው መራራው መድሃኔት። ካመንን በኋላ ሙሉ አቅማችንን ወደ መደራጀት ስራ ማሰለፍ ነው ያለብን። ካሁን ወድያ አንዳች የልሂቃን እና ሚዲያ ደቂቃ በእሮሮ፤ ለቅሶ፤ እና ልመና መጥፋት የለበትም። ሙሉ አቅማችን ወደ መደራጀት።

ምን ማለት ነው የመደራጀት ስራ (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/blog-post_18.html)? ብዙ ሚስጥር የለውም፤ የህዝብ የማህበራዊ እና ፖለቲካዊ መደራጀት ለሺዎች ዓመታት የተደረገ ነገር ነው። የአዲስ አበባ ህዝብ «የአዲስ አበባ ህዝቦች ድርጅት» ያስፈልገዋል። የዚህ ድርጅት (ድርጅቶች) ተእልኮ የአዲስ አበባ ነዋሪዎችን ጥቅም ማስከበር ነው። ቀላል ተእልኮ ነው፤ ሌላ ጣጣ አያስፈልገውም። ድርጅቱ በርካታ (በመቶ ሺዎች የሚቆጠር) አባላት ያስፈልጉታል። ባለ ሃብቱ በደምብ መሳተፍ አለበት። ስብሰባ፤ ሰርቬ፤ ምርጫ፤ ወዘተ የሚያካሄድ መሆን አለበት። አባላቶቹ በየ ማህበራዊ ዘርፍ፤ በየ መስርያቤት፤ በዬ ሰፈሩ የሚሰሩ እና የሚኖሩ መሆን አለባቸው። ድርጅቱ ሰፊ ኔትወርክ ኖሮት «የሚፈራ» ማለትም አቅም ያለው መሆን አለበት። በተለያዩ የከተማው ጉዳዮች፤ መብራት፤ ውሃ፤ መንገድ፤ ደህንነት፤ ጤንነት፤ መፈናቀል፤ ውክልና፤ ወዘተ የሚሰራ መሆን አለበት። በዴሞክራሲያዊ መልኩ የአባላቱን ፍላቶ የሚያውቅ፤ የሚያስከበር እና የሚወክል መሆን አለበት።

ይህ ድርጅት ሲኖር፤ ዛሬ ቢኖር ስለ አዲስ አበባ ያለው ጭቅጭቅ አይኖርም ነበር። ሁሉም ተሳታፊዎች የአዲስ አበባ ህዝብ ፍላጎትን አበጥረው ያውቃሉ። የሁሉም አቋም ሰልሚታወቅ የፖለቲካ ድርድሮች በግልጽ እና በጽጋ ይካሄዱ ነበር። የለገጣፎ ሰዎች አይፈናቀሉም ነበር። ጉዳዩ ገና ሲነሳ ድርጅቱ ተሳትፎበት ድርድር ተደርጎበት በሰላም በሁሉም የሚያስማማ መልኩ ይፈታ ነበር። የኦሮሚያ «ልዩ ጥቅም» ጉዳይም እንዲሁ። ወካይ ድርጅት ቢኖርን «ልዩ ጥቅም» ብለን አናለቅስም ነበር። ድሮውኑ ተደራድረን የልዩ ጥቅም ትርጉም ላይ ተስማምተን ነገሩ በሰላም ይወሰን ነበር። ወዘተ።

የአዲስ አበባ ችግር የመጣው በህወሓት ምክንያት አይደለም። በኦሮሞ ብሄርተኞች ምክንያት አይደለም። መሰረታዊ ችግሩ የአዲስ አበባ ህዝብ እርስ በርስ ተስማምቶ አለመደራጀቱ ነው። ይህን አምነን አንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ለቅሶ እና ልመናችንን ትተን ሙሉ አቅማችንን ወደ መደራጀት ማዋል አለብን። አለበለዛ በየበታችንነት እና ተገዥነት ስሜት እንደተገዛን እንቀጥላከን። መገዛት ማለት የራስን እጣ ፈንታ ለሌሎች መተው እና በራስ ህይወት ሃላፊነት አለመውስውድ ነው። ይህ ላለፉት በርካታ ዓመታት ጉዞአችንን ይገልጻል።