Showing posts with label Amhara nationalism. Show all posts
Showing posts with label Amhara nationalism. Show all posts

Friday, 4 November 2022

ስለ አማራ ብሔርተኝነት እንሟገት፤ በቅንነት!

ይህን አስመልክቶ መቼ ነው ለህዝብ ይፋ የሆኑ ውይይቶች የሚካሄዱት? ለአምራ ፖለቲካ ጤንነት ግልጽ ውይይት አስፈላጊ ይመስለኛል።

እኔ እንደሚገባኝ የአማራ ብሔርተኞች መሰረታዊ ችግር በእውነታ (reality) ሳይሆን በህልም/ቅዠት  የተመሰረተ ነው። የአማራ ብሔርተኝነት ህልም እንዲህ ነው፤ 

እነ አሳምነው ጽጌ (ነፍሱን ይማር) ወይንም ዛሬ እነ ዘመነ ካሴ በአማራ ብሔርተኝነት ፖለቲካ ተጠቅመው 1) ወልቃይት/ራያን ይመልሱ ነበር 2) ቤኒሻንጉል፤ ወለጋ፤ አዲስ አበባ ወዘተ ያለውን አማራ ይጠብቅ ነበር 3) ፌደራል መንግስት ላይ ከባድ ትጽእኖ ያሳድሩ ነበር 4) አማራ ክልልን ያጎለብቱ ነበር 5) ሀገ መንግስቱን ያስቀይሩ ነበር።

ይህ ከእውነታ እጅግ የራቀ እንደሆነ ግልጽ ነው። ለ50 ዓመት ተደራጅቶ የማያውቅ አማራ በአንድ ሁለት ዓመት ተደራጅቶ ህወሓትን፤ ኦነግን፤ ፌደራል መንግስትን፤ ሱዳንን፤ ምእራባውያንን፤ ግብጽን ሁሉ ሊገጥም ይችላል ብሎ ማሰብ ቅዠት ነው። ሆኖም ስሜተን ስለሚቀሰቅስ እና ተከታይን ስለሚያበዛ የፖለቲካ ነጋዴዎች ይህንን ቅዠት በመሸጥ ለስልጣን ይጠቀሙበታል።

የአማራ ህዝብን ህልውና የሚጠብቅ በእውነታ ላይ የተመሰረተ የፖለቲካ አካሄድ ነው። ይህም ህዝቡን በኢትዮጵያዊነት ማደራጀት ነው። ይህ አካሄድ የሚገነዘበው እውነታ ይህ ነው፤ የአማራ ትቅም የሚጠበቀው የመአከላዊ መንግስቱ በአግባቡ ከጠነከረ ነው። በተቃራኔው መአከላዊ መንግስቱ ከደከመ እና የጎሳ ፖለቲከኞቹ ከጠነከሩ አማራ ይጎዳል። ምክንያቱም 1) አማራ በዬ ክልል ተበትኗል እና 2) አማራው ከሌሎች ጎሳዎች የሚለየው ከባድ የትርክት ስራ ተሰርቶበት ጎሰኞቹ የአማራ ጥላቻን የፖለቲካ ንግድ አድርገውታል 3) አማራ በርካታ ታሪካዊ ጠላቶች አሉት። በዚህ ምክንያት የአማራ ህልውና ከመአከላዊ መንግስት ህልውና ጋር የተሳሰረ ነው። ኢትዮጵያዊነት የግዱ ነው።

«ኢትዮጵያዊነትን ሞክረን አልሆንም» የሚሉ አሉ። ይህ አስተያየት የሚመነጨው ከታሪክ አረዳዳት ስህተት ነው። በኃይለ ሥላሴ አገዛዝ ኢትዮጵያዊነት (እንደ nation state) ገና እየተገነባ ነበር። በደምብ ሳይጠነክር እራሱ የኢትዮጵያዊነት ጎራው (በዚህ ውስጥ አማራው ሙሉ በሙሉ የተካተተበት ነበር) ተከፋፈለ እራሱ ላይ አብዮት አስነሳ። የኢትዮጵያዊነት ጎራው ገና ያልተገነባን ኢትዮጵያዊነትን አደከመ ማለት ነው። ደርግ ደግሞ አባባሰው። አብዮቱን ሲያፋፍም የኢትዮጵያዊነት የፖለቲካ ጎራውን (እራሱንም ጨምሮ) ይበልጥ አድክሞ የኃይል ሚዛኑ ተቅላላ ወደ ጎሰኞቹ ጎራ እንዲያመዝን አደረገ። መጨረሻ ላይ ስልጣንን ለጎሰኞቹ አስረከበ። ጎሰኞቹ ሲያሸንፉ አማራ መጎዳት ጀመረ።

ይህ ታክሪክ በግልጽ የሚያስተምረን የአማራ ህዝብ ህልውና ከኢትዮጵያዊነት የተሳሰረ መሆኑ ነው። ለዚህ ነው ለአማራ ህዝብ ኢትዮጵያዊነት የግድ ነው ያልኩት።

የግድ እንደሆነ ካመንን ቀጥሎ ጥያቄ እንዴት ነው ኢትዮጵያዊነትን ማጠንከር የምንችለው ነው። አዎን እጅግ ከባድ ስራ ነው። ለዚህም ነው አንዳንዱ አይቻልም ብሎ የሚሸሸው። የጎሳ ፖለቲካ የተፋፋመብት ሀገር ውስት ኢትዮጵያዊነትን ማቀንቀን ከጎሰኞቹ እጥፍ ድርብ ብልህነት እና የፖለቲካ ችሎታ ያስፈልገዋል። በዚህ ምክንያት የአማራ ልሂቃን ማተኮር ያለበት ይህ ከባድ ስራ ላይ ነው። ህዝቡን በቀላሉ ስሜት ውስጥ የሚከተው ግን መጨረሻ ላይ ገደል የሚከተው ቀላል ፖለቲካን ትቶ ወደ ከባዱ ግን የግድ የሆነ ኢትዮጵያዊነት ስራ መግባት አለበት። 

የዐቢይ አህመድ መንግስትን መደገፍ እና ውስጡ ሆኖ መስራት አንዱ የዚህ ስራ ስትራቴጂ ነው። መአከላዊ መንግስቱ መጠንከር አለበት። ሀገረ መንግስቱ (nation state) መጠንከር አለበት የጎሰኞቹ ጎራም ይሁን የውጭ ጠላቶችም በቀላሉ ሊያጠቁ እንዳይችሉ። ስለዚህ መንግስት ምንም ችግሮች ቢኖሩት ለምጉዳት ይበልጥ ለማፍረስ መስራት የለብንም። መንግስትን መገንባት ነው ያለብን በተቻለ ቁጥር በኛ ፍላጎት። ይህ ስትራቴጂ የአማራ ህዝብን ይበጃል ብቻ ሳይሆን ለህልውናው የግድ ነው።

ሁለተኛ ስትራቲጂ ከሌሎች የኢትዮጵያ ህዝቦች ጋር መግባባት የግድ ነው ኢትዮጵያዊነትን ለማጠንከርና ሀገር መንግስቱንም ለማጠንከር። ሰጦ ገብ መቻል አለብን። በሶፍት ፓወር (መገናኛ ብዙሃን በመቋቋም፤ ቋንቋ በመማር፤ ወዘተ) ሌሎች ብሄረሰቦች ላይ መልካም ተጸኖ ማድረግ መቻል አለብን። ጎሰኞቹ አማራን በአማርኛ ሚዲያዎቹ እንደሰበኩ ነው አማራው ግን ወደነሱ ጎራ አይገባም! ይህ መቀልበስ አለበት። በታሪክ ቁርሾዎች በግልጽ መነጋገር እና መስማማት ያስፈልጋል።  

Defensive መሆን አያስፈልግም። ለኢትዮጵያዊነት ተብሎ የሌሎችን ምልከታ በትህትና መቀበል አለብን። በነዚህ አካሄዶች የአማራ ልሂቃን እና ህዝብ ከሌሎች ህዝቦች ጋር በተለይም ከለዘብተኞች ጋር ትብቅ ትስስር እንዲኖረን መስራት የግድ ነው።

ኢትዮጵያዊነት ከባድ ስራ እንደሆነ እንደሚሆን ግልጽ ነው። ግን ለአማራ ህዝብ የግድ ነው። ሌላ አማራጭ የለውም ታሪክ ይህንን ነው ያዘጋጀለት። ስለዚህ ወደ ስራ መግባት ነው እንጂ ስራን ሸሽቶ ወደ «የእጽ ፖለቲካ» የሆነው የአማራ ብሔርተኝነት መግባት የአማራ ህዝብ ሞት ንወ የሚሆነው።

Wednesday, 10 July 2019

ኸርማን ኮሆን ስለ አማራ ያሉትን አስመልክቶ...

እንደ ኸርማን ኮሆን አይነቱ በተረታ ላይ ያሉ መካከለኛ ደረጃ ዲፕሌማት ይህን ያህል ትኩረት ማግኘታቸው የኢትዬጵያን የኃይል ድክመት ምን ያህል እንደሆነ ያሳያል።

ለማንኛውም የዛሬው የአምሀራ ብሔርተኝነት (ይልነበረው) የድሮ የአምሀራ የበላይነትን ለመመለስ ሳይሆን አሁን ያለው የብሶት እና የበታችነት መንፍስን ለማባበል ነው አላማው! የበላይነት ሳይሆን የበታችነት መንፈስ ነው መሰረቱ፡፡ ከዚህ ረገድ ከትግራይ እና ኦሮሞ የጎሳ ብሔርተኝነት ምንም አይለይም። ጨራሽ የነዚህ (ያፈደ) ግልባጭ ነው።

Thursday, 28 March 2019

Overtures to the TPLF

Some Amhara nationalists, in the wake of a perceived rise in the power of Oromo nationalism, are making overtures to the TPLF or 'Tigray' for a possible alliance to combat Oromo nationalism. I'm sorry, but this is the height of silliness! It simply repeats our decades long practice of negative-sum politics, as disastrous in the long-term as it is appealing in the short.

First, those who support citizenship federalism should not need the TPLF or anyone else to combat ethnic nationalism. The very fact that some think they need the help illustrates the fundamental problem - the lack of a large and powerful citizenship politics organization. If we had a coherent movement concomitant to our grassroots support, then we would have easily come to a favourable agreement with ethnic nationalists. But our lack of tangible political power makes us flail around looking for help anywhere we can get it, thereby repeatedly building our political house on sand. Inevitably our temporary alliances and escapes end and we're back at throats of former allies.

Second, the TPLF and, dare I say, a significant portion of the Tigrean elite is in the midst of an identity crisis imposed upon them by unfortunate historical circumstances. The advent of Communism, the 1974 revolution, the Dergue's terrible misgovernance, etc., led to the birth of a TPLF with an outlook that stood firmly against the long term interests of Tigreans. Tigray, being a small, industrious, region, stands to benefit from a citizenship based federalism, a multicultural and decentralized federalism but one in which the citizen is primary. Ethnic federalism is completely against the interests of Tigray, because that would result, more or less, in Tigreans not being able to freely live and work outside their region. Yet the TPLF and most Tigrean intellectuals still support ethnic federalism! This is the problem that the rest of us Ethiopians, Ethiopian nationalists and even Amhara nationalists have to tackle, through persuasion and discussion, of course. This will be a long process. However, we should not abort this process by allying with the TPLF in an artificial power play.



Friday, 18 January 2019

Unraveling NAMA's "Intellectual Cover"

የአማራ ብሄርተኝነት በመሰረቱ የብሶት ፖለቲካ (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/07/blog-post_30.html) ነው። የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን) መሪዎችም ተከታዮችም በትርክታቸው የሚያተኩሩት ስለአማራ ላይ የደረሰው የ27/44 ዓመት በደል ነው። አማራ ከሌላው ኢትዮጵያዊ ተለይቶ ተበድሏል ይላሉ። አልፎ ተርፎ ካሳም ይገባዋል ይላሉ። ከፖለቲካዊ ፕሮፓጋንዳዎቻቸው ምናልባት 80%ኡ ስለዚህ ስለ አማራው መጨቆን ነው። ይህ የአማራ ብሄርተኝነት በመሰረቱ በብሶት የሚመራ ንቅናቄ መሆኑን ያስረዳል።

ሆኖም እንደ ማንኛውም ፖለቲካ ንቅናቄ የአማራ ብሄርተኝነት ትርክት እና ፖለቲካዊ ጽንሰ ሃሳብ (theory) ያስፈልገዋል። ይህ intellectual cover (የምሁራን ሽፋን ልበለው?) የአብን ምሁራኖች በደምብ ሰርተውበታል። ዋናው የዚህ ሽፋን መልእክት እንዲህ ነው፤

«የአማራ ብሄርተኝነት የሚያስፈልገው የሌሎች (ያጠቁን) የጎሳ ብሄርተኝነቶችን በኢትዮጵያ ፖለቲካ እንዳያመዝኑ ማድረግ ነው። የአማራ ብሄርተኝነት የሌሎች የጎሳ ብሄርተኝነቶችን balance በማድረግ የአማራንም የኢትዮጵያንም ህልውና ይጠብቃል።»

ማንኛውም ትንሽም ስለፖለቲካ/ታሪክ የሚያውቅ ሰው ይህ ትክርት እጅግ የተሳሳተ እንደሆነ ያውቃል። በርካታ ጎሳዎች ወይንም ክልሎች ባሉባቸው ሀገራት የስልጣን ውድድር በመሃል እና በክልሎቹ እንደሆነ የታወቀ ነው (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/on-nama-strategies.html)። ስልጣን ከምሃሉ (ኢትዮጵያዊነት) ወደ ልልሎች (ጎሳ ብሄርተኝነት) ቁጥር ሁሉም ጎሳ ብሄርተኞች ይጠነክራሉ። የጎሳ ብሄርተኞቹ ከእርስ በርስ ይልቅል የሚሟገቱት ከመሃሉ (ከኢትዮጵያዊነት) ነው። ዋናው አላማቸው መሃሉ ማድከም ነው። በዚህ ጋራ አላማቸው ይተባበራሉ። መሃሉ መንምኖ ሲያበቃው ስልጣን በሙሉ በጎሳ ብሄርተኞች እጅ ይሆናል። ከዛ እነዚህ የጎሳ ብሄርተኞች (ለምሳሌ ህወሓት፤ ኦነግ፤ አብን፤ ወዘተ)እርስ በርስ መደራደር አይችሉም። በጎሳ እና ብሶት የተመሰረቱ ስለሆነ የጋራ ማንነት እና ጥቅም ስለማይታያቸው የሚደራደሩት በባዶ ድምር (zero sum) አቋም ነው። ወጤቱ ጦርነት እና መለያየት ነው የሚሆነው። ሰለባው በየክልሉ የሚኖር አማራ፤ አማራ ክልል፤ መላው ኢትዮጵያዊ ነው የሚሆነው። መሃሉ ሲመነምን እና ጎሳ ብሄርተኞች ሲጠነክሩ ውጤቱ ይህ ነው።

እስቲ በዚህ ረገድ አንዳንድ የአብን አስተሳሰብ የውስጥ ተቃርኖዎች (inconsistencies) እንመልከት። በአንድ በኩል የጎሳ አስተዳደርን (ethnic nationalism) እንቃወማለን፤ የዜጋ ፖለቲካ ነው የሚያስፈልገው ያላሉ። በጎሳ የተደራጀነው ነባራዊው ሁኔታ አስገድዶን ነው እንጂ የጎሳ አስተዳደር ይቁም ይላሉ። የጎሳ አስተዳደር መኖር የለብትም ሲሉ ደግሞ ምክንያቱ አንድ ሀገር በጎሳ ሲስተዳደር ግጭቶች ይበዛሉ ነው። ኦሮሚያ የሚኖሩ አማሮች ይጠቃሉ፤ ነባር እና መጤ ግጭት። ጠረፍ ላይ ግጭት ይኖራል፤ የመሬት ግጭት። በሁሉም የፖለቲካም የማህበረሰብም መስክ ሰው ጎሳውን አስቀድሞ ኢ-ፍትሃዊነት ያራምዳል፤ የፍትህ ግጭት። ለዚህ ነው የጎሳ አስተዳደር የግጭት ምንጭ ነው እና ይቅር የሚባለው። በሌላ አባባል ፖለቲካ በጎሳ ብሄርተኝነት ሲመራ ግጭት ይመጣል ነው። እንዲህ ከሆነ ኢንዴት ነው አብን እንደሚለው የአማራ፤ የኦሮሞ፤ የትግራይ ወዘተ ብሄርተኞች ኢትዮጵያዊነትን አፍርሶ እንደገና በድርድር መገንባት የሚችሉት! የጎሳ ብሄርተኞች መደራደር አይችሉም ተብሏል። አሁን ደግሞ መደራደር ይችላሉ። ሃሳቦቹ ይቃረናሉ።

አልፎ ተርፎ «የኢትዮጵያ የብሄር (ጎሳ) እስር ቤት ናት፤ ሰለዚህም ሁሉም ኢትዮጵያዊ በጎሳው ይሰብሰብ እና እነዚህ የጎሳ ብሄርተኛ ስብስቦች አንዲስ ኢትዮጵያ ይመስርቱ» የሚለው ሃሳብ በ1950/60ዎቹ በማርክሲስት የተማሪ ንቅናቄው የተወለደ ነው። እስከ ዛሬም እነ ህወሓት፤ ኦነግ እና ሌሎች ጎሳ ብሄርተኞች ይህንን አቋም ነው የያዙት። በ1983 ህወሓት ስልጣን ሲይስዝም ይህን ነው አሰምሮ የተናገረው። «እንዳንተ «አንድነቶች» ኣናንተ «አማሮች»፤ እምዬ ኢትዮጵያ ከማለት በጎሳችሁ ተሰብሰቡ እና ተደራደሩ» እያሉ መሃይም ጥሩምባቸውን ይነፉ ነበር። ይህ ሃሳብ ወድቅ መሆኑ የገባን ደግሞ የጎሳ ብሄርተኞች ስብስብ ጦርነት እንጂ ሰላም አያመጣም ነበር። እንሆ ውጤቱን አየነው። ፖለቲካ በጎሳ ሲሆን ጸብ ብቻ ነው የሚኖረው። የጎሳ ፖለቲካ በተፈጥሮ የዜሮ ድምር አስተሳሰብን ይከተላልና።

ስለዚህ አብን ይህንን ታሪክ አውቆ እንዴት ነው ወደ ጎሳ ፖለቲካ እንመለስ የሚለው? አይገባኝም። እኔ እንደሚመስለኝ የሚገባ ብሶት እና ቅሬታቸውን የምሁራን ልብስ (intellectual cover) ለማልበስ ብለው የአብን ልሂቃን እራሳቸውን ወደ የማይሆን ትምዝምዝ ውስጥ አስገበተዋል። የአማራ ብሄርተኝነት በዚህ መልኩ ምንም አይነት ምሁራዊ ድጋፍ የለውም እና ሊፈጥሩ ለት አይችሉም። የብሶት የጎሳ ብሄርተኝነት ነው፤ ሌላ ነገር አንፍጠርለት። አንዴ ይህንን ካመንን በኋላ እንዴት ነው የህዝቡን ብሶት እና በደል በሚጠቅመው ሁኔታ ማስተናገድ የሚቻለውን የፖለቲካ ጥያቄን ለመመለስ እንስራ።

Monday, 14 January 2019

ክርስቲያን ታደለን ተውት፤ የመጠላለፍ ፖለቲካ ባህልን ካላቆምን ሁላችንም አብረን እንጠፋለን!

ሰሞኑን የአብን አመራር የሆነው ክርስቲያን ታደለ የህአዴግ አባል ስለነበር ስሙን ለማጥፋት የሚሯሯጡ የ«አንድነት» ደጋፊዎች አይተናል። እጅግ ያሳዝናል። አሁን ሀገራችን ባለችበት ከባድ የፖለቲካዊ እና ማህበራው ችግር፤ የግብረ ገብ እና ስነ መግባር እጦት፤ አሁን ባለንበት አደገኛ ጊዜ እንዲህ ያነት ርካሽ እና ጎጂ የፖለቲካ ሽኩቻ ሀገራችንን ወደ ማጥፋት ይመራናል።

እረ ከታሪካችን እንማር! የጃንሆይን መግስት የጣሉ ከራሳቸው መንግስት ያሉት አብረው ተስማምተው መስራት ባለመቻላቸው ነው። ደርግ እና ህወሓት በስልጣን ላይ ቆይተው ሀገሪቷን ማተራመስ የቻሉት አንድ አቋም ያላቸው ተቃዋሚዎች አብረው በስነ ስርአት መስራት ባለመቻላቸው ነው። እንደ ቅንጅት አይነት ተስፋ የነበረው ድርጅት/መንገስ የጠፋው አብሮ መስራትን እንደ ሽንፈት ስላየነው ነው። አብሮ ሰርቶ፤ win-win ሁኔታዎች ላይ አተኩሮ፤ long term ጥቅማችን ላይ አቶኩረን ከመስራት ፋንታ በርካሽ እና ጠቃሚ ያልሆነ ግብ-ግብ ላይ ተደምደን ሀገርን ለማፍረስ ሰራን!

ኢትዮጵያ አሜሪካ አይደለችም! እንደነሱ ርካሽ ፖለቲካ ጸቦችን አሽከርክረን ከምርጫ በኋላ የምንስማማበት ሁኔታ የለንም። አሁን ሀገር ግንባታ ላይ ነን እንጂ የአሜሪካ ምርጫ ላይ አይደለንም። ሀገር ግንባታ ርካሽ ሳይሆን ውድ እና ዘላቂ አቋም፤ ግንኙነት እና ግንባታ ነው የሚያስፈልገው (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/02/blog-post_20.html)።

ክርስቲያን ታደለ እንደ ሁላችንም ስህተቶች አድርጓል። ምናልባት ከኢህአዴግ መስራቱ ጠቅሞም ይሆናል (እንደነ ቲም ለማ እና ሌሎች በርካቶች)። አልፎ ተርፎ ክርስቲያን ታደለ ልጅ ነበር አሁንም ነው። «በአንድ ወቅት ክርስቲያን ታደለ የኢህአዴግ አባል ነበር አሁን ግን አቋሙን ቀይሯል» ማለት ተገቢ ነው። የክርስቲያን የሚያራምደውን አስተሳሰብ በሚገባው መግጠም እና መሟገት ተገቢ ነው። ጨዋ እና በቂ አካሄድ ነው። ግን ከዛ አልፎ መሳደብ ነውርነት፤ ርካሽነት እና ግብዝነት ነው። ርህራሄ ማጣት ነው። እነዚህን የሀገራችን ፖለቲካ ለዓመታት እያተራመሱት ያሉት ባህሪዎችን የሚያንጸባርቅ አካሄድ ነው። ዛሬውኑ ይቁም (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/07/blog-post_31.html)!

አሁን በሀገራችን የጎሰኝነት ችግር አለ። የህወሓት እና ሌሎች ነባሮች የሽብር ችግር አለን። የገብረ ገብ እጦት አለን። የመተማመን፤ አርቆ ማየት፤ የራስን የሩቅ ጥቅም መገንዘብ፤ የመራራት፤ የመተባበር ወዘተ ታላቅ እጦት አለን። Emergency ላይ ነን። ታሪካችንን አንድገም። ነውርነትን አቁመን ከጠ/ሚ ዓቢይ ተምረን አውንታዊ መንገድ እንያዝ ብሄ እለምናለሁ።

Friday, 4 January 2019

የአብን መሪዎች ትምክሕተኛ ናቸው!

https://www.facebook.com/seyoum.teshome/videos/1916214778447833/

ሙሉውን ቃለ ምልልስ አላየሁትም ግን… የአብን መሪዎች ክርስቲያን ታደለ እና በለጠ ሞላ ትምክተኛ ነን ሲሉ ይታያል። እስቲ ከዚህ ጥርውን ወገን ልውሰድ…

ባለፉት ረዥም ረዥም ዓመታት የጎሳ ብሄርተኞች አማራ ወይንም «የአማራ ግዥ መደብ» ዋና ጨቋኝ ነው ብለው ሲሰብኩ አብሮ ቋንቋችንን መርዘዋል። «አድሃሪ»፤ «ነፍጠኛ»፤ «ትምክሕርተኛ»፤ «ጠባብ» የሚሉትን ቃላቶች ለአሉታዊ እና ሃሰተኛ ትርክት ተጠቅመዋል። የ«ጨቋኝ ተጨቋኝ» ትርክትን ሽጠውልናል።

የትርክቱን ሃሰትነት ለማስረገጥ እግረ መንገዳችን እነዚህ ቃላቶችን መልሰን ማዳን አለብን። ማሸማቀቅያ እንዲሆኑ መፍቀድ የለብንም። አንዳንድ አማራዎች በተለይም ወደ አብን የሚሳቡት ለረዥም ዓመታት እነዚህን ስድቦች ሲሰሙ ስሜታቸው እጅግ ተነክቷል። የበታችነት እንዲሰማቸው ተደርጓል። ለዚህም ነው አዎ በአማራነቴ እመካለሁ የሚሉት። አላፍርበትም ነው። ካሁን ወድያ ይህ ቃል ኃይል የለውም ነው። ልድገመው፤ ካሁን ወድያ ይህ ቃል ኃይል የለውም ነው።

ይህ ጥሩ ነገር ነው። አብኖች፤ ቀጥሉበት! (ግን የውሃ ልክ አይነት ያልሆነ ነገር ተውው!)

ይህን ሁሉ ስል በአብን የአማራ ብሄርተኝነት እና በበርካታ የሚሪዎቻቸው አቋም ጭራሽ አልሳማማም። ግን ዛሬ እረፍት ልስጣቸው እና ጥሩ ወገኑን ልጥቀስ።

Thursday, 3 January 2019

አንዳንድ ሃሳቦች፤ የአንድነት አና የአማራ ብሄርተኝነት ፖለቲካ

ከአብርሃም ጮራ ገንቢ ጽሁፍ (https://www.facebook.com/abrham.tibebu/posts/10155875239026471) ተከትሎ አንዳንድ ሃሳቦች፤

1. የአንድነት አቋም እና ድርጅት/ደጋፊ/ሰው እንለይ። አቋም እና ሰው እንለይ። እንደማንኛውም ፍሬያማ ውይይት ሃሳብ እና ሰውን መለየት ያስፈልጋል። ይህ ባለመሆኑ አንዳንድ ሰዎች እንደ ግንቦት 7 አይነቱን የማይወዱትን የ«አንድነት ኃይል» ለመኮነን የአንድነት ጽንሰ ሃሳቡንም ይኮንናሉ። እንደሚገባኝ አብን (ለምሳሌ) ሁለት ግብ ነው ያለው፤ 1) የአማራ ህዝብ መብትን ለማስከበር 2) ኢትዮጵያ ዙርያ የጎሳ አስተዳደር የንዲፈርስ እና የዜግነት ፖለቲካ እንዲሰፍን። ስለዚህ አብን በ«አንድነት» ያምናል። ግን አንዳንድ የአብን ደጋፊዎች ግንቦት 7ን ወይንም ሌሎች የማይወዱትን ለመኮነን እራሳቸው የሚያምኑበት የአንድነት ወይንም የዜግነት ፖልቲካን ይኮንናሉ!

2. ሃላፊነት እንውስድ፤ ሁላችንም የአማራ ብሄርተኞችም (ሁሉ አይነት የአማራ ብሄርተኞች) የተወሰነ ዓመታት በፊት የአንድነት ኃይሉ አካል ነበርን። ለምሳሌ የቅንጅት ደጋፊ ነበርን። ወይንም የመኢአድ ደጋፊ፤ ወይንም እድሜአችን ጠና ከሆነ የኢዲዩ ደጋፊ። ወዘተ። ስለዚህ የአንድነት አስተሳሰብንም የአንድነት ድርጅቶችንም እንደ ባይተዋር አንመልከታቸው። እራሳችን ከነሱ ነበርን/ነን።

3. የምዕራባዊያን/ማርክሲስት/ወዘተ ጨቋኝ ተጨቁኝ ውየንን us vs them ሃሰተኛ ትርክት እናቁም! አሁን ያለው የሃሳብ ግጭት ነው። ለምሳሌ፤ የ«አንድነት ኃይሉም» «አማራ ብሄርተኛውም» በአንድነት/ዜግነት ፖለቲካ ያምናል። ያሁኑ ህገ መንግስት ፈርሶ ጎሳ/ዘር የሌለበት ሀገ መንግስት መኖር አለበት ያልሉ ሁለቱም አንድነቶቹም አማራ ብሄርተኞችም። ታድያ ልዩነቱ ምንድነው? የስልት (strategy) ምናልባትም የታክቲክ ነው። አንድ አቋም እያለን በአካሄድ ከሆነ ልዩነታችን መቦጫጨቁ ሁለታችንንም እንደሚጎዳ ግልጽ ነው። ታሪክ መድገም ነው የሚሆነው።

4. ልጅ የሆኑት የአማራ ብሄርተኞች እኛ የ60ዎቹ ተቃራኒ ነን ይላሉ። ግን ይህ us vs them dialectical ትርክት የ60ዎቹ መሰረታዊ አካዬድ ነው!! ከሃሳብ ይልቅ ሰው/ቡደን ላይ ማተኮር ይ60ዎቹ አካሄድ ነው። በስልታዊ ልዩነት መፋጀት የ60ዎቹ «ሌጋሲ» ነው። ፌው ከዛፉ ርቆ አይወድቅም። የአባቶቻን ስህተት አንድገም። የ60ዎቹ የ«ጠላት/ወዳጅ» ፖለቲካ የተጠቀሙት በቀላሉ ተከታዮች በስሜት ለማሰባሰብ ነው፤ እንደ ህወሓት ማለት ነው። ለዚህ ግብ ይህ ጠላት/ወዳጅ ትርክት ማንዴላ እንዳለው ጥይት/መድፍ ነው። ስልጣን ያመጣል ግን ሀገር ያፈርሳል።

5. Counterforce ጥሩ ይመስላል ግን አይሰራም። ነገ አማራ ተደራጅቶ ከነ ህወሓት እጥፍ ድርብ ጠንካራ ሆነ hard እና soft powerኡን በገንዘብ፤ በinfluence፤ በኔትዎርክ ወዘተ ሌሎች ክልሎች ላይ ጫና መፍጠር ይችላል ነው የcounterforce ሃሳብ። ይህን ለማድረግ መሃሉን መያዝ (capture the centre) አለበት ልክ ህወሓት እንዳደረገው። በዛሬ ነባራዊ ሁኔታ አማራም ሌላም የጎሳ ብሄርተኝነት ይህን ማድረግ እንደማይችል መቼም ለሁሉም ግልጽ ይሆናል ብሄ እገምታለሁ። ሌሎች ጎሳዎች ምንም ያህል ከአማራው ደካማ ቢሆኑም ይህን አይፈቅዱም። ሁከት እና ሽብር ይሻላቸዋል። አማራው ይበልጥ ለአማራ ብቻ በቆመ ቁጥር እነሱም ወደ ራሳቸው ይሸገሸጋሉ። ጠንካራ የአማራ ብሄርተኝነት የአማራ ክልልን ልዋላዊነት ያስከብራል ብዬ አምናለሁ። ግን ከሌሎች ጎሳ ድርጅቶች ጋር መስማማት አይችልም።

6. ህወሓት ከሌሎች ጎሳዎች ጋር መተባበር የቻለው ለምን አማራ ብሄርተኛው አይችልም ብላችሁ ትጠይቁ ይሆናል። ህወሓት መቼ ቻለ! ለጊዜው (27 ዓመት) አማራን ጥላት በማድረግ ጎሰኝነትን በማስፈን ከጎሰኞች ጋር ህብረት ፈጠረ። በሌላው በኩል ጸንፈኛ ጎሰኞች እንዳይመጡብህ እጠብቅሃለው ብሎ ሌላውን በፍርሃት ያዜ። ግን ሁሉም አሻጥር የማይሆን ከጥላቻ ወይንም ከአሉታዊነት ውጭ የሌላው መሰረት ነበር። ዛሬ ጠንካራ አማራ ብሄርተኛው ይህን ላድርግ ቢል ማን እንደሚተባበረው አይታየኝም።

7. በአጭሩ ጠንካራ አብን (የዛሬው ሳይሆን እንደሚፈልገው ስራውን ሰርቶ የጠነከረ እና የአማራ ክልል ሙሉ ድጋፍ ያለው) ከሌሎች የጎሳ ድርጅቶች ጋር መወየየት አይችልም። የጎሳ ስብስብ ተወያይቶ መስማማት አይችልም። ሁልጊዜ ወደ ግጭት ያመራል። ምርጫው ሀገሪቷን መከፋፈል ነው የሚሆነው። ይህም በብዙ ደም ነው የሚካሄደው ብየቦታው minorityዎች ወደ «ቦታቸው» መመለስ ስለሚኖርባቸው።

8. በህብረ ጎሳዊ ሀገር force/counterforce በጎሳዎች መካከል ቀውስን ነው የሚያመጣው። ስንሰ ሃሳቡን ትተን empirically በኢትዮጵያም አይተነዋል እያየነው ነው። በህበረ ጎሳዊ ሀገር ታላቁ force/counterforce በመሃሉ እና በጎሳዎቹ መካከል ያለው ነው። መሃሉ በጠነከረ ቁጥር ሰላም እየሰፈነ ይመጣል ጎሳዎችን አለፍላጎታቸው ካልጨፈለቀ ድርስ። ጎሳዎቹ እየጠነከሩ መሃሉ በላላ ቅጥር ጎሳዎቹ እርስ በርስ ያላቸው ልዩነት እየከረረ ይሄዳል ማለት ነው። ልዩነታቸው ጨመረ አንድነታቸው ቀነሰ። ይህ የግጭት መንስኤ ነው። አንዱ ጎሳ ከሌላው ምንም ያህል ቢጠነክር በኃይል ይሁን በድርድር ሰላምን ሊያመጣ አይችልም።

9. ስለዚህ አብን ለሌሎች ጎሰኞች counterforce መሆን ለግቤ ይጠቅማል ብሎ ማሰብ የለበትም። ለኔ ዋናው የአብን ስትራቴጂካል ጥቅም (ሌሎች ቢኖሩም) የአማራ ክልልን ከህወሓት ናፋቂዎች፤ ክሙስና፤ ከሞራል ዝቅተት ወዘተ ለማዳን መስራት ነው። ያለውን የአማራ ብሄርተኝነት ስሜትን ወደዚህ አይነት አውንታዊ አቅጣጫ ማሰማራት ነው። አማራ ክልልን rehabilitate ማድረግ ነው።

10. እንጂ አብን የአማራ ብሄርተኝነትን አስፋፍቼ የአንድነት ፖለቲካን አጥፍቼ እንደገነ ገነባለሁ ከሆነ ለአማራ ህዝብም ለሁሉም ቀውስ ነው የሚያመጣው።

11. የአማራ ብሄርተኝነትን እንደ መሳርያ ተጠቅሜ በኋላ ተወዋለሁ ማለትም አይቻልም! አንዴ የፖለቲካ ውጤት ካመጣ ማንም ፖለቲከኛ አይተወውም። «ሱስ ይሆናል»! ይህ መቼም የታወቀ የፖለቲካ ሃቅ ነው።

12. የአንድነት ፖለቲካ መሰረታዊ ችግሩ የመጠላለፍ ፖለቲካ (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/09/blog-post_21.html) ነበር አሁንም ነው። በጃንሆይ ዘመንም መንግስታቸው ውስጥ የነበረው የእርስ በርስ ሹኩቻ ነው መንግስታቸውን አድክሞ ለውጦች አንዳያደርግ እና እንዲፈርስ ያደረገው። የተማሪ ንቅናቄውንም የፈጠረው። ከዛ ኢዲዩ፤ መድህን፤ ግራኞቹ (ኢህአፓ፤ መኢሶን፤ ወዘተ)፤ መኢአድ፤ ቅንጅት ወዘተ ቁም ነገር ላይ መድረስ ያልቻሉት በመጠላለፍ ፖለቲካ ባህል ምክንያት ነው በመሰረቱ። ይህ ችግር ግን የአንድነት ወይንም የዜግነት ፖለቲካ ርዕዮት ዓለም ሳይሆን የፖለቲካ ባህል ችግር ነው።

13. በሁለተኛ ደረጃ ነው የነ ቅንጅት ችግር የ«ነፍጠኛ ነህ» ክስ። ይህን ክስ ለማስቆም እና ከራሱ የጎሳ መጨፍለቅ ሃሳብ ለማውጣት ብሎ ነው የአንድነት ፖለቲካው አማራ ያልሆኑትን በተጨማሪ ማቀፍ የፈለገው። ለመድገም ያህል ሁለት ምክንያት፤ 1) አማራ ብቻ ነህ እናይባል እና 2) ኢትዮጵያ multicultural መሆን የለባትም የሚሉትን ከማህሉ ለማውጣት። ግን ይህን በማድረግ፤ ለምሳሌ መድረክን በመፍጠር፤ የአንድነት ኃይሉ የተወሰን መሻሻል ቢያሳይም መጠንከር አልቻለም። ለምን፤ ከላይ ያልኩት መሰረታዊው የመጠላለፍ ፖለቲካ ባህል ስላለቀቀው። ያበደምብ address አልተደረገም።

14. ታድያ ለምንድነው እነ አብን፤ ህወሓት እና ሌሎች የጎሳ ፓርቲዎች ይህ የመጠላለፍ ፖለቲካ ባህል የማያጠቃቸው? ያው ጎሰኝነት ስሜታዊ አንድነት ስለሚያመጣ ትብብርን ይጨምራል፤ የታወቀ ነገር ነው። የጎሰኝነትን ግን ትክክለኛ ጽንሰ ሃሳብ አያደርገውም!! የጎሳ ፖለቲካ ድርጅት በ mobilization ዋና ቢሆንም ለጭኮና እና ግጭትም ዋና ነው። ህወሓት መጀመርያ የማይስማሙትን ትግሬዎች አጠፋ። በኃይለ ጎሳ ትግራይን ተቆጣጠረ ጠላት አለህ ብሎ እይሰበከ። ስለዚህ ጎሰኝነት ለፖለቲከኞች attractive ቢሆንም መጨረሻ ላይ ግጭት ነው የሚያመጣው። ስለዚህ የጎሳ ፖለቲካ ድርጅቶች እንደ አንድነት ኃይሎች ባይደነባበሩም ጥሩ አያደርጋቸውም። የአንድነት/ዜግነት ፖለቲካ ከባድ ቢሆንም ለሰላም ግዴታ ነው። ለዚህም ነው አብን የዜግነት ህገ መንግስት እንደ ግብ ያስቀመጠው።

Monday, 15 October 2018

On NAMA Strategies

One of the National Movement of Amhara's (NAMA) strategies seems to be to out-ghetto Oromo nationalists, so to speak. That is, to demonstrate political positions and attitudes that are as radical or even more radical than Oromo nationalists. Simple examples - NAMA leadership and intellectuals have made statements in support of Article 39 and of maintaining ethnic identification on kebele id cards. And apparently at a recent NAMA meeting, supporters publicly voiced the idea of evicting Oromos living on Oromia zones in Amhara Region.

The idea behind this strategy, it seems to me, is that taking extreme positions, which, by the way, have no acceptance from the Amhara masses, will help neutralize Oromo and other ethnic nationalists by restoring the political balance. The NAMA view is that Oromo nationalists have been 'coddled' for too long and now have too much political power now, and one of the ways for NAMA to counteract that is by showing strength through extremism. Basic tit-for-tat strategy.

The problem with this is that it is based on an erroneous and simplistic understanding of the phenomenon of ethnic nationalism in a multi-ethnic nation. The goal of ethnic nationalism is to tear away at the centre, weaken it, and take power away from it to the periphery, which is various ethnic nationalisms. Adding 'another' ethnic nationalism to this actually further weakens the centre and strengthens all ethnic nationalist movements.

A further factor that NAMA doesn't seem to consider is the asymmetric nature of ethnic relations in Ethiopia. The Amhara live in large numbers in various regions, while the Oromo do not.

Given this, Oromo nationalists would much rather have a weak or empty centre and deal with a strong Amhara nationalist movement. This is their perfect scenario, in which all Oromos, including moderate ones, will congregate to Oromo nationalism, making it the only game in Oromia, so to speak. They will negotiate tit for tat agreements with Amhara nationalism and have their Oromo homeland.

What about issues that Oromo nationalists and Amhara nationalists do not agree on, such as Amharas in Oromia, and the case of Addis Ababa? With all Oromos on board, Oromo nationalists will not give an inch on this, and there will be conflict, either overt or covert. The main victims, given the population distribution I mentioned above, will be Amharas and other ethnic groups in Oromia and in Addis Ababa. And if NAMA has a vision of being able to carry out a TPLF 2.0 and forcing itself on the whole country, well, I think we all realize how realistic that is.

Now, I think we should take a step back and ask ourselves 'why'. Why does NAMA exist and why does it take the positions and attitudes in does? In order to reach any kind of understanding and solution to the issues at hand, this question has to be the focus. As I've written about this in my blog, for me, there are two major reasons: 1) The upheaval and resulting weakness of Ethiopian nationalism (or 'the centre') over the past 50 years, and 2) accumulated resentment for the treatment of the Amhara, including by Amhara 'traitors', over the past 27 years, and the resulting grievance and inferiority complex. NAMA is simply an outgrowth of this. The second factor we can do little about - time will heal wounds. But the first we must work hard with all our might to correct, as fixing that - strengthening the centre tangibly via political parties and institutions - is a sine qua non for the survival of Ethiopia.

Monday, 17 September 2018

Centre and periphery in Ethiopia

There seems to be a perception among some elements in the Amhara Nationalism movement that if the Amhara manage to mobilize into a force more powerful than the Oromo and other ethnic movements in the country, the current ethnic imbalance (against the Amhara) will be corrected, resulting in a beneficial arrangement for the Amhara as well as all of Ethiopia.

The assumption here is that a nation that consists simply of a political balance between ethnic groups is a viable nation. This is of course a basic error. It is an error, by the way, that has been propagated by ethnic nationalists, as we've seen in Ethiopia for over 40 years, that is is possible to create a nation out of inter-ethnic negotiation.

But this is not possible. Ethnic political movements naturally devolve politics into a zero-sum game. They capture all political, economic, and social competitions and force them into this zero-sum game. The result is perpetual conflict.

We know this not only in theory, but in examples around the world, and most importantly, in Ethiopia over the past 27 years. Issues such as political power, border, citizen and group rights, security, etc. have all been sources of conflict and will continue to be so as long as ethnicity is the main political driver.

Around the world, we see that multi-ethnic nations are careful not to as much as possible institutionalize ethnicity. They institutionalize language, culture, regional rights, etc., sometimes in an effort to indirectly achieve ethnic rights, but they never directly institutionalize ethnicity because the resulting conflicts are well known.

So in the case of Ethiopia today, let us assume that the Amhara create a movement stronger than any ethnic movement in Ethiopia. At the negotiating table or the battlefield, this movement will be capable of overpowering others, but at what cost. Will it be able to regain territories such as Welqait by negotiation or force? Will it be able to protect Addis Ababa from Oromo ethnic nationalism by negotiation or force? Will it be able to protect Amharas outside Amhara Region by negotiation or force?

The answer is obviously no. Why? The answer is simple. All the other ethnic movements will obviously demand the same rights (or more rights) as the Amhara movement. Why would they settle for less? So if the Amhara want the return of Welqait, Tigray will resist. No amount of ethnic to ethnic negotiation will work. So the only path will be force. If the Oromo insist on Amharas in Oromia having second class citizenship, what can the Amhara do but do the same to Oromos in Amhara? Will they both be able to agree to treat each others 'citizens' like their own? No, the Oromo nationalists are interested in nation-building, so they will enforce Oromocization. What can the Amharas do except tit-for-tat? Or else resort to force.

So it is a fallacy to assume that a strong Amhara movement will do well at the negotiating table. It will not. It may do well on the battlefield, however. It might be able to, like the TPLF, exert itself on others by force. But I assume we all know that in the long run this will be against the interests of the Amhara and all of Ethiopia.

These examples illustrate clearly that it is impossible to achieve a decent outcome - a viable nationa- with ethnic-to-ethnic negotiation. What is possible to achieve is a perpetual zero-sum game and perpetual conflict. That is why it is impossible to create a nation out of a political negotiation between ethnic groups.

In order to have a viable nation, one needs a centre. Anyone who has read any Ethiopian history and politics knows the concept of centre and periphery as it applies in Ethiopia. The 'centre' is the political constituency that, to put it simply, identifies as Ethiopian first and foremost. Its other identities, such as ethnicity, are secondary. This centre is an integrated political constituency created by and with a centuries old history of integration and assimilation. The 'peripheries' are those constituencies which have been less integrated and therefore have somewhat separate political identities from the centre. The ethnic nationalisms in Ethiopia are such examples.

There is always a tension between the centre and periphery. Many say that one of the reasons the Haile Selassie government eventually fell was that it 'centralized' too much. In other words, it gave to much power to the centre, which resulted in rebellion from the periphery. The Dergue regime continued this mistake, and the resulting revolution brought about a violent backlash that took Ethiopia to the opposite extreme, where all power, in theory, rests in the periphery, with the centre being nothing but a negotiated settlement by the peripheries.

So what Ethiopia needs today is to restore the balance not between ethnic groups, but between the centre and the periphery, the centre being "Ethiopianism", and the periphery being ethnic nationalism. The centre needs to get stronger so that it can resist the centrifugal force of the peripheries pulling at it. This will result in less conflict as well as more representative government, in the sense that not only ethnic rights but all rights will be respected. Human rights will no longer be steamrolled in favour of ethnic rights.

What does this mean for the Amhara? Well, as most Amhara nationalists acknowledge, the interests of Ethiopianism is for the most part aligned with the interests of the Amhara. For example, a citizen-based instead of ethnicity-based constitution is in the interests of both the centre and of the Amhara. Since the interests of the centre and the Amhara are aligned, if the Amhara line up to strengthen the centre vis a vis the periphery, they will by default have defended the interests of the Amhara.

Let me offer some practical examples. One of the interests of the Amhara is enforcing the right of all Ethiopians to live as equals in any region in Ethiopia. In a nation of peripheries, this will never happen, as I explained above. But if the centre is strong, this will happen. Because not only Amharas, but all others who have this in their interests will together demand equality of citizenship. Thus, not only Amharas, who say, are 30% of the population, but vast numbers from other ethnic groups will together, as Ethiopians, demand this right. This will make it impossible for those peripheries who are against this to resist, because the demand is not being made by other ethnic groups, but by the centre.

Recall that the victims of the recent ethnic cleansing around Addis Ababa were from at least three different ethnic groups. With a weak centre, these three ethnic groups would be separately advocating for the rights of their members. But a strong centre would result in a far more powerful united front.

Another example would be the question of Wolqait. Perhaps the most effective route to liberating Wolqait from being part of ethnic Tigray is to restructure federalism away from ethnic into regional federalism. This restructuring can only be done by a strong centre, since there will be no coalition of ethnic groups willing to do this. So again, the Amhara, by reinforcing the centre, will strengthen it to the extent that it will be able to peacefully negotiate such a change with the peripheries.

The centre is a powerful force. This is why throughout Ethiopian history, as we all know, most political forces, even those which started out as peripheral liberators, wanted as the final prize to get a hold of the centre. From ancient history, to the present, this story has repeated itself. Amhara nationalists would do well to review this history. It does not make sense to retreat to the periphery when ones interests are best served by bolstering the centre and ensuring its interests align with yours.

Thursday, 23 August 2018

ስለ አማራ ብሄርተኝነት ንቅናቄ ልሟገት

እስቲ በጠ/ሚ አብይ የተለምዶ አካሄድ (http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/08/blog-post_10.html) ልጀምር… የድሮ ንጉሦቻችን ታላቅ ውሳኔዎች ለመወሰን ዘንድ አማካሪዎቻቸውን ሰብስበው ጉዳዩን እየገለባበጡ ከጫፍ እስከ ጫፍ ተሟገቱበት እና ፈትሹት ይሏቸው ነበር። አማካሪዎቻቸው ሁሉንም የሚቃረኑትን ሀሳቦችን ወክለው እርስ በርስ ተከራክረው አሸናፊውን (አሸናፊዎቹን) ለንጉሡ ያቀርባሉ። ንጉሡ ይህን መረጃ ተጠቅመው ይወስናሉ። ይህ ትውፊታችን ነው።

በአማራ ብሄርተኝነት ፅንሰ ሃሳብ አልስማማም። ሆኖም ሃሳቡን በሚገባው ለመረዳት እና ለመፈተሽ ሃሳቡን ደፌ ለመሟገት እወዳለሁ። በአማራ ብሄርተኝነት እና ኢትዮጵያዊ ብሄርተኝነት ያለው ውይይት ትንሽ የረከሰ ነው ማለት ይቻላል። ውይይትም ማለት አይችላልም። በስድብ፤ ዘለፋ እና በመግባባት እጦት የተሞለ ነው። አንዱ ወገን (እዚህ ላይ እራሴን አካትቼ ነው የምናገረው) ለሌላው ወገን አይቆረቀሩምጅ("empathy" የለም)። የዚህ ጽሁፍ አንዱ አላማ ይህንን ለማስተካከል ነው።

ሌላው አላማ ይውይይት ነጥቦቹን ለማጠንከር ነው። ይህን ማድረግ የሚቻለው የሌላውን ወገን ክርክሮች ስንመለከት ጠንካራ ጎኑን (http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/03/blog-post_21.html) በማየት ነው። ፉክክር ላይ ደካማ ጎን ላይ እናተኩራለን። ገምቢ ውይይት ላይ ግን ጠንካራ ወገን ላይ ነው ማተኮር ያለብን። ስለዚህ ከአማራ ብሄርተኝነት መከራከርያ ነጥቦቻቸው ደካማ ወይንም ስሜታዊ ወይንም መሰረት የሌላቸውን ነጥቦች ትተን ምክንያት እና አቅም ያላቸውን ነጥቦች ማየት ይገባል።

ክዚህ ጽሁፍ ልመልሰው የምፈልገው ጥያቄ ይህ ነው፤ « ለመን በአማራነት መደራጀት አስፈለገ በኢትዮጵያዊነት መደራጀት አይሻልም ወይ?»። ለዚህ ጥያቄ አጭር መልሱ ይህ ይመስለኛል፤

1. የጎሳ ብሄርተኝነት አሁንም በኢትዮጵያ ዙርያ ሰፍኗል እያደገም እያለ ነው እነ ጠ/ሚ አብይ ለመቀነስ ምንም እየሞከሩ ቢሆንም። የጎሳ ብሄርተኝነት በደምብ ያልነገሰው ቦታ የአማራ ክልል ነው። ሌሎች ክልሎች በሙሉ ፖለቲካቸውን በጎሰኝነት እና ጎሰኝነት ብቻ አደራጅተዋል።

2. የዛሬው ሁኔታ ይህ በመሆኑ እና ሀገሪቷ ለ27 ዓመት በጎሳ አስተዳደር ፕሮፓጋንዳ መሞላቱ ለአማራው ህልውና እና ጠቃሚ ስልት (strategy) ሲባል ለአማራው በጎሳ ብብሄርተኝነት መልክ መደራጀት ይመረጣል በኢትዮጵያዊነት ወይንም አንድነት ከመደራጀት ይልቅ።

3. የአማራ ህዝብ ላለፉት 27 ዓመት ስለተጨቆነ እና የሀገራዊ ብሄርተኝነት ራዕይ አልሰራም የሚል አመለካከት አንዳንዱ ላይ ስላለ የአማራ ህዝብ የሀገራዊ ብሄርተኛ የሆኑት ድርጅቶችን ደግፍ ቢባልም በሙሉ ልቡ አይደግፍም።

4. ሀገሪቷ በጎሳ ብሄርተኝነት ስለጥለቀለቀች ከአማራ ውጭ ለሀገራዊ ብሄርተኝነት ያለው ድጋፍ እጅግ ዝቅተኛው ነው የሚሆነው። የነ ለማ ቡድን ኢትዮጵያ ብሄርተኛ ቢሆንም ፖለቲካ ውድድር ቢካሄድ (እንደ ምርጫ) የኦሮሞ ብሄርተኞች በቀላሉ እነ ለማ ቡድንን ያሸንፏቸዋል። ሰለዚህ በመጨረሻ የሀገራዊ ብሄርተኛ ፓርቲዎች ከአማራ ውጭ ኢሚንት ድጋር ይኖራቸዋል በአማራ ክልል ደግሞ ደካማ ድጋፍ ይኖራቸዋል። ስለዚህ ሀገር ዙርያ ሲደመር የኢትዮጵያ ብሄርተኝነት ንቅናቄው ደካማ ይሆናል ከጎሳ ብሄርተኝነት አንፃር። የጎሳ ብሄርተኝነት በደምብ አይሎ አሸናፊ ሆኖ ይገኛል።

5. ይህ ብዙ ድጋፍ የሌለው የኢትዮጵያ ብሄርተኝነት ፓርቲ የኢትዮጵያ ብሄርተኝነትን የሚደግፈው ህብረተሰብ ከነ አማራውን በሚገባው መወከል አይችልም ኃይሉ ከጎሳ ብሄርተኞች እጅግ ደካማ በመሆኑ። በድርድር ጠረጵዛ፤ ፓርላማ፤ ወይንም በፖለቲካ ኃይል ሙግት የሀገራዊ ፓርቲው ይጨፈለቃል።

6. ገን አማራው በአማራ ብሄርተኝነት ስር ከተደረጀ ለአመታት የተከማቸውን ብሶት እንደ ኃይል ተጠቅሞ ጠንካራ አማራውን በማንኛውም ደረጃ መወከል የሚችል ድርጅት ይገነባል። አሁን ባለው የጎሳ ብሄርተኝነት ያጥለቀለቀው የሀገራችን የፖለቲካ ሁኔታ የአማራ ህዝብን የብሶት ስሜት እንደ ኃይል ተጠቅሞ ጠንካራ እና ቋሚ ድርጅት ማቋቋም ለአማራው ህልውና ግዴታ ነው።

7. ጠንካራ የአማራ ፓርቲ ከተቁቁመ ሌሎች የጎሳ ፓርቲዎችን በኃይል ሚዛን ይይዛቸዋል። ምክንያቱም የአማራ ብሄርተኛ ፓርቲው የጎሳ ፓርቲ ቢሆንም አማራ ጎሰኝነት በባህሪው ከኢትዮጵያ ብሄርተኝነት የተቆራኘ ስለሆነ። በዚህም ብምክንያት የአማራ ብሄርተኝነት ፓርቲው ከክልል ውጭ ላሉት አማሮች ያገለግላል።

እኔ እንደሚመስለኝ የአማራ ብሄርተኝነት ንቅናቄ መኖር ምክንያት ባጭሩ ይህ ነው።

እስካሁን ባየሁት የተለየዩ ሰዎች አስተያየት ሌሎች የክርክር ነጥቦች ይነሳሉ። ለምሳሌ «አምራ ከሁል ተጨቁኗል»፤ «ሌላው ሲደራጅ ልምን አማራ ይጠየቃል»፤ «በአማራ ብሄርተኝነት ምን አገባችሁ»፤ «ኢትዮጵያዊ ድርጅቶች በአማራ ትከሻ ላይ ነው የተቁቁሙት»፤ «የአንድነት ኃይሎች አማራን ዘርፈውታል ነግደውታል»፤ «የአንድነት ኃይሎች ሌቦች ናቸው» ወዘተ። እነዚህ ስሜታዊ፤ ከመሰረተ ጉዳዩ ውጭ፤ ወይንም ሃሰት የሆኑ የክርክር ነጥቦች ስለሆኑ አልተጠቀምኳቸውም ክርክሩን ያደክማሉ እና።

ስለዚህ የአብን ከአንድነት ይልቅ በአማራነት መደራጀት ምክንያት እንዲህ ነው። እስቲ ህልችሁም በሁለቱም ወገን ያላችሁ ይህን አንብቡ እና እናንተም ከአቋማችሁ ተቃራኒ የሆነውን ወገን ይዛችሁ መከራከር ሞክሩ። እንዲህ እያደረግን ወደ መስማማት ወይንም በሰላም ላለመስማማት ደረጃ (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2016/10/blog-post.html) እንደርሳለን ብዬ እገምታለሁ።

Monday, 20 August 2018

ከሰው ማንነት ጋር መከራከር ያስቸግራል

ድሮ ከኤርትራዊያን፤ ትግራይ፤ ኦሮሞ ብሄርተኞች ጋር ስንከራከር እንዲህ አይነቱ ነጥቦችን እናነሳ ነበር፤

  • ሁላችንም ኢትዮጵያዊ ነን ማንም ከማንም በላይ አልተጠቀመም አልተጨቆነም
  • መንግስት በጎሳ ወይም ብሄር አድሎ አድርጎ አያውቅም
  • ከሁሉም ጎሳ የፖለቲካ መሪዎች አሉ ታላላቅ መሪዎቻችን ብዙ የተለያየ የጎሳ ደም አላቸው
  • የሁላችንም ጥቅም አብሮ ከመሆን የተያያዘ ነው
  • ጎሰኝነት የጋራችንንም የያንዳንድ ጎሳችንንም ጥቅም ይጎዳል ግጭት እንዲሰፍን ያደርጋል
    ወዘተ

እነዚህን አይነት ፍሬአማ ነጥቦች ላይ ከተወያየን ብኋላ ሁልጊዜ መጨረሻ ላይ ወደ አንድ ነጥብ እንመለሳለን። ኤርትራዊያኖች «እኛ ኤርትራዊያን ነን ኢትዮጵያዊ አይደለንም» ትግራዮውቹ «እኛ መጀመርያ ትግራይ ነን» ኦሮሞ ብሄርተኞች «እኛ ኦሮሞ ነን ኢትዮጵያዊ አይደለንም» ብለው ውይይታችንን ያቆማሉ። የአባባላቸው ትርጉም ግልጽ ነበር፤ ማንነታችን ይህ ነው እና ስለ ማንነታችን ምንም ማለት አይቻልም ነው። ጉዳዩ ሌላ አይደለም፤ ጥቅም እና ጉዳትም አይደለም፤ «ማንነት» ነው።

እንዲሁም አሁን ከአማራ ብሄርተኝነት ደጋፊዎች ይህንን ነው የማየው። ባለፉት 45 ዓመት የፖለቲካ ችግሮቻች (http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/07/blog-post_15.html) ምክንያት የተወሰነው የአማራ ህብረተሰብ ውስጥ አዲስ የአማራ ማንነት (http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/08/blog-post_17.html) ተፈጥሯል። ይህ ማንነት የአማራ ብሄርተኝነት ንቅናቄ መሪ @  የጻፉት በደምብ የሚገልጸው ይመስለኛል፤

«አማራ ነኝ ፣ አማራ ነን ፤ እንደአማራነት የተሰነዘረብኝን ጥቃት በአማራነት ተደራጅቼ እመክታለሁ ፤ በዚህም ህልዉናዬን፣ ፍላጎቶቸንና ዘላቂ ጥቅሞችን አስከብራለሁ»
(https://www.facebook.com/photo.php?fbid=1934811083224914&set=a.308423195863719&type=3)

ጉዳዩ የማንነት ስለሆነ ምንም አይነት «ሎጂካል» ሙግት ማንነትን እንደሚያጣጥል ሊቆተር ይችላል። ውይይት ቶሎ ወደ ቅራኔ ይወሰዳል። ለምሳሌ እንደ እኔ አይነቱ በኢትዮጵያዊነት መደራጀትን የሚያምን «የአማራ ጥቅምን የሚያሟላው በኢትዮጵያዊነት መደራጀት ነው» ብል ለአማራ ብሄርተኛው ማንነቱን የተቸትኩኝ ይመስለዋል እና መልሱ ከጉዳዩ ጋር ሳይሆን ከማንነቱን መከላከል ጋር የተያያዘ ይሆናል። «ይህን ሁሉ ጥቃት ደርሶብን እንዴት በአማራነት አትደራጁ ትላለህ» ይባላል። «ድሮስ እናንተ በኛ ትነግዱ ትጫወቱ ነበር አህን ያበቃል» ይባላል። «ሌሎች የጎሳ ብሄርተኞችን ለምን አትተቹም?» ይባላል። ወዘተ።

የነ ጃንሆይ፤ ደርግ፤ ኢህአፓ፤ መኢሶን፤ መላው አማራ/ኢትዮጵያ፤ ቅንጅት፤ ግንቦት ሰባት ወዘተ ኃጢአቶች በሙሉ በ«አንድነት ድርጅቶች» እና በ«ኢትዮጵያዊነት» ርዕዮተ ዓለም ላይ ይለጠፋሉ! ይህ ሁሉ የማይሆኑ («ኢሎጊካል») መልሶች የሚሰነዘሩት ጉዳዩ በዋናነት የማንነት ስለሆነ ነው።

አንዴ በበሶት እና «ጭቁንነት» የተመሰረተ ማንነት ስር ከሰደደ በሎጂክ የተመሰረተ ሙግት ምንም መቀየር አይቻልም። ወይ ከነሱ ጋር ነህ ወይንም ጠላት ነህ።

እዚህ ላይ አንድ መናገር የምፈልገው ነገር አለ። በነዚህ የአማራ ብሄርተኞች ምንም ምንም አልፈርድም። ያወረስናቸው ኢትዮጵያ እጅግ ህመምተኛ እና ደካማ ናት (አሁንም እንዳ አብይ አህመድ አይነት ጀግና መውለድ ብትችልም)። ያወረስናቸው የፖለቲካ ባህል ጥላቻ የቶሞለው ስልት-ቢስ የሆነ ነው። በጃንሆይ ዘመን በሰላም ነገሮችን ከማስተካከል ሀገሪቷን ወደ ገደል ወሰድናት (http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/07/blog-post_15.html)። ለዚህ ማንም ላይ ጣቴን አልጠቁምም። እንደ በኢትዮጵያዊነት የሚያምን ኢትዮጵያዊ ብሄርተኛ የኔ ጥፋት ነው ብዬ ሃላፊነት እወስዳለሁ። ይቅርታም እተይቃለሁ።

ይህን ካልኩኝ በኋላ የአማራ ብሄርተኞችን እንደ ኦርሞ ብሄርተኞች ተጠንቅቆ መያዝ ያስፈልጋል እላለው። እርግጥ የአማራ ብሄርተኞች በአብዛኛው በጎሳ ብሄርተኝነት አናምንም ስትራቴጂ ነው ወይንም ሌሎቹ በጎሳ ስለተደራጁ ግዴታ ሆኖብን ነው ይላሉ። በኢትዮጵያዊነት እናምናለን ይላሉ። ነገ ህገ መንግስቱ ቢቀየር እኛም በጎሳችን መደራጀት እናቆማለን ይላሉ። አቃፊ ብሄርተኞች ነን ይላሉ።

ሆኖም የጎሳ ማንነት በደምብ ገብቶባቸዋል። መጀመርያ አማራ ነን ቀጥሎ ኢትዮጵያዊ የሚሉ አሉ። ኢትዮጵያዊነት ጠፍቷል የሚሉ አሉ። አንቀጽ 39 ጥሩ ነው የሚሉ አሉ። በመታወቅያ ላይ ጎሳ ቢኖር ጥሩ ነው የሚሉ አሉ። አማራ ብሄርተኛ ያልሆነ አማራ አይደለም የሚሉ አሉ። ወዘተ።

ስለዚህ ይህን ማንነት በዘዴ መያዝ ይኖርብናል። ከሙግት ይልቅ empathy ወይን መቆርቆር ነው የሚያስፈልገው። ከሙግት በፊት መተማመንን መፍጠር ያስፈልጋል (አንድ የሆንን እና የምንተማመን መስሎኝ ነበር ግን ለካ የማላውቀው ብዙ ግጭት እና ቁስል አለ በአምራ ብሄርተኞች እና «አንድነት ኃይሎች»)። ትክክለኛ መተማመን ጋር ከደረስን በኋላ ብቻ ነው ወደ ውይይት እና ሙግት መግባት ያሚቻለው።

የ27 ዓመት ጥቃትን አናጣጥል። የብዙ አማራ «ሞራል» ተሰብሯል። ጥቂት ትግሬ ገዝቶን ነበር ብለው የሚያስቡ ብዙ አሉ። ትክክለኛውን ሚዛናዊውን ግንዛቤ ላይ ከመድረስ በራስ አለመተማመን እና የ«ጭቁን» ስሜት ብዙዎቻችን ላይ አድሯል። ይህን እኔ በበኩሌ አልተገነዘብኩትም ነበር። ምን ያህል ስር እንደሰደደ አልገብኛም ነበር። ድሮ ኩሩ የነበረው አማራ ምን ያህል ሞራሉ እንደተጎዳ እና ወደ ጎሳ ብሄርተኝነት ማዘንበል እንደሚችል አልገባኝም ነበር። አሁን ግን ትንሽ የገባኝ ይመስለኛል። ከተሳሳትኩኝ አርሙኝ።