ሰሞኑን የአብን አመራር የሆነው ክርስቲያን ታደለ የህአዴግ አባል ስለነበር ስሙን ለማጥፋት የሚሯሯጡ የ«አንድነት» ደጋፊዎች አይተናል። እጅግ ያሳዝናል። አሁን ሀገራችን ባለችበት ከባድ የፖለቲካዊ እና ማህበራው ችግር፤ የግብረ ገብ እና ስነ መግባር እጦት፤ አሁን ባለንበት አደገኛ ጊዜ እንዲህ ያነት ርካሽ እና ጎጂ የፖለቲካ ሽኩቻ ሀገራችንን ወደ ማጥፋት ይመራናል።
እረ ከታሪካችን እንማር! የጃንሆይን መግስት የጣሉ ከራሳቸው መንግስት ያሉት አብረው ተስማምተው መስራት ባለመቻላቸው ነው። ደርግ እና ህወሓት በስልጣን ላይ ቆይተው ሀገሪቷን ማተራመስ የቻሉት አንድ አቋም ያላቸው ተቃዋሚዎች አብረው በስነ ስርአት መስራት ባለመቻላቸው ነው። እንደ ቅንጅት አይነት ተስፋ የነበረው ድርጅት/መንገስ የጠፋው አብሮ መስራትን እንደ ሽንፈት ስላየነው ነው። አብሮ ሰርቶ፤ win-win ሁኔታዎች ላይ አተኩሮ፤ long term ጥቅማችን ላይ አቶኩረን ከመስራት ፋንታ በርካሽ እና ጠቃሚ ያልሆነ ግብ-ግብ ላይ ተደምደን ሀገርን ለማፍረስ ሰራን!
ኢትዮጵያ አሜሪካ አይደለችም! እንደነሱ ርካሽ ፖለቲካ ጸቦችን አሽከርክረን ከምርጫ በኋላ የምንስማማበት ሁኔታ የለንም። አሁን ሀገር ግንባታ ላይ ነን እንጂ የአሜሪካ ምርጫ ላይ አይደለንም። ሀገር ግንባታ ርካሽ ሳይሆን ውድ እና ዘላቂ አቋም፤ ግንኙነት እና ግንባታ ነው የሚያስፈልገው (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/02/blog-post_20.html)።
ክርስቲያን ታደለ እንደ ሁላችንም ስህተቶች አድርጓል። ምናልባት ከኢህአዴግ መስራቱ ጠቅሞም ይሆናል (እንደነ ቲም ለማ እና ሌሎች በርካቶች)። አልፎ ተርፎ ክርስቲያን ታደለ ልጅ ነበር አሁንም ነው። «በአንድ ወቅት ክርስቲያን ታደለ የኢህአዴግ አባል ነበር አሁን ግን አቋሙን ቀይሯል» ማለት ተገቢ ነው። የክርስቲያን የሚያራምደውን አስተሳሰብ በሚገባው መግጠም እና መሟገት ተገቢ ነው። ጨዋ እና በቂ አካሄድ ነው። ግን ከዛ አልፎ መሳደብ ነውርነት፤ ርካሽነት እና ግብዝነት ነው። ርህራሄ ማጣት ነው። እነዚህን የሀገራችን ፖለቲካ ለዓመታት እያተራመሱት ያሉት ባህሪዎችን የሚያንጸባርቅ አካሄድ ነው። ዛሬውኑ ይቁም (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/07/blog-post_31.html)!
አሁን በሀገራችን የጎሰኝነት ችግር አለ። የህወሓት እና ሌሎች ነባሮች የሽብር ችግር አለን። የገብረ ገብ እጦት አለን። የመተማመን፤ አርቆ ማየት፤ የራስን የሩቅ ጥቅም መገንዘብ፤ የመራራት፤ የመተባበር ወዘተ ታላቅ እጦት አለን። Emergency ላይ ነን። ታሪካችንን አንድገም። ነውርነትን አቁመን ከጠ/ሚ ዓቢይ ተምረን አውንታዊ መንገድ እንያዝ ብሄ እለምናለሁ።
የሰላም ክፍሌ ይትባረክ ብሎግ፤ ስለ ሀገራችን ኢትዮጵያ ያለኝን ትናንሽ ሀሳቦች በትህትና አቀርባለሁ። ለስሕተቶቼም በቅድሚያ ይቅርታ እጠይቃለሁ
Showing posts with label trust building. Show all posts
Showing posts with label trust building. Show all posts
Monday, 14 January 2019
Tuesday, 25 September 2018
ግንቦት 7 የህዝብ ግንኙነቱን ያጎልብት
ግንቦት 7 የ«ኢትዮጵያዊ ብሀርተኝነት» ዋናው (እክካሁን) የፖለቲካ ድርጅት በመሆኑ ለሀገራችን ህልውና ታላቅ ሚና መጫወት ይኖርበታል። ግን የሚገባውን ሚና ለመጫወት አንድ አንድ ድክመቶቹን ማስተካከል ይኖርበታል።
በሰሞኑ የእውን (real)፤ የዜና እና ማህበራዊ ሚዲያ ግርግር የግንብቶ 7 የህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ድክመቶች ጎልተው የታዩ ይመስለኛል። ድክመቶቹ፤
1. ምንም መልዕክት አያስተላልፍም
2. መልዕክቶች ካስተላለፈም ከተለያዩ ሰዎች ዥንጉርጉር የሆኑ መልዕክቶች ናቸው
3. የሚመጡት መልዕክቶች የድርጅቱን አላማ የሚያደናቅፉ ናቸው
4. አጄንዳ መሪ ከመሆን አጄንዳ ተከታይ ይመስላል (instead of setting the agenda, always in reaction mode)
1. በአሁኑ ዘመን ማንኛውም የለህዝብ አስተያየት የሚያገባው ተቋም ለህዝብ መልዕክቶች ቶሎ ብሎ ማሰራጨት አለበት። በኦነግ አቀባበል ግርግር፤ በቡራዩ ክስተት፤ በአዲስ አበባው የህዝብ አፈሳ ወዘተ ግንቦት 7 በፍጥነት አጫጭር የሆኑ የድርጅቱን አስተያየት እና ግብ የሚያንጸባርቁ መልዕክቶችን ማስተላለፍ ነበረበት ግን አላደረገም። ባለማድረጉ ህዝብ ለመረጃ ወደ ሌሎች ምንጮች እንዲሄድ አድርጓል። ሌሎች ደግሞ በደስታ የማይሆን ፕሮፓጋንዳ ለህዝቡ ያንሰራጫሉ። ይህ ለግንቦት 7 አደጋ ነው።
2. ግንቦት 7 የሚያንስተላለፉት መልዕክቶች ደግሞ የተለያዩ ናቸው። ለምሳሌ እኔ ያነበብቋቸው ከአንዳርጋቸው ጽጌ እና ከነአምን ዘለቀ ትንሽ ተመሳሳይ የሆኑ አለ። ግን ደግሞ ሙሉነህ እዮኤል ስለ ስልክ ጠለፋ የሚያተኩር መልዕክት አስተላለፈ። አንድ official መልዕክት ሊኖር ይገባ ነበር ከዛ ሌሎቹ ያንን ቴማ የሚከተሉ መሆን ነበረበት። ለምሳሌ ዋና ቴማ «ስራችንን በደምብ እየሰራን ነው ተረጋግቶ ስራችንን መቀጠል ነው» ከሆነ ሁሉም መልዕክቶች ይህንን ማንጸባረቅ አለባቸው።
3. የሙሉነህ እዮኤል መልዕክት ጥሩ ነገሩ የድርጅቱ አመራር የተሰሩትን የግንቦት 7 አባላትን ጠየቁ የሚለው ነው። ግን ስለ ስልክ ጠለፋ ያስተላለፈው መልዕክት ከግንቦት 7 አላማ ተጻራሪ ይመስለኛል። አሁን የግንቦት 7 ዋና ስራ አቅም ግንባታ (capacity building) የሆነ ይመስለኛል። ድጋፍ፤ አባላት፤ ገንዘብ እና የሰው አቅም ማጎልበት ነው። ለዚህ ደግሞ ሰውዉ እንዲረጋጋ እና ፖለቲካውን እንዳይፈራ ማድረግ ያስፈልጋል። ሁሉን የጊዜያዊ ክስተቶች (short term events) በቀላሉ እንደወሰዱ እና ከዋና አላማ እንዳያዘናጉ ማድረግ ነው ያለበት። ለምሳሌ ስለ ስልክ ጠለፋ፤ መንግስት ስልክን እንደሚጠልፍ የታወቀ ነው። በተለይም የተቃዋሚ ስልኮችን። ግንቦት 7 ሀገር ውስጥ ሲገባ ይህንን ጠንቅቆ ያውቃል። ገና በርካታ የነባር ኃይል ደጋፊዎች አሉ በመንግስቱ። እነሱም አዲሶቹም ለድህንነት እና ፖለቲካቸው የስልክ ጠለፋን ይፈልጉታል። ስለዚህ የተቃዋሚ ስልክ ተጠለፈ ብሎ መአስደንገጥ አያስፈልግም። ይህ ህዝብን ያስፈራራል መፍራቱ ደግሞ ከግንቦት 7 ፍላጎት የሚጻረር ነው። ግንቦት 7 ከሁሉም ነገር በላይ ዛሬ ህዝቡ ፖለቲካን እንዳይፈራ እና ከሱ ስር እንዲሳተፍ ነው የሚፈልገው። «የሁሉም ስልክ ይጠለፋል እንኳን የነኦነግ ስልክም ተጠለፈ» ማለት ነው። አሁን ወደ ስራችን እንመለስ ነው።
4. ምንም አዲስ ወይንም አስደናቂ ዜና ባይኖርም ግንቦት 7 በየቀኑ የሚዲያ አጄንዳ የሚመራ መልዕክት ማስተላለፍ አለበት። በተለይም ስለ ሰላም፤ ፍቅር፤ መደራጀት፤ ስብሰባ፤ አቅም ግንባታ ወዘተ። እንደዚህ አይነት አካሄድ ግንቦት 7 በህዝቡ እምኔታ እንዲያገኝ ይረደዋል (it breeds familiarity and trust)። ይህ ደግሞ አባላት እና አቅም ለመሰብሰብ አስፈላጊ ነው።
በሰሞኑ የእውን (real)፤ የዜና እና ማህበራዊ ሚዲያ ግርግር የግንብቶ 7 የህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ድክመቶች ጎልተው የታዩ ይመስለኛል። ድክመቶቹ፤
1. ምንም መልዕክት አያስተላልፍም
2. መልዕክቶች ካስተላለፈም ከተለያዩ ሰዎች ዥንጉርጉር የሆኑ መልዕክቶች ናቸው
3. የሚመጡት መልዕክቶች የድርጅቱን አላማ የሚያደናቅፉ ናቸው
4. አጄንዳ መሪ ከመሆን አጄንዳ ተከታይ ይመስላል (instead of setting the agenda, always in reaction mode)
1. በአሁኑ ዘመን ማንኛውም የለህዝብ አስተያየት የሚያገባው ተቋም ለህዝብ መልዕክቶች ቶሎ ብሎ ማሰራጨት አለበት። በኦነግ አቀባበል ግርግር፤ በቡራዩ ክስተት፤ በአዲስ አበባው የህዝብ አፈሳ ወዘተ ግንቦት 7 በፍጥነት አጫጭር የሆኑ የድርጅቱን አስተያየት እና ግብ የሚያንጸባርቁ መልዕክቶችን ማስተላለፍ ነበረበት ግን አላደረገም። ባለማድረጉ ህዝብ ለመረጃ ወደ ሌሎች ምንጮች እንዲሄድ አድርጓል። ሌሎች ደግሞ በደስታ የማይሆን ፕሮፓጋንዳ ለህዝቡ ያንሰራጫሉ። ይህ ለግንቦት 7 አደጋ ነው።
2. ግንቦት 7 የሚያንስተላለፉት መልዕክቶች ደግሞ የተለያዩ ናቸው። ለምሳሌ እኔ ያነበብቋቸው ከአንዳርጋቸው ጽጌ እና ከነአምን ዘለቀ ትንሽ ተመሳሳይ የሆኑ አለ። ግን ደግሞ ሙሉነህ እዮኤል ስለ ስልክ ጠለፋ የሚያተኩር መልዕክት አስተላለፈ። አንድ official መልዕክት ሊኖር ይገባ ነበር ከዛ ሌሎቹ ያንን ቴማ የሚከተሉ መሆን ነበረበት። ለምሳሌ ዋና ቴማ «ስራችንን በደምብ እየሰራን ነው ተረጋግቶ ስራችንን መቀጠል ነው» ከሆነ ሁሉም መልዕክቶች ይህንን ማንጸባረቅ አለባቸው።
3. የሙሉነህ እዮኤል መልዕክት ጥሩ ነገሩ የድርጅቱ አመራር የተሰሩትን የግንቦት 7 አባላትን ጠየቁ የሚለው ነው። ግን ስለ ስልክ ጠለፋ ያስተላለፈው መልዕክት ከግንቦት 7 አላማ ተጻራሪ ይመስለኛል። አሁን የግንቦት 7 ዋና ስራ አቅም ግንባታ (capacity building) የሆነ ይመስለኛል። ድጋፍ፤ አባላት፤ ገንዘብ እና የሰው አቅም ማጎልበት ነው። ለዚህ ደግሞ ሰውዉ እንዲረጋጋ እና ፖለቲካውን እንዳይፈራ ማድረግ ያስፈልጋል። ሁሉን የጊዜያዊ ክስተቶች (short term events) በቀላሉ እንደወሰዱ እና ከዋና አላማ እንዳያዘናጉ ማድረግ ነው ያለበት። ለምሳሌ ስለ ስልክ ጠለፋ፤ መንግስት ስልክን እንደሚጠልፍ የታወቀ ነው። በተለይም የተቃዋሚ ስልኮችን። ግንቦት 7 ሀገር ውስጥ ሲገባ ይህንን ጠንቅቆ ያውቃል። ገና በርካታ የነባር ኃይል ደጋፊዎች አሉ በመንግስቱ። እነሱም አዲሶቹም ለድህንነት እና ፖለቲካቸው የስልክ ጠለፋን ይፈልጉታል። ስለዚህ የተቃዋሚ ስልክ ተጠለፈ ብሎ መአስደንገጥ አያስፈልግም። ይህ ህዝብን ያስፈራራል መፍራቱ ደግሞ ከግንቦት 7 ፍላጎት የሚጻረር ነው። ግንቦት 7 ከሁሉም ነገር በላይ ዛሬ ህዝቡ ፖለቲካን እንዳይፈራ እና ከሱ ስር እንዲሳተፍ ነው የሚፈልገው። «የሁሉም ስልክ ይጠለፋል እንኳን የነኦነግ ስልክም ተጠለፈ» ማለት ነው። አሁን ወደ ስራችን እንመለስ ነው።
4. ምንም አዲስ ወይንም አስደናቂ ዜና ባይኖርም ግንቦት 7 በየቀኑ የሚዲያ አጄንዳ የሚመራ መልዕክት ማስተላለፍ አለበት። በተለይም ስለ ሰላም፤ ፍቅር፤ መደራጀት፤ ስብሰባ፤ አቅም ግንባታ ወዘተ። እንደዚህ አይነት አካሄድ ግንቦት 7 በህዝቡ እምኔታ እንዲያገኝ ይረደዋል (it breeds familiarity and trust)። ይህ ደግሞ አባላት እና አቅም ለመሰብሰብ አስፈላጊ ነው።
Subscribe to:
Posts (Atom)