ባለፈው ጽሁፌ (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2019/03/blog-post_19.html) ግንቦት 7 እና ሌሎች «የዜግነት ፖለቲካ» ፓርቲዎች፤ አዴፓ እና አብን ግቦቻቸው የዜግነት ፖለቲካ እንደመሆኑ ጸጉር መቀንጠስ ትተው መተባበር ቢያንስ አለመጠላለፍ አለባቸው ብዬ ነበር። የሀገራችን ነባራዊ አደገኛ ሁኔታ ስለሚያስገድደን ማለት ነው።
ዋናው ግባችን የዜግነት ፖለቲካ (የዜግነት አስተዳደር ነው)። የጎሳ ፌደራሊዝምን አፍርሰን የብዝሃነት (multicultural and multilanguage) ፌዸራሊዥም ነው የሚበጀን ነው አቋማችን።
የዚህ ግብ ዋና ምክንያት ርዕዮት ዓለማዊ ሳይሆን መረጃ ላይ የተመሰረተ (empirical) ነው፤ የጎሳ ፌደራሊዝም የግጭት መንስኤ መሆኑን ለ28 ዓመት በአምባገነንትም በአንጻራዊ ነፃነትም አይተናል። ሚዛናዊ፤ ለዘብተኛ፤ ዓለም ዙርያ ተሞክሮ ያለው በዜግነት የተመሰረተ ክልሎችን በርካታ መብት የሚጸት ፌደራሊዝም እነዚህን ህልውናችንን ለማጥፋት የደረሱትን ግጭቶች ይቀንሳል። ለዚህ ነው የዜግነት ፖለቲካን የምንፈልገው፤ ግንቦት 7ም፤ አዴፓም፤ አብንም።
ይህን ግብ ለመምታት መደራጀት ግድ እንደሆነ ከምናልባት 50 ዓመታት ብኋላ እየገባን ይመስላል። ገንዘብ እየተሰበሰበ ነው ድርጅት(ቶች) እየተቋቋመ ነው። ይህ ግድ ነው። አሰምርበታለሁ፤ ግድ ነው። አልያ እልቂት ነው የሚጠብቀን።
ግን ወደ ግባችን ስንጓዝ የተለያየ መንገድ እንጠቀም ይሆናል። የተለያየ ስትራቴጂ እና ታክቲክ ማለት ነው። ለምሳሌ፤ አናንዶቻችን ለዘብተኛ አቋም እና በተለይ ለዘብተኛ አነጋገር እና ኮምዩኒካሽን ግድ ነው ጎሰኝነትን ለመቀነስ ብለን እናምናለን (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2019/03/blog-post_15.html)። ሌሎች ደግሞ ጠንቅረን መናገር እና መሟገት አለብን ይላሉ።
ይሁን፤ በዚህ ጉዳይ እንሟገት። ግን ግባችንን አንርሳ። አንጠላለፍ። አንዱ ግድ የሌላውን መንገድ ካልተጠቀምክ አልተባበርህም አይበል። ምን ይደረግ ሰው ነን ፖለቲካ ነው እና አቋም ይለያያል። በፖለቲካ ፍፁምነት የለም።
ግን ትብብር እና አለመጠላለፍ ግድ ነው። አለበለዛ አስፈላጊ የሆኑን ግዙፍ ድርጅቶች እና አቋሞችን ማቋቋም አንችልም፤ ይህ ማለት ግባችን አቅራቢያም አንደርስም፤ ይህ ማለት የጎሳ ፖለቲካ እንደምናየው ሀገራችንን እያቃጠለ ይቀጥላል።
የሰላም ክፍሌ ይትባረክ ብሎግ፤ ስለ ሀገራችን ኢትዮጵያ ያለኝን ትናንሽ ሀሳቦች በትህትና አቀርባለሁ። ለስሕተቶቼም በቅድሚያ ይቅርታ እጠይቃለሁ
Showing posts with label cooperation. Show all posts
Showing posts with label cooperation. Show all posts
Thursday, 21 March 2019
Monday, 17 September 2018
የአዲስ አበባ ህዝብ፤ ፍርሃት እና ህፍረት
ሁላችንም ቄሮ፤ ፋኖ፤ አቢይ፤ ለማ፤ ኦነግ፤ ግንቦት 7 ወዘተ ሲባል ህወሓትን ከስልጣን ማውረድ የተቻለው የ27 ዓመት የተጠራቀመ የግለሰቦች እና የቡድኖች ትግል እንደሆነ እንረሳለን። አንዱ የትግል ዘርፍ ምርጫ 97 ዙርያ በተለይም በአዲስ አበባ የተደረገው ተቃውሞ እና የህዝብ አመጽ ነበር። በዚህ ልጀምርና…
ሁላችንም እንደምናውቀው ለ27 ዓመታት የአዲስ አበባ ህዝብ በፍርሃት ነው የኖረው ማለት ይቻላል። (የብሄር ብሄረሰቦች) ጨቋኝ፤ ገዥ፤ ትምክህተኛ ወዘተ ተብሎ በመንግስት ትርክት ተሰይሟል። ይህ ህዝብ ነገ በጎሳ ብሄርተኞች ተከበን እንወራለን፤ እንገደላለን እና እንፈናቀላለን ብሎ በስጋር ይኖራል። ይህን አይነት ክስተት ደግሞ በተለያየ የኢትዮጵያ ክልሎች ሲከሰቱ አይቷል። አዲስ አበባ ከበየቦታ የተፈናቀሉትን ተቀብሏለችም!
በሌላ በኩል ደግሞ የአዲስ አበባ ህዝብ ይህ በእውነት የተመሰረተ ፍርሃት ምንጭን ለመከላከል ተባብሮ መደራጀት አልቻለም። አዎን በምርጫ 97 ለተወሰነ ጊዜ አሸዋ ላይ ተደራጀ ግን ይህ ወድያው ፈረሰ። አልፎ ተርፎ ህዝቡ ይበልጥ እንዲፈራ እና መደራጀት እንዳይሞክር አደረገ።
ሆኖም የአዲስ አበባ ህዝብ በልቡ መደራጀት እንደሚገባው ያውቃል። የህዝብ ቁጥር እና አቅም እንዳለው ያውቃል። መደራጀት ያልቻለበት ምክንያት የራሱ ድክመት እና ጥፋት መሆኑም በተወሰነ ደረጃ ውስጡ ያውቃል። ጭቆናውን ችሎ መደራጀት እንደነበረበት ያውቃል።
ህወሓት ደጋግሞ እንድተጫወተበትም ያውቃል። ለኔ ስገዱ አለበለዛ ጎሰኞቹን ለቅባችኋለው እያለ ቆዬ። የአዲስ አበባ ህዝብ እራሱን አጠንክሮ ዞርበል ከማለት ፈርተን ዝም አልን። እውነታውን እንመን።
ይህ ነው የአዲስ አበባ ህፍረት የምለው። የተገዛው በትንሽ የምትባል ቡድን (ህወሓት) እንደሆነ ያውቃል። ህወሓት አንድ ለአምስት በሚባለው የቁጥጥር ዘዴ ሲፈጸምበት በራሱ ድክመት እንደሆነ የሚገዛው ህዝቡ አውቋል። ቄሮ እና ፋኖ ሲወራላቸው ዝም ብሎ ቁጭ እንዳለ ያውቃል። ይህ ለአዲስ አበባ ህዝብ ታላቅ የስነ ልቦና ቁስል ሆኗል። የዝቅተኛ መንፈስ እንዲያድርበት፤ አቅም የሌለው እንዲመስለው፤ የተዋረደ እንዲመስለው አድርጓል። ይህ ነው የአዲስ አበባ ህዝብ ሀፍረታችን።
ፍርሃት እና ህፍረት ስላለን ነው በቀደም ኦነግ ወደ አዲስ አበባ ሲገባ ችግሮች የተፈጠሩት። ህዝቡ ፍርሃቱን በእውን አየው። የሚፈራው የሚፈራቸው ሲገቡ ደንግጧል። በሌላ በኩል ደግሞ እንዳልተደራጀ እና አቅሙን እንዳልሰበሰበ ያውቃል እና ታላቅ insecurity ተሰምቶታል። ሰለዚህም ነው በሰንደቅ አላማ እና አርማ ዙርያ ግጭቶች የነበሩት። ከፍርሃት የመነጨ ምላሽ ነው የአዲስ አበባ ውጣቶች የሰጡት።
እዚህ ላይ አንድ aside ያስፈልጋል። መደራጀት ማለት መዋጋት አይደለም። ውግያ እንዳይኖር ጠንክሮ ስልታማ ሆኖ መገኘት ነው። ግዙፍ አቅም እና ስነ ስረዓት ያላቸው የህዝብን አላማ የሚያስፈጽሙ መዋቅሮችን መፍጠር ማለት ነው። እነዚህ መዋቅሮች ብዙ ሚና ሊጫወቱ ይችላሉ። ለምሳሌ በከተማ አስተዳደር፤ በምሃበራዊ ኑሮ ጉዳዎች፤ በጸጥታ ዘርፍ፤ በፍትህ ወዘተ። እነዚህ ህዝብን የሚወክሉ መዋቅሮች ቢኖር ሁሉም የአዲስ አበባ ድርጅቶች በህዝብ ፍላጎት እንዲመሩ፤ ተጠያቂነት እና ግልጸኝነትት እንዲኖር ወዘተ ያደርጋሉ። በአጭሩ ህዝቡን አንድ ገልጽ ላይ ያደርጋል። እነዚህ መዋቅሮች ቢኖሩ ኦነግ ሲገባ ህዝቡ ምንም አይመስለውም ነበር። ምንም አይነት ኃይልን መቋቋም የሚችሉ መዋቅሮች እንዳሉት ስለሚያውቅ። ጭራሽ የኦነግ አርማ ይዞ ለመቀበል ይወጣ ነበር! መደራጀት ይህ ማለት ይህ ነው። በአጭሩ አዲስ አበባ በአዲስ አበባ ህዝብ ፍላጎት እንዲመራ ማድረግ ነው።
ዛሬ የአዲስ አበባ ህዝብ እንደ መላው ኢትዮጵያ ህዝብ በፍጥነት በዚህ መልኩ መደራጀት አለበት። የፖለቲካ ፓርቲ መፍጠር አለበት ወይንም እንደ ግንቦት 7 አይነቱ ጋር ተባብሮ ለአዲስ አበባ መዋቅር መዘርጋት አለበት። ሚዲያ መመስረት አለበት። የባህላዊ ድርጅቶችን በአንድ ጃንጥላ ስር ማሰባሰብ አለበት። ህዝቡ የሚወያይበት መዋቅሮች መዘርጋት አለበት። በጥቅልሉ ህዝቡን በአንድ ገልጽ የሚያደርገው መዋቅሮች እና ድርጅቶች መፈጠር አለበት። ነጻነት ማለት እንደዚህ አይነት የፖለቲካ ሃላፊነትን መወጣት ነው።
ግን በመጀመርያ ፍርሃት እና ህፍረታችንን ማመን አለብን። ይህ መደበቅ የለበትም። ስለዚህ በይፋ ማውራት መቻል አለብን። እውነቱ ከሃሰቱ መለየት አለበት። ይህም በውይይት እና መመካከር ነው የሚመጣው። አንዴ ፍርሃት እና ህፍረታችንን ካመንን በኋላ ወደ መፍትሄ ለመሄድ ይቀለናል።
ሁላችንም እንደምናውቀው ለ27 ዓመታት የአዲስ አበባ ህዝብ በፍርሃት ነው የኖረው ማለት ይቻላል። (የብሄር ብሄረሰቦች) ጨቋኝ፤ ገዥ፤ ትምክህተኛ ወዘተ ተብሎ በመንግስት ትርክት ተሰይሟል። ይህ ህዝብ ነገ በጎሳ ብሄርተኞች ተከበን እንወራለን፤ እንገደላለን እና እንፈናቀላለን ብሎ በስጋር ይኖራል። ይህን አይነት ክስተት ደግሞ በተለያየ የኢትዮጵያ ክልሎች ሲከሰቱ አይቷል። አዲስ አበባ ከበየቦታ የተፈናቀሉትን ተቀብሏለችም!
በሌላ በኩል ደግሞ የአዲስ አበባ ህዝብ ይህ በእውነት የተመሰረተ ፍርሃት ምንጭን ለመከላከል ተባብሮ መደራጀት አልቻለም። አዎን በምርጫ 97 ለተወሰነ ጊዜ አሸዋ ላይ ተደራጀ ግን ይህ ወድያው ፈረሰ። አልፎ ተርፎ ህዝቡ ይበልጥ እንዲፈራ እና መደራጀት እንዳይሞክር አደረገ።
ሆኖም የአዲስ አበባ ህዝብ በልቡ መደራጀት እንደሚገባው ያውቃል። የህዝብ ቁጥር እና አቅም እንዳለው ያውቃል። መደራጀት ያልቻለበት ምክንያት የራሱ ድክመት እና ጥፋት መሆኑም በተወሰነ ደረጃ ውስጡ ያውቃል። ጭቆናውን ችሎ መደራጀት እንደነበረበት ያውቃል።
ህወሓት ደጋግሞ እንድተጫወተበትም ያውቃል። ለኔ ስገዱ አለበለዛ ጎሰኞቹን ለቅባችኋለው እያለ ቆዬ። የአዲስ አበባ ህዝብ እራሱን አጠንክሮ ዞርበል ከማለት ፈርተን ዝም አልን። እውነታውን እንመን።
ይህ ነው የአዲስ አበባ ህፍረት የምለው። የተገዛው በትንሽ የምትባል ቡድን (ህወሓት) እንደሆነ ያውቃል። ህወሓት አንድ ለአምስት በሚባለው የቁጥጥር ዘዴ ሲፈጸምበት በራሱ ድክመት እንደሆነ የሚገዛው ህዝቡ አውቋል። ቄሮ እና ፋኖ ሲወራላቸው ዝም ብሎ ቁጭ እንዳለ ያውቃል። ይህ ለአዲስ አበባ ህዝብ ታላቅ የስነ ልቦና ቁስል ሆኗል። የዝቅተኛ መንፈስ እንዲያድርበት፤ አቅም የሌለው እንዲመስለው፤ የተዋረደ እንዲመስለው አድርጓል። ይህ ነው የአዲስ አበባ ህዝብ ሀፍረታችን።
ፍርሃት እና ህፍረት ስላለን ነው በቀደም ኦነግ ወደ አዲስ አበባ ሲገባ ችግሮች የተፈጠሩት። ህዝቡ ፍርሃቱን በእውን አየው። የሚፈራው የሚፈራቸው ሲገቡ ደንግጧል። በሌላ በኩል ደግሞ እንዳልተደራጀ እና አቅሙን እንዳልሰበሰበ ያውቃል እና ታላቅ insecurity ተሰምቶታል። ሰለዚህም ነው በሰንደቅ አላማ እና አርማ ዙርያ ግጭቶች የነበሩት። ከፍርሃት የመነጨ ምላሽ ነው የአዲስ አበባ ውጣቶች የሰጡት።
እዚህ ላይ አንድ aside ያስፈልጋል። መደራጀት ማለት መዋጋት አይደለም። ውግያ እንዳይኖር ጠንክሮ ስልታማ ሆኖ መገኘት ነው። ግዙፍ አቅም እና ስነ ስረዓት ያላቸው የህዝብን አላማ የሚያስፈጽሙ መዋቅሮችን መፍጠር ማለት ነው። እነዚህ መዋቅሮች ብዙ ሚና ሊጫወቱ ይችላሉ። ለምሳሌ በከተማ አስተዳደር፤ በምሃበራዊ ኑሮ ጉዳዎች፤ በጸጥታ ዘርፍ፤ በፍትህ ወዘተ። እነዚህ ህዝብን የሚወክሉ መዋቅሮች ቢኖር ሁሉም የአዲስ አበባ ድርጅቶች በህዝብ ፍላጎት እንዲመሩ፤ ተጠያቂነት እና ግልጸኝነትት እንዲኖር ወዘተ ያደርጋሉ። በአጭሩ ህዝቡን አንድ ገልጽ ላይ ያደርጋል። እነዚህ መዋቅሮች ቢኖሩ ኦነግ ሲገባ ህዝቡ ምንም አይመስለውም ነበር። ምንም አይነት ኃይልን መቋቋም የሚችሉ መዋቅሮች እንዳሉት ስለሚያውቅ። ጭራሽ የኦነግ አርማ ይዞ ለመቀበል ይወጣ ነበር! መደራጀት ይህ ማለት ይህ ነው። በአጭሩ አዲስ አበባ በአዲስ አበባ ህዝብ ፍላጎት እንዲመራ ማድረግ ነው።
ዛሬ የአዲስ አበባ ህዝብ እንደ መላው ኢትዮጵያ ህዝብ በፍጥነት በዚህ መልኩ መደራጀት አለበት። የፖለቲካ ፓርቲ መፍጠር አለበት ወይንም እንደ ግንቦት 7 አይነቱ ጋር ተባብሮ ለአዲስ አበባ መዋቅር መዘርጋት አለበት። ሚዲያ መመስረት አለበት። የባህላዊ ድርጅቶችን በአንድ ጃንጥላ ስር ማሰባሰብ አለበት። ህዝቡ የሚወያይበት መዋቅሮች መዘርጋት አለበት። በጥቅልሉ ህዝቡን በአንድ ገልጽ የሚያደርገው መዋቅሮች እና ድርጅቶች መፈጠር አለበት። ነጻነት ማለት እንደዚህ አይነት የፖለቲካ ሃላፊነትን መወጣት ነው።
ግን በመጀመርያ ፍርሃት እና ህፍረታችንን ማመን አለብን። ይህ መደበቅ የለበትም። ስለዚህ በይፋ ማውራት መቻል አለብን። እውነቱ ከሃሰቱ መለየት አለበት። ይህም በውይይት እና መመካከር ነው የሚመጣው። አንዴ ፍርሃት እና ህፍረታችንን ካመንን በኋላ ወደ መፍትሄ ለመሄድ ይቀለናል።
Thursday, 23 August 2018
ስለ አማራ ብሄርተኝነት ንቅናቄ ልሟገት
እስቲ በጠ/ሚ አብይ የተለምዶ አካሄድ (http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/08/blog-post_10.html) ልጀምር… የድሮ ንጉሦቻችን ታላቅ ውሳኔዎች ለመወሰን ዘንድ አማካሪዎቻቸውን ሰብስበው ጉዳዩን እየገለባበጡ ከጫፍ እስከ ጫፍ ተሟገቱበት እና ፈትሹት ይሏቸው ነበር። አማካሪዎቻቸው ሁሉንም የሚቃረኑትን ሀሳቦችን ወክለው እርስ በርስ ተከራክረው አሸናፊውን (አሸናፊዎቹን) ለንጉሡ ያቀርባሉ። ንጉሡ ይህን መረጃ ተጠቅመው ይወስናሉ። ይህ ትውፊታችን ነው።
በአማራ ብሄርተኝነት ፅንሰ ሃሳብ አልስማማም። ሆኖም ሃሳቡን በሚገባው ለመረዳት እና ለመፈተሽ ሃሳቡን ደፌ ለመሟገት እወዳለሁ። በአማራ ብሄርተኝነት እና ኢትዮጵያዊ ብሄርተኝነት ያለው ውይይት ትንሽ የረከሰ ነው ማለት ይቻላል። ውይይትም ማለት አይችላልም። በስድብ፤ ዘለፋ እና በመግባባት እጦት የተሞለ ነው። አንዱ ወገን (እዚህ ላይ እራሴን አካትቼ ነው የምናገረው) ለሌላው ወገን አይቆረቀሩምጅ("empathy" የለም)። የዚህ ጽሁፍ አንዱ አላማ ይህንን ለማስተካከል ነው።
ሌላው አላማ ይውይይት ነጥቦቹን ለማጠንከር ነው። ይህን ማድረግ የሚቻለው የሌላውን ወገን ክርክሮች ስንመለከት ጠንካራ ጎኑን (http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/03/blog-post_21.html) በማየት ነው። ፉክክር ላይ ደካማ ጎን ላይ እናተኩራለን። ገምቢ ውይይት ላይ ግን ጠንካራ ወገን ላይ ነው ማተኮር ያለብን። ስለዚህ ከአማራ ብሄርተኝነት መከራከርያ ነጥቦቻቸው ደካማ ወይንም ስሜታዊ ወይንም መሰረት የሌላቸውን ነጥቦች ትተን ምክንያት እና አቅም ያላቸውን ነጥቦች ማየት ይገባል።
ክዚህ ጽሁፍ ልመልሰው የምፈልገው ጥያቄ ይህ ነው፤ « ለመን በአማራነት መደራጀት አስፈለገ በኢትዮጵያዊነት መደራጀት አይሻልም ወይ?»። ለዚህ ጥያቄ አጭር መልሱ ይህ ይመስለኛል፤
1. የጎሳ ብሄርተኝነት አሁንም በኢትዮጵያ ዙርያ ሰፍኗል እያደገም እያለ ነው እነ ጠ/ሚ አብይ ለመቀነስ ምንም እየሞከሩ ቢሆንም። የጎሳ ብሄርተኝነት በደምብ ያልነገሰው ቦታ የአማራ ክልል ነው። ሌሎች ክልሎች በሙሉ ፖለቲካቸውን በጎሰኝነት እና ጎሰኝነት ብቻ አደራጅተዋል።
2. የዛሬው ሁኔታ ይህ በመሆኑ እና ሀገሪቷ ለ27 ዓመት በጎሳ አስተዳደር ፕሮፓጋንዳ መሞላቱ ለአማራው ህልውና እና ጠቃሚ ስልት (strategy) ሲባል ለአማራው በጎሳ ብብሄርተኝነት መልክ መደራጀት ይመረጣል በኢትዮጵያዊነት ወይንም አንድነት ከመደራጀት ይልቅ።
3. የአማራ ህዝብ ላለፉት 27 ዓመት ስለተጨቆነ እና የሀገራዊ ብሄርተኝነት ራዕይ አልሰራም የሚል አመለካከት አንዳንዱ ላይ ስላለ የአማራ ህዝብ የሀገራዊ ብሄርተኛ የሆኑት ድርጅቶችን ደግፍ ቢባልም በሙሉ ልቡ አይደግፍም።
4. ሀገሪቷ በጎሳ ብሄርተኝነት ስለጥለቀለቀች ከአማራ ውጭ ለሀገራዊ ብሄርተኝነት ያለው ድጋፍ እጅግ ዝቅተኛው ነው የሚሆነው። የነ ለማ ቡድን ኢትዮጵያ ብሄርተኛ ቢሆንም ፖለቲካ ውድድር ቢካሄድ (እንደ ምርጫ) የኦሮሞ ብሄርተኞች በቀላሉ እነ ለማ ቡድንን ያሸንፏቸዋል። ሰለዚህ በመጨረሻ የሀገራዊ ብሄርተኛ ፓርቲዎች ከአማራ ውጭ ኢሚንት ድጋር ይኖራቸዋል በአማራ ክልል ደግሞ ደካማ ድጋፍ ይኖራቸዋል። ስለዚህ ሀገር ዙርያ ሲደመር የኢትዮጵያ ብሄርተኝነት ንቅናቄው ደካማ ይሆናል ከጎሳ ብሄርተኝነት አንፃር። የጎሳ ብሄርተኝነት በደምብ አይሎ አሸናፊ ሆኖ ይገኛል።
5. ይህ ብዙ ድጋፍ የሌለው የኢትዮጵያ ብሄርተኝነት ፓርቲ የኢትዮጵያ ብሄርተኝነትን የሚደግፈው ህብረተሰብ ከነ አማራውን በሚገባው መወከል አይችልም ኃይሉ ከጎሳ ብሄርተኞች እጅግ ደካማ በመሆኑ። በድርድር ጠረጵዛ፤ ፓርላማ፤ ወይንም በፖለቲካ ኃይል ሙግት የሀገራዊ ፓርቲው ይጨፈለቃል።
6. ገን አማራው በአማራ ብሄርተኝነት ስር ከተደረጀ ለአመታት የተከማቸውን ብሶት እንደ ኃይል ተጠቅሞ ጠንካራ አማራውን በማንኛውም ደረጃ መወከል የሚችል ድርጅት ይገነባል። አሁን ባለው የጎሳ ብሄርተኝነት ያጥለቀለቀው የሀገራችን የፖለቲካ ሁኔታ የአማራ ህዝብን የብሶት ስሜት እንደ ኃይል ተጠቅሞ ጠንካራ እና ቋሚ ድርጅት ማቋቋም ለአማራው ህልውና ግዴታ ነው።
7. ጠንካራ የአማራ ፓርቲ ከተቁቁመ ሌሎች የጎሳ ፓርቲዎችን በኃይል ሚዛን ይይዛቸዋል። ምክንያቱም የአማራ ብሄርተኛ ፓርቲው የጎሳ ፓርቲ ቢሆንም አማራ ጎሰኝነት በባህሪው ከኢትዮጵያ ብሄርተኝነት የተቆራኘ ስለሆነ። በዚህም ብምክንያት የአማራ ብሄርተኝነት ፓርቲው ከክልል ውጭ ላሉት አማሮች ያገለግላል።
እኔ እንደሚመስለኝ የአማራ ብሄርተኝነት ንቅናቄ መኖር ምክንያት ባጭሩ ይህ ነው።
እስካሁን ባየሁት የተለየዩ ሰዎች አስተያየት ሌሎች የክርክር ነጥቦች ይነሳሉ። ለምሳሌ «አምራ ከሁል ተጨቁኗል»፤ «ሌላው ሲደራጅ ልምን አማራ ይጠየቃል»፤ «በአማራ ብሄርተኝነት ምን አገባችሁ»፤ «ኢትዮጵያዊ ድርጅቶች በአማራ ትከሻ ላይ ነው የተቁቁሙት»፤ «የአንድነት ኃይሎች አማራን ዘርፈውታል ነግደውታል»፤ «የአንድነት ኃይሎች ሌቦች ናቸው» ወዘተ። እነዚህ ስሜታዊ፤ ከመሰረተ ጉዳዩ ውጭ፤ ወይንም ሃሰት የሆኑ የክርክር ነጥቦች ስለሆኑ አልተጠቀምኳቸውም ክርክሩን ያደክማሉ እና።
ስለዚህ የአብን ከአንድነት ይልቅ በአማራነት መደራጀት ምክንያት እንዲህ ነው። እስቲ ህልችሁም በሁለቱም ወገን ያላችሁ ይህን አንብቡ እና እናንተም ከአቋማችሁ ተቃራኒ የሆነውን ወገን ይዛችሁ መከራከር ሞክሩ። እንዲህ እያደረግን ወደ መስማማት ወይንም በሰላም ላለመስማማት ደረጃ (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2016/10/blog-post.html) እንደርሳለን ብዬ እገምታለሁ።
በአማራ ብሄርተኝነት ፅንሰ ሃሳብ አልስማማም። ሆኖም ሃሳቡን በሚገባው ለመረዳት እና ለመፈተሽ ሃሳቡን ደፌ ለመሟገት እወዳለሁ። በአማራ ብሄርተኝነት እና ኢትዮጵያዊ ብሄርተኝነት ያለው ውይይት ትንሽ የረከሰ ነው ማለት ይቻላል። ውይይትም ማለት አይችላልም። በስድብ፤ ዘለፋ እና በመግባባት እጦት የተሞለ ነው። አንዱ ወገን (እዚህ ላይ እራሴን አካትቼ ነው የምናገረው) ለሌላው ወገን አይቆረቀሩምጅ("empathy" የለም)። የዚህ ጽሁፍ አንዱ አላማ ይህንን ለማስተካከል ነው።
ሌላው አላማ ይውይይት ነጥቦቹን ለማጠንከር ነው። ይህን ማድረግ የሚቻለው የሌላውን ወገን ክርክሮች ስንመለከት ጠንካራ ጎኑን (http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/03/blog-post_21.html) በማየት ነው። ፉክክር ላይ ደካማ ጎን ላይ እናተኩራለን። ገምቢ ውይይት ላይ ግን ጠንካራ ወገን ላይ ነው ማተኮር ያለብን። ስለዚህ ከአማራ ብሄርተኝነት መከራከርያ ነጥቦቻቸው ደካማ ወይንም ስሜታዊ ወይንም መሰረት የሌላቸውን ነጥቦች ትተን ምክንያት እና አቅም ያላቸውን ነጥቦች ማየት ይገባል።
ክዚህ ጽሁፍ ልመልሰው የምፈልገው ጥያቄ ይህ ነው፤ « ለመን በአማራነት መደራጀት አስፈለገ በኢትዮጵያዊነት መደራጀት አይሻልም ወይ?»። ለዚህ ጥያቄ አጭር መልሱ ይህ ይመስለኛል፤
1. የጎሳ ብሄርተኝነት አሁንም በኢትዮጵያ ዙርያ ሰፍኗል እያደገም እያለ ነው እነ ጠ/ሚ አብይ ለመቀነስ ምንም እየሞከሩ ቢሆንም። የጎሳ ብሄርተኝነት በደምብ ያልነገሰው ቦታ የአማራ ክልል ነው። ሌሎች ክልሎች በሙሉ ፖለቲካቸውን በጎሰኝነት እና ጎሰኝነት ብቻ አደራጅተዋል።
2. የዛሬው ሁኔታ ይህ በመሆኑ እና ሀገሪቷ ለ27 ዓመት በጎሳ አስተዳደር ፕሮፓጋንዳ መሞላቱ ለአማራው ህልውና እና ጠቃሚ ስልት (strategy) ሲባል ለአማራው በጎሳ ብብሄርተኝነት መልክ መደራጀት ይመረጣል በኢትዮጵያዊነት ወይንም አንድነት ከመደራጀት ይልቅ።
3. የአማራ ህዝብ ላለፉት 27 ዓመት ስለተጨቆነ እና የሀገራዊ ብሄርተኝነት ራዕይ አልሰራም የሚል አመለካከት አንዳንዱ ላይ ስላለ የአማራ ህዝብ የሀገራዊ ብሄርተኛ የሆኑት ድርጅቶችን ደግፍ ቢባልም በሙሉ ልቡ አይደግፍም።
4. ሀገሪቷ በጎሳ ብሄርተኝነት ስለጥለቀለቀች ከአማራ ውጭ ለሀገራዊ ብሄርተኝነት ያለው ድጋፍ እጅግ ዝቅተኛው ነው የሚሆነው። የነ ለማ ቡድን ኢትዮጵያ ብሄርተኛ ቢሆንም ፖለቲካ ውድድር ቢካሄድ (እንደ ምርጫ) የኦሮሞ ብሄርተኞች በቀላሉ እነ ለማ ቡድንን ያሸንፏቸዋል። ሰለዚህ በመጨረሻ የሀገራዊ ብሄርተኛ ፓርቲዎች ከአማራ ውጭ ኢሚንት ድጋር ይኖራቸዋል በአማራ ክልል ደግሞ ደካማ ድጋፍ ይኖራቸዋል። ስለዚህ ሀገር ዙርያ ሲደመር የኢትዮጵያ ብሄርተኝነት ንቅናቄው ደካማ ይሆናል ከጎሳ ብሄርተኝነት አንፃር። የጎሳ ብሄርተኝነት በደምብ አይሎ አሸናፊ ሆኖ ይገኛል።
5. ይህ ብዙ ድጋፍ የሌለው የኢትዮጵያ ብሄርተኝነት ፓርቲ የኢትዮጵያ ብሄርተኝነትን የሚደግፈው ህብረተሰብ ከነ አማራውን በሚገባው መወከል አይችልም ኃይሉ ከጎሳ ብሄርተኞች እጅግ ደካማ በመሆኑ። በድርድር ጠረጵዛ፤ ፓርላማ፤ ወይንም በፖለቲካ ኃይል ሙግት የሀገራዊ ፓርቲው ይጨፈለቃል።
6. ገን አማራው በአማራ ብሄርተኝነት ስር ከተደረጀ ለአመታት የተከማቸውን ብሶት እንደ ኃይል ተጠቅሞ ጠንካራ አማራውን በማንኛውም ደረጃ መወከል የሚችል ድርጅት ይገነባል። አሁን ባለው የጎሳ ብሄርተኝነት ያጥለቀለቀው የሀገራችን የፖለቲካ ሁኔታ የአማራ ህዝብን የብሶት ስሜት እንደ ኃይል ተጠቅሞ ጠንካራ እና ቋሚ ድርጅት ማቋቋም ለአማራው ህልውና ግዴታ ነው።
7. ጠንካራ የአማራ ፓርቲ ከተቁቁመ ሌሎች የጎሳ ፓርቲዎችን በኃይል ሚዛን ይይዛቸዋል። ምክንያቱም የአማራ ብሄርተኛ ፓርቲው የጎሳ ፓርቲ ቢሆንም አማራ ጎሰኝነት በባህሪው ከኢትዮጵያ ብሄርተኝነት የተቆራኘ ስለሆነ። በዚህም ብምክንያት የአማራ ብሄርተኝነት ፓርቲው ከክልል ውጭ ላሉት አማሮች ያገለግላል።
እኔ እንደሚመስለኝ የአማራ ብሄርተኝነት ንቅናቄ መኖር ምክንያት ባጭሩ ይህ ነው።
እስካሁን ባየሁት የተለየዩ ሰዎች አስተያየት ሌሎች የክርክር ነጥቦች ይነሳሉ። ለምሳሌ «አምራ ከሁል ተጨቁኗል»፤ «ሌላው ሲደራጅ ልምን አማራ ይጠየቃል»፤ «በአማራ ብሄርተኝነት ምን አገባችሁ»፤ «ኢትዮጵያዊ ድርጅቶች በአማራ ትከሻ ላይ ነው የተቁቁሙት»፤ «የአንድነት ኃይሎች አማራን ዘርፈውታል ነግደውታል»፤ «የአንድነት ኃይሎች ሌቦች ናቸው» ወዘተ። እነዚህ ስሜታዊ፤ ከመሰረተ ጉዳዩ ውጭ፤ ወይንም ሃሰት የሆኑ የክርክር ነጥቦች ስለሆኑ አልተጠቀምኳቸውም ክርክሩን ያደክማሉ እና።
ስለዚህ የአብን ከአንድነት ይልቅ በአማራነት መደራጀት ምክንያት እንዲህ ነው። እስቲ ህልችሁም በሁለቱም ወገን ያላችሁ ይህን አንብቡ እና እናንተም ከአቋማችሁ ተቃራኒ የሆነውን ወገን ይዛችሁ መከራከር ሞክሩ። እንዲህ እያደረግን ወደ መስማማት ወይንም በሰላም ላለመስማማት ደረጃ (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2016/10/blog-post.html) እንደርሳለን ብዬ እገምታለሁ።
Subscribe to:
Posts (Atom)