የመጨረሻ ዸቂቃ እየደረሰ ስለሆነ ጸጉር ቅንጠሳችንን ትተን ወደፊት እንራመድ።
የግንቦት ፯፤ አዴፓ እና አብን ግብ ከሞላ ጎደል አንድ ነው። ግንቦት ፯ የዜግነት ፖለቲካን ነው ማስፈን የሚፈልገው። በሌላ ቋንቋ ህገ መንግስቱን ከጎሳ አስተዳደር ወደ ብዝሃነት ያለው የዜጋ አስተዳደር መቀየር ነው።
አዴፓ በይፋ አይናገረው እንጂ ወደ ዜግነት ፖለቲካ ማምራቱ የታወቀ ነው። ህገ መንግስቱ በዚህ መንገድ ይቀየር ቢባል አዴፓ ይደግፈዋል።
አብን ደግሞ አንዳንድ መሪዎቻቸው ምንም ቢደነባበሩ ሁለት አላማ አለኝ ብሎ በይፋ ተናግሯል። እነዚህን ፩) የአማራ ህዝብ ጥቅምን ማስከበር እና ፪) ህገ መንግስቱን ወደ ዜግነት አስተዳደር መቀየር።
ስለዚህ ሶስቱ ድርጅቶች፤ ግንቦት ፯፤ አዴፓ እና አብን፤ የዜግነት ፖለቲካ በኢትዮጵያ እንዲሰፍን ይታገላሉ። ታባባሪ ናቸው እና እንደ ታባባሪ አብረው ሊሰሩ ይገባል።
ግቡ የዜግነት ፖለቲካ ነው። የግቡ ምክንያት የጎሳ ፖለቲካ የግጭት መንስኤ ስለሆነ የባህል ብዝሃነት ያለው የዜግነት ፖለቲካ ብቻ ነው ሰላም የሚያመጣው ነው።
ይህን ግብ ለመምታት ሶስቱ ፓርቲዎች የተለያየ መንገድ ይጠቀሙ ይሆናል። ግን ሶስቱም በአንድ አቅጣጫ እየሄዱ ስለሆነ ከመጠላለፍ ተቆጥበው ወደ መደጋገፍ ሊገቡ ይገባል። ለሶስቱም የሚጠቅም ነገር ነው።
በመቸረሻ ግንቦት ፯ ጠንክሮ ድርሻውን ማሟላት አለበት። አዴፓ ጠንካራ ነው፤ አብን አባላትን በደምብ እየሰበሰበ ነው። ግን ግንቦት ፯ ከብዙሃን ድጋፉ አንጻር ገና ነው። መፍጠን አለበት፤ አማራጭ የለም።
የሰላም ክፍሌ ይትባረክ ብሎግ፤ ስለ ሀገራችን ኢትዮጵያ ያለኝን ትናንሽ ሀሳቦች በትህትና አቀርባለሁ። ለስሕተቶቼም በቅድሚያ ይቅርታ እጠይቃለሁ
Showing posts with label NAMA. Show all posts
Showing posts with label NAMA. Show all posts
Tuesday, 19 March 2019
Friday, 18 January 2019
Unraveling NAMA's "Intellectual Cover"
የአማራ ብሄርተኝነት በመሰረቱ የብሶት ፖለቲካ (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/07/blog-post_30.html) ነው። የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን) መሪዎችም ተከታዮችም በትርክታቸው የሚያተኩሩት ስለአማራ ላይ የደረሰው የ27/44 ዓመት በደል ነው። አማራ ከሌላው ኢትዮጵያዊ ተለይቶ ተበድሏል ይላሉ። አልፎ ተርፎ ካሳም ይገባዋል ይላሉ። ከፖለቲካዊ ፕሮፓጋንዳዎቻቸው ምናልባት 80%ኡ ስለዚህ ስለ አማራው መጨቆን ነው። ይህ የአማራ ብሄርተኝነት በመሰረቱ በብሶት የሚመራ ንቅናቄ መሆኑን ያስረዳል።
ሆኖም እንደ ማንኛውም ፖለቲካ ንቅናቄ የአማራ ብሄርተኝነት ትርክት እና ፖለቲካዊ ጽንሰ ሃሳብ (theory) ያስፈልገዋል። ይህ intellectual cover (የምሁራን ሽፋን ልበለው?) የአብን ምሁራኖች በደምብ ሰርተውበታል። ዋናው የዚህ ሽፋን መልእክት እንዲህ ነው፤
«የአማራ ብሄርተኝነት የሚያስፈልገው የሌሎች (ያጠቁን) የጎሳ ብሄርተኝነቶችን በኢትዮጵያ ፖለቲካ እንዳያመዝኑ ማድረግ ነው። የአማራ ብሄርተኝነት የሌሎች የጎሳ ብሄርተኝነቶችን balance በማድረግ የአማራንም የኢትዮጵያንም ህልውና ይጠብቃል።»
ማንኛውም ትንሽም ስለፖለቲካ/ታሪክ የሚያውቅ ሰው ይህ ትክርት እጅግ የተሳሳተ እንደሆነ ያውቃል። በርካታ ጎሳዎች ወይንም ክልሎች ባሉባቸው ሀገራት የስልጣን ውድድር በመሃል እና በክልሎቹ እንደሆነ የታወቀ ነው (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/on-nama-strategies.html)። ስልጣን ከምሃሉ (ኢትዮጵያዊነት) ወደ ልልሎች (ጎሳ ብሄርተኝነት) ቁጥር ሁሉም ጎሳ ብሄርተኞች ይጠነክራሉ። የጎሳ ብሄርተኞቹ ከእርስ በርስ ይልቅል የሚሟገቱት ከመሃሉ (ከኢትዮጵያዊነት) ነው። ዋናው አላማቸው መሃሉ ማድከም ነው። በዚህ ጋራ አላማቸው ይተባበራሉ። መሃሉ መንምኖ ሲያበቃው ስልጣን በሙሉ በጎሳ ብሄርተኞች እጅ ይሆናል። ከዛ እነዚህ የጎሳ ብሄርተኞች (ለምሳሌ ህወሓት፤ ኦነግ፤ አብን፤ ወዘተ)እርስ በርስ መደራደር አይችሉም። በጎሳ እና ብሶት የተመሰረቱ ስለሆነ የጋራ ማንነት እና ጥቅም ስለማይታያቸው የሚደራደሩት በባዶ ድምር (zero sum) አቋም ነው። ወጤቱ ጦርነት እና መለያየት ነው የሚሆነው። ሰለባው በየክልሉ የሚኖር አማራ፤ አማራ ክልል፤ መላው ኢትዮጵያዊ ነው የሚሆነው። መሃሉ ሲመነምን እና ጎሳ ብሄርተኞች ሲጠነክሩ ውጤቱ ይህ ነው።
እስቲ በዚህ ረገድ አንዳንድ የአብን አስተሳሰብ የውስጥ ተቃርኖዎች (inconsistencies) እንመልከት። በአንድ በኩል የጎሳ አስተዳደርን (ethnic nationalism) እንቃወማለን፤ የዜጋ ፖለቲካ ነው የሚያስፈልገው ያላሉ። በጎሳ የተደራጀነው ነባራዊው ሁኔታ አስገድዶን ነው እንጂ የጎሳ አስተዳደር ይቁም ይላሉ። የጎሳ አስተዳደር መኖር የለብትም ሲሉ ደግሞ ምክንያቱ አንድ ሀገር በጎሳ ሲስተዳደር ግጭቶች ይበዛሉ ነው። ኦሮሚያ የሚኖሩ አማሮች ይጠቃሉ፤ ነባር እና መጤ ግጭት። ጠረፍ ላይ ግጭት ይኖራል፤ የመሬት ግጭት። በሁሉም የፖለቲካም የማህበረሰብም መስክ ሰው ጎሳውን አስቀድሞ ኢ-ፍትሃዊነት ያራምዳል፤ የፍትህ ግጭት። ለዚህ ነው የጎሳ አስተዳደር የግጭት ምንጭ ነው እና ይቅር የሚባለው። በሌላ አባባል ፖለቲካ በጎሳ ብሄርተኝነት ሲመራ ግጭት ይመጣል ነው። እንዲህ ከሆነ ኢንዴት ነው አብን እንደሚለው የአማራ፤ የኦሮሞ፤ የትግራይ ወዘተ ብሄርተኞች ኢትዮጵያዊነትን አፍርሶ እንደገና በድርድር መገንባት የሚችሉት! የጎሳ ብሄርተኞች መደራደር አይችሉም ተብሏል። አሁን ደግሞ መደራደር ይችላሉ። ሃሳቦቹ ይቃረናሉ።
አልፎ ተርፎ «የኢትዮጵያ የብሄር (ጎሳ) እስር ቤት ናት፤ ሰለዚህም ሁሉም ኢትዮጵያዊ በጎሳው ይሰብሰብ እና እነዚህ የጎሳ ብሄርተኛ ስብስቦች አንዲስ ኢትዮጵያ ይመስርቱ» የሚለው ሃሳብ በ1950/60ዎቹ በማርክሲስት የተማሪ ንቅናቄው የተወለደ ነው። እስከ ዛሬም እነ ህወሓት፤ ኦነግ እና ሌሎች ጎሳ ብሄርተኞች ይህንን አቋም ነው የያዙት። በ1983 ህወሓት ስልጣን ሲይስዝም ይህን ነው አሰምሮ የተናገረው። «እንዳንተ «አንድነቶች» ኣናንተ «አማሮች»፤ እምዬ ኢትዮጵያ ከማለት በጎሳችሁ ተሰብሰቡ እና ተደራደሩ» እያሉ መሃይም ጥሩምባቸውን ይነፉ ነበር። ይህ ሃሳብ ወድቅ መሆኑ የገባን ደግሞ የጎሳ ብሄርተኞች ስብስብ ጦርነት እንጂ ሰላም አያመጣም ነበር። እንሆ ውጤቱን አየነው። ፖለቲካ በጎሳ ሲሆን ጸብ ብቻ ነው የሚኖረው። የጎሳ ፖለቲካ በተፈጥሮ የዜሮ ድምር አስተሳሰብን ይከተላልና።
ስለዚህ አብን ይህንን ታሪክ አውቆ እንዴት ነው ወደ ጎሳ ፖለቲካ እንመለስ የሚለው? አይገባኝም። እኔ እንደሚመስለኝ የሚገባ ብሶት እና ቅሬታቸውን የምሁራን ልብስ (intellectual cover) ለማልበስ ብለው የአብን ልሂቃን እራሳቸውን ወደ የማይሆን ትምዝምዝ ውስጥ አስገበተዋል። የአማራ ብሄርተኝነት በዚህ መልኩ ምንም አይነት ምሁራዊ ድጋፍ የለውም እና ሊፈጥሩ ለት አይችሉም። የብሶት የጎሳ ብሄርተኝነት ነው፤ ሌላ ነገር አንፍጠርለት። አንዴ ይህንን ካመንን በኋላ እንዴት ነው የህዝቡን ብሶት እና በደል በሚጠቅመው ሁኔታ ማስተናገድ የሚቻለውን የፖለቲካ ጥያቄን ለመመለስ እንስራ።
ሆኖም እንደ ማንኛውም ፖለቲካ ንቅናቄ የአማራ ብሄርተኝነት ትርክት እና ፖለቲካዊ ጽንሰ ሃሳብ (theory) ያስፈልገዋል። ይህ intellectual cover (የምሁራን ሽፋን ልበለው?) የአብን ምሁራኖች በደምብ ሰርተውበታል። ዋናው የዚህ ሽፋን መልእክት እንዲህ ነው፤
«የአማራ ብሄርተኝነት የሚያስፈልገው የሌሎች (ያጠቁን) የጎሳ ብሄርተኝነቶችን በኢትዮጵያ ፖለቲካ እንዳያመዝኑ ማድረግ ነው። የአማራ ብሄርተኝነት የሌሎች የጎሳ ብሄርተኝነቶችን balance በማድረግ የአማራንም የኢትዮጵያንም ህልውና ይጠብቃል።»
ማንኛውም ትንሽም ስለፖለቲካ/ታሪክ የሚያውቅ ሰው ይህ ትክርት እጅግ የተሳሳተ እንደሆነ ያውቃል። በርካታ ጎሳዎች ወይንም ክልሎች ባሉባቸው ሀገራት የስልጣን ውድድር በመሃል እና በክልሎቹ እንደሆነ የታወቀ ነው (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/on-nama-strategies.html)። ስልጣን ከምሃሉ (ኢትዮጵያዊነት) ወደ ልልሎች (ጎሳ ብሄርተኝነት) ቁጥር ሁሉም ጎሳ ብሄርተኞች ይጠነክራሉ። የጎሳ ብሄርተኞቹ ከእርስ በርስ ይልቅል የሚሟገቱት ከመሃሉ (ከኢትዮጵያዊነት) ነው። ዋናው አላማቸው መሃሉ ማድከም ነው። በዚህ ጋራ አላማቸው ይተባበራሉ። መሃሉ መንምኖ ሲያበቃው ስልጣን በሙሉ በጎሳ ብሄርተኞች እጅ ይሆናል። ከዛ እነዚህ የጎሳ ብሄርተኞች (ለምሳሌ ህወሓት፤ ኦነግ፤ አብን፤ ወዘተ)እርስ በርስ መደራደር አይችሉም። በጎሳ እና ብሶት የተመሰረቱ ስለሆነ የጋራ ማንነት እና ጥቅም ስለማይታያቸው የሚደራደሩት በባዶ ድምር (zero sum) አቋም ነው። ወጤቱ ጦርነት እና መለያየት ነው የሚሆነው። ሰለባው በየክልሉ የሚኖር አማራ፤ አማራ ክልል፤ መላው ኢትዮጵያዊ ነው የሚሆነው። መሃሉ ሲመነምን እና ጎሳ ብሄርተኞች ሲጠነክሩ ውጤቱ ይህ ነው።
እስቲ በዚህ ረገድ አንዳንድ የአብን አስተሳሰብ የውስጥ ተቃርኖዎች (inconsistencies) እንመልከት። በአንድ በኩል የጎሳ አስተዳደርን (ethnic nationalism) እንቃወማለን፤ የዜጋ ፖለቲካ ነው የሚያስፈልገው ያላሉ። በጎሳ የተደራጀነው ነባራዊው ሁኔታ አስገድዶን ነው እንጂ የጎሳ አስተዳደር ይቁም ይላሉ። የጎሳ አስተዳደር መኖር የለብትም ሲሉ ደግሞ ምክንያቱ አንድ ሀገር በጎሳ ሲስተዳደር ግጭቶች ይበዛሉ ነው። ኦሮሚያ የሚኖሩ አማሮች ይጠቃሉ፤ ነባር እና መጤ ግጭት። ጠረፍ ላይ ግጭት ይኖራል፤ የመሬት ግጭት። በሁሉም የፖለቲካም የማህበረሰብም መስክ ሰው ጎሳውን አስቀድሞ ኢ-ፍትሃዊነት ያራምዳል፤ የፍትህ ግጭት። ለዚህ ነው የጎሳ አስተዳደር የግጭት ምንጭ ነው እና ይቅር የሚባለው። በሌላ አባባል ፖለቲካ በጎሳ ብሄርተኝነት ሲመራ ግጭት ይመጣል ነው። እንዲህ ከሆነ ኢንዴት ነው አብን እንደሚለው የአማራ፤ የኦሮሞ፤ የትግራይ ወዘተ ብሄርተኞች ኢትዮጵያዊነትን አፍርሶ እንደገና በድርድር መገንባት የሚችሉት! የጎሳ ብሄርተኞች መደራደር አይችሉም ተብሏል። አሁን ደግሞ መደራደር ይችላሉ። ሃሳቦቹ ይቃረናሉ።
አልፎ ተርፎ «የኢትዮጵያ የብሄር (ጎሳ) እስር ቤት ናት፤ ሰለዚህም ሁሉም ኢትዮጵያዊ በጎሳው ይሰብሰብ እና እነዚህ የጎሳ ብሄርተኛ ስብስቦች አንዲስ ኢትዮጵያ ይመስርቱ» የሚለው ሃሳብ በ1950/60ዎቹ በማርክሲስት የተማሪ ንቅናቄው የተወለደ ነው። እስከ ዛሬም እነ ህወሓት፤ ኦነግ እና ሌሎች ጎሳ ብሄርተኞች ይህንን አቋም ነው የያዙት። በ1983 ህወሓት ስልጣን ሲይስዝም ይህን ነው አሰምሮ የተናገረው። «እንዳንተ «አንድነቶች» ኣናንተ «አማሮች»፤ እምዬ ኢትዮጵያ ከማለት በጎሳችሁ ተሰብሰቡ እና ተደራደሩ» እያሉ መሃይም ጥሩምባቸውን ይነፉ ነበር። ይህ ሃሳብ ወድቅ መሆኑ የገባን ደግሞ የጎሳ ብሄርተኞች ስብስብ ጦርነት እንጂ ሰላም አያመጣም ነበር። እንሆ ውጤቱን አየነው። ፖለቲካ በጎሳ ሲሆን ጸብ ብቻ ነው የሚኖረው። የጎሳ ፖለቲካ በተፈጥሮ የዜሮ ድምር አስተሳሰብን ይከተላልና።
ስለዚህ አብን ይህንን ታሪክ አውቆ እንዴት ነው ወደ ጎሳ ፖለቲካ እንመለስ የሚለው? አይገባኝም። እኔ እንደሚመስለኝ የሚገባ ብሶት እና ቅሬታቸውን የምሁራን ልብስ (intellectual cover) ለማልበስ ብለው የአብን ልሂቃን እራሳቸውን ወደ የማይሆን ትምዝምዝ ውስጥ አስገበተዋል። የአማራ ብሄርተኝነት በዚህ መልኩ ምንም አይነት ምሁራዊ ድጋፍ የለውም እና ሊፈጥሩ ለት አይችሉም። የብሶት የጎሳ ብሄርተኝነት ነው፤ ሌላ ነገር አንፍጠርለት። አንዴ ይህንን ካመንን በኋላ እንዴት ነው የህዝቡን ብሶት እና በደል በሚጠቅመው ሁኔታ ማስተናገድ የሚቻለውን የፖለቲካ ጥያቄን ለመመለስ እንስራ።
Friday, 4 January 2019
የአብን መሪዎች ትምክሕተኛ ናቸው!
https://www.facebook.com/seyoum.teshome/videos/1916214778447833/
ሙሉውን ቃለ ምልልስ አላየሁትም ግን… የአብን መሪዎች ክርስቲያን ታደለ እና በለጠ ሞላ ትምክተኛ ነን ሲሉ ይታያል። እስቲ ከዚህ ጥርውን ወገን ልውሰድ…
ባለፉት ረዥም ረዥም ዓመታት የጎሳ ብሄርተኞች አማራ ወይንም «የአማራ ግዥ መደብ» ዋና ጨቋኝ ነው ብለው ሲሰብኩ አብሮ ቋንቋችንን መርዘዋል። «አድሃሪ»፤ «ነፍጠኛ»፤ «ትምክሕርተኛ»፤ «ጠባብ» የሚሉትን ቃላቶች ለአሉታዊ እና ሃሰተኛ ትርክት ተጠቅመዋል። የ«ጨቋኝ ተጨቋኝ» ትርክትን ሽጠውልናል።
የትርክቱን ሃሰትነት ለማስረገጥ እግረ መንገዳችን እነዚህ ቃላቶችን መልሰን ማዳን አለብን። ማሸማቀቅያ እንዲሆኑ መፍቀድ የለብንም። አንዳንድ አማራዎች በተለይም ወደ አብን የሚሳቡት ለረዥም ዓመታት እነዚህን ስድቦች ሲሰሙ ስሜታቸው እጅግ ተነክቷል። የበታችነት እንዲሰማቸው ተደርጓል። ለዚህም ነው አዎ በአማራነቴ እመካለሁ የሚሉት። አላፍርበትም ነው። ካሁን ወድያ ይህ ቃል ኃይል የለውም ነው። ልድገመው፤ ካሁን ወድያ ይህ ቃል ኃይል የለውም ነው።
ይህ ጥሩ ነገር ነው። አብኖች፤ ቀጥሉበት! (ግን የውሃ ልክ አይነት ያልሆነ ነገር ተውው!)
ይህን ሁሉ ስል በአብን የአማራ ብሄርተኝነት እና በበርካታ የሚሪዎቻቸው አቋም ጭራሽ አልሳማማም። ግን ዛሬ እረፍት ልስጣቸው እና ጥሩ ወገኑን ልጥቀስ።
ሙሉውን ቃለ ምልልስ አላየሁትም ግን… የአብን መሪዎች ክርስቲያን ታደለ እና በለጠ ሞላ ትምክተኛ ነን ሲሉ ይታያል። እስቲ ከዚህ ጥርውን ወገን ልውሰድ…
ባለፉት ረዥም ረዥም ዓመታት የጎሳ ብሄርተኞች አማራ ወይንም «የአማራ ግዥ መደብ» ዋና ጨቋኝ ነው ብለው ሲሰብኩ አብሮ ቋንቋችንን መርዘዋል። «አድሃሪ»፤ «ነፍጠኛ»፤ «ትምክሕርተኛ»፤ «ጠባብ» የሚሉትን ቃላቶች ለአሉታዊ እና ሃሰተኛ ትርክት ተጠቅመዋል። የ«ጨቋኝ ተጨቋኝ» ትርክትን ሽጠውልናል።
የትርክቱን ሃሰትነት ለማስረገጥ እግረ መንገዳችን እነዚህ ቃላቶችን መልሰን ማዳን አለብን። ማሸማቀቅያ እንዲሆኑ መፍቀድ የለብንም። አንዳንድ አማራዎች በተለይም ወደ አብን የሚሳቡት ለረዥም ዓመታት እነዚህን ስድቦች ሲሰሙ ስሜታቸው እጅግ ተነክቷል። የበታችነት እንዲሰማቸው ተደርጓል። ለዚህም ነው አዎ በአማራነቴ እመካለሁ የሚሉት። አላፍርበትም ነው። ካሁን ወድያ ይህ ቃል ኃይል የለውም ነው። ልድገመው፤ ካሁን ወድያ ይህ ቃል ኃይል የለውም ነው።
ይህ ጥሩ ነገር ነው። አብኖች፤ ቀጥሉበት! (ግን የውሃ ልክ አይነት ያልሆነ ነገር ተውው!)
ይህን ሁሉ ስል በአብን የአማራ ብሄርተኝነት እና በበርካታ የሚሪዎቻቸው አቋም ጭራሽ አልሳማማም። ግን ዛሬ እረፍት ልስጣቸው እና ጥሩ ወገኑን ልጥቀስ።
Monday, 15 October 2018
On NAMA Strategies
One of the National Movement of Amhara's (NAMA) strategies seems to be to out-ghetto Oromo nationalists, so to speak. That is, to demonstrate political positions and attitudes that are as radical or even more radical than Oromo nationalists. Simple examples - NAMA leadership and intellectuals have made statements in support of Article 39 and of maintaining ethnic identification on kebele id cards. And apparently at a recent NAMA meeting, supporters publicly voiced the idea of evicting Oromos living on Oromia zones in Amhara Region.
The idea behind this strategy, it seems to me, is that taking extreme positions, which, by the way, have no acceptance from the Amhara masses, will help neutralize Oromo and other ethnic nationalists by restoring the political balance. The NAMA view is that Oromo nationalists have been 'coddled' for too long and now have too much political power now, and one of the ways for NAMA to counteract that is by showing strength through extremism. Basic tit-for-tat strategy.
The problem with this is that it is based on an erroneous and simplistic understanding of the phenomenon of ethnic nationalism in a multi-ethnic nation. The goal of ethnic nationalism is to tear away at the centre, weaken it, and take power away from it to the periphery, which is various ethnic nationalisms. Adding 'another' ethnic nationalism to this actually further weakens the centre and strengthens all ethnic nationalist movements.
A further factor that NAMA doesn't seem to consider is the asymmetric nature of ethnic relations in Ethiopia. The Amhara live in large numbers in various regions, while the Oromo do not.
Given this, Oromo nationalists would much rather have a weak or empty centre and deal with a strong Amhara nationalist movement. This is their perfect scenario, in which all Oromos, including moderate ones, will congregate to Oromo nationalism, making it the only game in Oromia, so to speak. They will negotiate tit for tat agreements with Amhara nationalism and have their Oromo homeland.
What about issues that Oromo nationalists and Amhara nationalists do not agree on, such as Amharas in Oromia, and the case of Addis Ababa? With all Oromos on board, Oromo nationalists will not give an inch on this, and there will be conflict, either overt or covert. The main victims, given the population distribution I mentioned above, will be Amharas and other ethnic groups in Oromia and in Addis Ababa. And if NAMA has a vision of being able to carry out a TPLF 2.0 and forcing itself on the whole country, well, I think we all realize how realistic that is.
Now, I think we should take a step back and ask ourselves 'why'. Why does NAMA exist and why does it take the positions and attitudes in does? In order to reach any kind of understanding and solution to the issues at hand, this question has to be the focus. As I've written about this in my blog, for me, there are two major reasons: 1) The upheaval and resulting weakness of Ethiopian nationalism (or 'the centre') over the past 50 years, and 2) accumulated resentment for the treatment of the Amhara, including by Amhara 'traitors', over the past 27 years, and the resulting grievance and inferiority complex. NAMA is simply an outgrowth of this. The second factor we can do little about - time will heal wounds. But the first we must work hard with all our might to correct, as fixing that - strengthening the centre tangibly via political parties and institutions - is a sine qua non for the survival of Ethiopia.
The idea behind this strategy, it seems to me, is that taking extreme positions, which, by the way, have no acceptance from the Amhara masses, will help neutralize Oromo and other ethnic nationalists by restoring the political balance. The NAMA view is that Oromo nationalists have been 'coddled' for too long and now have too much political power now, and one of the ways for NAMA to counteract that is by showing strength through extremism. Basic tit-for-tat strategy.
The problem with this is that it is based on an erroneous and simplistic understanding of the phenomenon of ethnic nationalism in a multi-ethnic nation. The goal of ethnic nationalism is to tear away at the centre, weaken it, and take power away from it to the periphery, which is various ethnic nationalisms. Adding 'another' ethnic nationalism to this actually further weakens the centre and strengthens all ethnic nationalist movements.
A further factor that NAMA doesn't seem to consider is the asymmetric nature of ethnic relations in Ethiopia. The Amhara live in large numbers in various regions, while the Oromo do not.
Given this, Oromo nationalists would much rather have a weak or empty centre and deal with a strong Amhara nationalist movement. This is their perfect scenario, in which all Oromos, including moderate ones, will congregate to Oromo nationalism, making it the only game in Oromia, so to speak. They will negotiate tit for tat agreements with Amhara nationalism and have their Oromo homeland.
What about issues that Oromo nationalists and Amhara nationalists do not agree on, such as Amharas in Oromia, and the case of Addis Ababa? With all Oromos on board, Oromo nationalists will not give an inch on this, and there will be conflict, either overt or covert. The main victims, given the population distribution I mentioned above, will be Amharas and other ethnic groups in Oromia and in Addis Ababa. And if NAMA has a vision of being able to carry out a TPLF 2.0 and forcing itself on the whole country, well, I think we all realize how realistic that is.
Now, I think we should take a step back and ask ourselves 'why'. Why does NAMA exist and why does it take the positions and attitudes in does? In order to reach any kind of understanding and solution to the issues at hand, this question has to be the focus. As I've written about this in my blog, for me, there are two major reasons: 1) The upheaval and resulting weakness of Ethiopian nationalism (or 'the centre') over the past 50 years, and 2) accumulated resentment for the treatment of the Amhara, including by Amhara 'traitors', over the past 27 years, and the resulting grievance and inferiority complex. NAMA is simply an outgrowth of this. The second factor we can do little about - time will heal wounds. But the first we must work hard with all our might to correct, as fixing that - strengthening the centre tangibly via political parties and institutions - is a sine qua non for the survival of Ethiopia.
Subscribe to:
Posts (Atom)