Showing posts with label nation building. Show all posts
Showing posts with label nation building. Show all posts

Monday, 14 January 2019

ክርስቲያን ታደለን ተውት፤ የመጠላለፍ ፖለቲካ ባህልን ካላቆምን ሁላችንም አብረን እንጠፋለን!

ሰሞኑን የአብን አመራር የሆነው ክርስቲያን ታደለ የህአዴግ አባል ስለነበር ስሙን ለማጥፋት የሚሯሯጡ የ«አንድነት» ደጋፊዎች አይተናል። እጅግ ያሳዝናል። አሁን ሀገራችን ባለችበት ከባድ የፖለቲካዊ እና ማህበራው ችግር፤ የግብረ ገብ እና ስነ መግባር እጦት፤ አሁን ባለንበት አደገኛ ጊዜ እንዲህ ያነት ርካሽ እና ጎጂ የፖለቲካ ሽኩቻ ሀገራችንን ወደ ማጥፋት ይመራናል።

እረ ከታሪካችን እንማር! የጃንሆይን መግስት የጣሉ ከራሳቸው መንግስት ያሉት አብረው ተስማምተው መስራት ባለመቻላቸው ነው። ደርግ እና ህወሓት በስልጣን ላይ ቆይተው ሀገሪቷን ማተራመስ የቻሉት አንድ አቋም ያላቸው ተቃዋሚዎች አብረው በስነ ስርአት መስራት ባለመቻላቸው ነው። እንደ ቅንጅት አይነት ተስፋ የነበረው ድርጅት/መንገስ የጠፋው አብሮ መስራትን እንደ ሽንፈት ስላየነው ነው። አብሮ ሰርቶ፤ win-win ሁኔታዎች ላይ አተኩሮ፤ long term ጥቅማችን ላይ አቶኩረን ከመስራት ፋንታ በርካሽ እና ጠቃሚ ያልሆነ ግብ-ግብ ላይ ተደምደን ሀገርን ለማፍረስ ሰራን!

ኢትዮጵያ አሜሪካ አይደለችም! እንደነሱ ርካሽ ፖለቲካ ጸቦችን አሽከርክረን ከምርጫ በኋላ የምንስማማበት ሁኔታ የለንም። አሁን ሀገር ግንባታ ላይ ነን እንጂ የአሜሪካ ምርጫ ላይ አይደለንም። ሀገር ግንባታ ርካሽ ሳይሆን ውድ እና ዘላቂ አቋም፤ ግንኙነት እና ግንባታ ነው የሚያስፈልገው (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/02/blog-post_20.html)።

ክርስቲያን ታደለ እንደ ሁላችንም ስህተቶች አድርጓል። ምናልባት ከኢህአዴግ መስራቱ ጠቅሞም ይሆናል (እንደነ ቲም ለማ እና ሌሎች በርካቶች)። አልፎ ተርፎ ክርስቲያን ታደለ ልጅ ነበር አሁንም ነው። «በአንድ ወቅት ክርስቲያን ታደለ የኢህአዴግ አባል ነበር አሁን ግን አቋሙን ቀይሯል» ማለት ተገቢ ነው። የክርስቲያን የሚያራምደውን አስተሳሰብ በሚገባው መግጠም እና መሟገት ተገቢ ነው። ጨዋ እና በቂ አካሄድ ነው። ግን ከዛ አልፎ መሳደብ ነውርነት፤ ርካሽነት እና ግብዝነት ነው። ርህራሄ ማጣት ነው። እነዚህን የሀገራችን ፖለቲካ ለዓመታት እያተራመሱት ያሉት ባህሪዎችን የሚያንጸባርቅ አካሄድ ነው። ዛሬውኑ ይቁም (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/07/blog-post_31.html)!

አሁን በሀገራችን የጎሰኝነት ችግር አለ። የህወሓት እና ሌሎች ነባሮች የሽብር ችግር አለን። የገብረ ገብ እጦት አለን። የመተማመን፤ አርቆ ማየት፤ የራስን የሩቅ ጥቅም መገንዘብ፤ የመራራት፤ የመተባበር ወዘተ ታላቅ እጦት አለን። Emergency ላይ ነን። ታሪካችንን አንድገም። ነውርነትን አቁመን ከጠ/ሚ ዓቢይ ተምረን አውንታዊ መንገድ እንያዝ ብሄ እለምናለሁ።

Thursday, 18 October 2018

የአዲስ አበባ ህዝብ መደራጀት፤ እንደ እባብ ልባሞች እንደ ርግብም የዋሆች ሁኑ

ትላንት ሁለት የአዲስ አበባ ሰዎች በማይሆን ክስ ታስረዋል። ከሱም እንደገባኝ ከሆነ ወጣቶችን በ«አዲስ አበባ በከተማው ተወላጅ ነው መመራት ያለበት» መፈክር ዙርያ ማደራጀት ነው። ለዚህም አደረጃጀት ከፍልስቴም ኮንሱሌት ጋር ተባብረዋል ነው ሌላው ክስ። እነዚህ ስራዎች በፍፁም ህገ ወጥ አይደሉም እና መታሰር እንደሌለባቸው ግልጽ ነው። ሆኖም ትላንት እነዚህ እስረኞች በጭለማ ቤት እየተሰቃዩ (torture) ይገኙ ነበር። ዛሬ ደህና ፍርድ ሳያገኙ አይቀርም። መከራ ለነሱ ቢሆንም መሻሻል ነው።

በዚህ ግዳይ በርካቶች አቤቱታ እያቀረቡ ነው። ጥሩ ነው፤ እንደዚህ አይነት የማይሆን እስርን መቃወም አለብን። ግን እንደምናውቀው ፖለቲካችን ከመቃወም ወደ መስራት መሻገር አለበት። Proactive politics beats reactive politics anytime።

መሰራት ያለበት ስልታዊ አደረጃጀት ነው። በመጀመርያ ለምንድነው «ወጣቶችን» የምናደራጀው? ሰራተኛው የት አለ? ወዝ አደሩ የት አለ? የቢሮ ሰራተኛው የት አለ? ወላጆች የት አሉ? ጡረተኞች የት አሉ? መከከለኛ መደቡ የት አለ? ሃብታሙ የት አለ? «የተማረው» የት አለ? ምሁራኑ የት አለ? ልሂቃኑ የት አለ? ለምንድነው «ወጣቱ» (እውነቱን ለመናገር ስራ የሌለው ወጣት) ሸክሙን መሸከም ያለበት?

ይህ «ወጣትን» ማደራጀት ዘላቂነት እንደሌለው ይታወቃል። ሁሉም ህዝብ መሳተፍ አለበት ለእውነተኛ የዜግነት ፖለቲካ ወይንም የሲቪክ አደረጃጀት። ወጣቱ ተሳትፎ ሌላው ከሸሸ ዋጋ የለውም ብቻ ሳይሆን ጎጂም ሊሆን ይችላል። እንደ ሜኪናን በአራተኛ ማርሽ ማስጀመር ማለት ነው።

ሌላው ችግር ገና መደራጀቱ በተገቢው ሁኔታ አይጀምር እራስን ለጥቃት ማጋለጥ ነው። እኔ እንደሚገባኝ የአዲስ አበባ መደራጀት አላማ «የአዲስ አበባ ህዝብ መብቱ እንዲከበር» ነው። ከንቲባው የአዲስ አበባ ትውልድ ይሁን አይሁን አይደለም። የአዲስ አበባ ህዝብ መብት ከተጠበቀ ምርጫ ይኖራል እና ህዝቡ የፈለገውን ይመርጣል። ግቡ እንዲህ ግልጽ ሆኖ ካየነው እና ግቡ ላይ ካተኮርን 1) ስራችንን በትክክሉ እንሰራለን እና ይሳካልናል 2) ለጥቃት እራሳችንን አናጋልጥም!

አካሄዱ እንደሚመስለኝ እንዲህ ነው መሆን ያለበት፤

1) በጣም ሰፊ ተዕልኮ (vision and mission) ያለው ድርጅት ማቋቋም፤ ለምሳሌ «የአዲስ አበባ ህዝብ መብት እና ጥቅም ለማስከበር የሚሰራ» ድርጅት ማለት ነው። ሀ) ሰፊ ተዕልኮ ስለሆነ ለመጠቃት መጋለጡ አነስተኛ ነው የሚሆነው። ለ) ብዙ ሰዎችን በተለይም «መደራጀት» ሲባል የማይገባቸው ወይንም የሚፈሩትን ይጋብዛል። እናቶች፤ ወላጆች፤ መካከለኛ መደቡን። ሃብታሙን ወዘተ ይጋብዛል።

2) ከመፈክር በፊት መደራጀት። መጀመርያ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ከፋይ አባላት ይኖረው። ከዛ በኋላ ነው መንቀሳቀስ። እንቅስቃሴው ከአቅም ጋር አብሮ መሄድ አለበት! እንቅስቃሴው ከአቅም ጋር አብሮ መሄድ አለበት! አቅም ሳይጎለበት መራመዱ ጥቃትን መጋበዝ ነው። የቅንጅት ታሪክ ይህን ነው የሚያስተምርን። ቅንጅት በመቶ የሚቆጠሩ መሪዎች እና አባላት ነበረው ከዛ ቀጥሎ እስከ ብዙሃኑ ድረስ ከሞላ ጎደል ባዶ መዋቅር ነበር። ጥቂት መሪዎች እና ብዙ ብዙሃን። መሃሉ ባዶ ነው። እነዚህ ጥቂት መሪዎች ሲጠቁ እና እርስ በርስ ሲጣሉ ማን ይተካቸው። መዋቅሩ እስከ ታች ባዶ ነበርና። ስለዚህ መጀመርያ መጠንከር ከዛ ወደ ዋና ስራ መግባት ነው ትክክለኛ አሰራር። ይመስለኛል።

የአዲስ አበባ ህዝብ ወይንም ጠቅላላ የኢትዮጵያ ህዝብ በተለያየ ወኪላዊ ድርጅቶች መደራጀት አለበት (በዜግነት ፖለቲካ ካመንን)። አለበለዛ ያው የጎሳ ፖለቲካ ማለትም የግጭት ፖለቲካ ነው የሚቀረን። ለሀገራችን ህልውና ቅድመ ሁኔታ ነው ማለት ነው። ስለዚህ ይህን ዋና ስራ በሙሉ ተሳትፎ በሰከን ያለ ብልጥ መንገድ እንስራው። ህዝብ በሙሉ እንዲሳተፍ እናድርግ።

«እንደ በጎች በተኵላዎች መካከል እልካችኋለሁ፤ ስለዚህ እንደ እባብ ልባሞች እንደ ርግብም የዋሆች ሁኑ።»

Tuesday, 20 February 2018

ታሪክን አንድገም፤ ሀገርን እንገንባ

አሳፋሪና አገር አፍራሽ ታሪካችንን እንዳንደግም ነው ይህን ጽሁፍ የምጽፈው። ታሪክ እንደመዘገበው ከኢህአዴግ ውጭ ያለነው ምሁራን፤ ፖለቲከኞችና ብዙሃን በፖለቲካ ረገድ ቁም ነገር ለማድረግ እድል ባጋጠመን ቁጥር እልዳችንን አበላሽተናል። በተደጋጋሚ ጊዜ ለአገራችን የፖለቲካ መስተካከል ከኢህአዴግም ይበልጥ እንቅፋት ሆነን ተገኝተናል።  ይህን ደፍሬ መናገር የምችል ይመስለኛል።

አንዱ የድክመታችን ምክንያት ተልዕኮአችንን አለማወቃችን ወይም መርሳታችን ነው። ተልዕኮአችን የአገር ፖለቲካ ግንባታ ነው እንጂ የፖለቲካ ውድድር አይደለም። የአገር ፖለቲካ ስርዓት ግንባታ ሲባል ሁላችንም ስለ ህገ መንግስትን ማርቀቅ ነው የምናስበው። ግን ከዚህ ህገ መንግስት ማርቀቅ ስራ በፊት  የልብ ለልብ መተዋወቅ፤ በተወሰነ ደረጃ መተማመን፤ መግባባትና መስማማት ያስፈልጋል። እነዚህ ለአገር ግንባታ የፖለቲካ ድርድር ቀድሞ ሁኔታዎች ናቸውና። አለነዚህ ማንኛውም በወረቀት ያለ ህግ፤ ምንም አይነት ወርቅ የሆነ ህግ ቢሆነም፤ በስራ ሊተገበር አይችልም

ቀጥሎ በነዚህ ተመስርቶ ህገ መንግስትና ሌሎች የርዓይና የህግ ሰነዶች ይደነገጋሉ። ቅራኔ ወይም አለመግባባት ካለ በህግ መሰረት ይፈታል ህጉ ደግሞ በቂ ካልሆነ ያለው መተማንና ስምምነት ለፍትህ ይረዳል። የአገር የፖለቲካ ግንባታ ሂደት እንደዚህ ነው መሆን ያለበት።

የፖለቲካ ውድድር ደግሞ የሚጀምረው የፖለቲካ ስረዓቱ ከተዋቀረ በኋላ የሚመጣው የፖለቲከኞችና ሌሎች ለመሪነት እርስ በርስ በህጉ መሰረት መወዳደር ነው። በምእራብ «ዴሞክራሲዎች» እንደዚህ አይነቱ ውድድር በርካታ ክርክር፤ ክስ፤ ዘለፋም ወዘተ ያካትታል። የህጉን ገደብ ዳር ዳር እየነኩ ግን ሳያልፉ እነዚህን አይንቶች ባህሪዎችን ያንጸባርቃሉ። ይህ ስልጣን ለመያዝ ሊበጃቸው ይችላል ግን ምንም አይገነባም። እርግጥ መተማመንንና ውይይትን ይጎዳል ግን ከምርጫው በኋላ የደረሰውን ጉዳት ይጠግኑና የአገር ማስተዳደር ስረአቸውን ይጀምራሉ። ይህ ነው በተለምደው የምናውቀው የፖለቲካ ውድድር።

የፖለቲካ ውድድር ደግሞ የፖለቲካ ስርዓቱ ከተዋቀረ በኋላ የሚከተለው የፖለቲከኞችና ሌሎች ለመሪነት እርስ በርስ በህጉ መሰረት መወዳደር ነው። በምእራብ «ዴሞክራሲዎች» እንደዚህ አይነቱ ውድድር በርካታ ክርክር፤ ክስ፤ ዘለፋ ወዘተ ያካትታል። የህጉን ገደብ ዳር ዳር እየነኩ ግን ሳያልፉ እነዚህን አይንቶች ባህሪዎችን እያንጸባርቁ ይወዳደራሉ። ይህ ስልጣን ለመያዝ ሊበጃቸው ይችል ይሆናል ግን አገርን አይገነባም ይጎዳልም። ሰልዚህም ነው ውድድሩ ምርጫው ካለፈ አሸናፊዎቹ ውድድሩ ያደረሰውን ንዴት፤ ቂምና ጉዳት ይጠግን ዘንድ ትሸናፊዎቹንም መላው የአገሪቷን ህዝብ አንድ የሚያረግ እርቃዊ ንግግርና ተግባር የሚአደርጉት። ይህ ነው በተለምዶ የምናውቀው የፖለቲካ ውድድር።

ስለዚህ አገርን መገንባትና የፖለቲካ ውድድር የተለያዩ ባህሪያት፤ ተግባራትና ልምድ ያስፈልጋቸዋል። የአገር ግንባታ ሂደት እንደ መተማመን፤ ስምምነት፤ አንድነት፤ መግባባት፤ ህብረት፤ ቅራኔን መፍታት፤ ውይይት ወዘተ አይነቱ ባህሪያትና ልምዶች ያስፈልጉታል። የፖለቲካ ውድድር ግን ክርክር፤ ውድድር፤ ፉክክር፤ መካሰስ፤ ህግና ስረዓትን ዳር ዳሩን መጣስ፤ ወዘተ አይነቱን ልምዶች ያካትታል። በአገር ግንባታ ሂደት መካከል እነዚህን የፖለቲካ ውድድር ባህሪያትና ልምዶች ይዘን ከገባን አገርን መገንባት ሳይሆን ማፍረ ነው የምናደርገው።

ለዚህ ደግሞ በርካታ ታሪካዊ ምሳሌዎች አሉን። እስቲ ወደ 15 ዓመታት ወደ ኋላ ተመልሰን የ«ተቃዋሚ» ምሁራን፤ ጋዜጠኛና ፖለቲከኞች እያደረጉ፤ እየተናገሩ፤ እየጻፉ ምን እንደነበር እናስታውስ። ስራቸውን ባጭሩ ለመግለጽ «እርስ በርስ መበላላት» ማለት ይቻላል! ተቃዋሚዎች ኢህአዴግ ከሚተቹት ይበልጥ እርስ በርስ ነበር የሚፋጁት። ጋዜጣ ላይ ቁም ነገር ሳይሆን ስድብና የመንደር ወሬ ነበር የሰፈነው። ከሞላ ጎደል ስራቸው 90% አፍራሽ 10% ገምቢ ነበር። ስለዚህም ነው ተቃዋሚው ጎራ ምርጫ '97 በግንቦት ሆኖ እሰከ የካቲት አካባቢ የትብብር መዋቅሮች ያላደራጀው! ለዚህም ነው ከምርጫው በኋላ ተቃዋሚዎች በቀላሉ የተበታተኑት። በበፊቱ ዓመታት እዱሉ እያለን ቅስ ብለን በትብብር ጉዳይ ተወያይቶ ትብብርን ከመፈጸምና ጠንካራ መሰረት የሆነ መዋቅርን ከመገንበት እንደ ምርጫ ተዋዳዳሪዎች እየተሰዳደብን ዋልን። ችግር ሲመጣ ለመቋቋም አቅሙ አልነበረንም። እርስ በርስ ተፋጅተን አለቅን። የግንባታ ስራ ያልተሰራባቸው ቅንጅትና ህብረት በቀላሉ ፈረሱ። የፖለቲካ መዋቅር ግንባታንና የፖለቲካ ውድድርን መለየት ያልቻሉትም ከፖለቲካ ወጡ። የህዝብም ትዝብት አደረባቸው።

በርካታዎቻችን በምዕራብ የሚዲያ ዜና፤ ትምህርትና ፕሮፓጋንዳ ስላደግን የነዚህ አገራት ፖለቲካ ስናይ ፖለቲካ እንደዛ መሆን እንዳለበት ይመስለናል። የናየው ደግሞ የፖለቲካ ውድድራቸውን ነው። ክርክሩን፤ ዘለፋውን፤ ስድቡን፤ ሴራውን ወዘተ። እኛም እንደነሱ ማድረግ እንወዳለን መሰለኝ። ግን ኢትዮጵያ ያለችበት ቦት፤ ለረዥም ዓመታት ያለችበት ቦታ፤ ገና የአገር ፖለቲካ ግንባታ ላይ ናት። ብዙሃኑም ልሂቃኑም የፖለቲካ መደቦቻችን እስካሁን በእምነት የተመሰረተ አገራቷን ምን መምሰል አለበት የሚል ሰፊ ስምምነት ላይ አልደረስንም። አሁንም ያለው ዋና ስራችን የህ ነው። አዎን ህገ መንግስት አለን ግን ሰፊው ርአይና ስምምነት የለንም። ነገ ኢህአዴግ ከስልጣን ቢወርድም ይህ ስምምነቱ ስለሌለ ሁከትና አብዮት ይከተላል።

በዚህ ምክንያት ሁላችንም፤ ምሁራን፤ ብዙሃን፤ ፖለቲከኛ፤ የመንግስት ሰራተኛ፤ ወዘተ ትኩረታችን ወደ አገር ግንባታ መቀየር አለበት። ይህ ማለት ከታች የተጠቀሱትን ለአገር ግንባታ አስፈላጊ የሆኑትን ብሃሪያት፤ ተግባሮችና ልምዶች ከራሳችን ጋር መዋሃድና በዚህ አስተሳሰብ ወደ ፊት መራመድ።

ስምምነት፤ አንድነት፤ መግባባት፤ ህብረት፤ መተማመን፤ በስነ ስረዓት መነጋገር፤ ውይይት፤ ቅራኔን መፍታት።

የሚቀጥለው ጊዜ አንድ ሰውን ወይም ቡድንን መዝለፍ ወይም መስደብ ካሰኘን ቆመን እናስብ። የፖለቲካ ውድድር ውስጥ አይደለንም። እንደዚህ አይነቱ ባህሪያት ታሪካችን እንደሚያረጋግጠው ሁላችንንም ጠርጎ ገደል ውስጥ ያስገባል አገራችንን ያፈርሳል። በሰላም እየተከባበርን እየተማመንን ነው መወያየት ያለብን። ይህ የሁላችንንም ጥቅም ያስከብራልና። ይህንን ብቻ ተግባራዊ ካደረግን አለ ምንም ጥርጣሬ ታላቅ አገር እንገነባለን ጠላት የምንላቸውም ምንም ሊጎዱንም አይችሉም።