Sunday 10 February 2019

በ«ቤተሰብ ምጣኔ» ስም የሚፈጸመው ጉዳት



 

በ«ቤተሰብ ምጣኔ» ስም በአማራ ክልል እየተፈጸመ የነበረው ማህበረሰባዊ ጉዳት ይህ ደብዳቤ / መመርያ ይገልጻል። አንብቡት።

ከዚህ ደብዳቤ የምንረዳው ዋና ነገሮች እነዚህ ይመስሉኛል፤

፩፤ የመጀመርያ ነጥብ የድርጅቱ አንዱ ግብ (target) የወሊድ መቆጣጠርያ የሚጠቀሙ ሴቶች ቁጥር መጨምር እንደሆነ ግልጽ ያደርጋል። እነዚህ ግቦች የሚመነጩት ደግሞ ከጤና ጥበቃ ቢሮ ብቻ ሳይሆኑ በዋና ደረጃ ከለጋሾቻቸው ማለትም ከተለያዩ የውጭ ሀገር ለጋሾች እንደ ኢዩ እና ዩኤሴይድ (አንድ ምሳሌ፤ http://www.healthpolicyproject.com/index.cfm?ID=country-Ethiopia)። ይህ ማለት የክልሉ መንግስት፤ የጤና ጥበቃ ቢሮ ሃላፊዎች፤ እና የጤና ቢሮ በታቾች ለገንዘብ ብለውም እንደዚህ አይነት ጉዳት የሞላው ፖሊሲ ፈጽመዋል። አዲሱ ቅኝ ግዛት እንዲህ ነው የሚሰራው።

፪፤ እነዚህን ግቦች ለመምታት በጣም ግልጽ የሆኑ ስህተቶች ተፈጽመዋል። ለምሳሌ በሁለተኛ፤ ሶስተኛ እና አምስተኛ ነጥቦች እንደሚገለጸው በረጅም ጊዜ መቆጣጠርያ ላይ የማይሆን ትኩረት ተደርጓል። የጤና ተቋሙ ገንዘቡን ለማምጣት ጸንፈኛ የሆነ አቋም እና ፖሊሲ ለማራመድ ወደኋላ አላለም። ለምሳሌ ሁሉንም ሴቶች የወሊድ መቆጣጠርያ ተጠቃሚ የማድረግ ታርጌት እና ፖሊሲ ከጫፍ የያዙ ጽንፈኝነት በቀር ሌላ ቃል ሊሰጠው ያችልም።

፫፤ ነጥብ ሰባት የጤና ጥበቃ ቢሮው እንደ ተቋምም ሰራቶኞቹም ለገንዘብ ብለው የተለያዩ የወሊድ መቆጣጠርያ እንደሚያስተዋወቁ እና ሴቶች ላይ እንደሚጭኑ በግልጽ ያስረዳል። ፖሊሲው የሚመራው ለህዝቡ ጤንነት ምን ይበጃል በሚለው መርህ ሳይሆን ምን ገንዘብ / ጉቦ ያመጣልናል በሚለው ነው። ስለዚህ የፖለሲው እና የተግባሩ አለቆች እና ወሳኞች የውጭ ሀገር ለገሾች እና የወሊድ መቆጣጠርያ ሳጭ ኩባኒያዎች ናቸው ማለት ነው።

፬፤ ይህ የብሉሹ እና የበሰበሰ አሰራር የጤና ተቋሙ ሚስኪን ሴቶች ላይ የቅስቀሳ ዘመቻ እያካሄዱ የሴቶቹ ስነ ልቦና እና ጤና የሚጎዳ ነገሮች እንዲያደርጉ እንደሚያደርግ ነጥብ ስምንት ያረጋግጣል። የጤና ጥበቃ ቢሮ ቢሮው ገንዘብ እንዲአገኝ፤ ሰራተኞቹም ለግላቸው ገንዘብ / ጉቦ / ስኮላርሺፕ እንዲያገኙ ጉዳት እንደሚፈጽሙ ግልጽ ነው።

፭፤ የአማራ ህዝብ ልሂቃኑን በደምብ መፈተሽ እና ማስተካከል እንዳለበት ግልጽ ነው። ከላይ ደጋግሜ የገንዘብ ሚና እንዴት የአማራ ጤና ጥበቃ ቢሮ የውጭ ሀገር ለጋሾች እና የመድሃኔት ሻጮች መሳርያ እንዲሆን እንዳደረገ ገለጽኩኝ። ገን ከዚም አልፎ ተርፎ በርካቶች በርዕዮት ዓለም ደረጃ በዚህ ጸንፈኛ ፖሊሲ የሚያምኑ የአማራ «የተማሩ» ልሂቃን አሉ። ከሁሉም በላይ ይህ ነው የሚያሳዝነው። ልሂቃኖቻችን በበአድ አስተሳሰብ አዕምሮአቸው ተገዝቷል። ወደ ኋላ ብለው የጠጡትን ፕሮፓጋንዳ መፈተሽም አይችሉም። የህዝብ ቁጥር ምጣኔ ከሌላ አንጻር መመልከትም አይችሉም። ህዝቡ እራሱ የራሱን የቤተሰብ ምጣኔ መወሰን እንደሚችል፤ ሃብታም በሆነ ቁጥር እራሱ የሚወልደውን ቁጥር እንደሚቀንስ፤ የቤተሰብ ምጣኔ የህዝብ ቁጥርም መቀነስ ጉዳይ አለመሆኑ፤ ወዘተ መገንዘብ የማይችል ልሂቃን ተፈጥሯል። የህዝቡን ስነ ልቦና እና ማህበረሰባዊ እሴቶች የማያውቅ ልሂቃን ተፈጥሯል። በዚህ ላይ ብዙ ስራ ሊሰራ የሚያስፈልግ ይመስለኛል።

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!