ሁልጊዜ ጥሩውን ነገር መውሰድ ነው… ደካማውን ወገን ትቶ…
የጎሳ አስተዳደር (ፌደራሊዝም) ደጋፊዎች ባህል፤ ቋንቋ እና ሌላ ማንነታችን ለራሳችን ተትቶ እውቅና ይኖረው ይላሉ። የጨርጨር ኦሮሞ የራሱን ማንነት ጠብቆ በሰላም ለመኖር ለዓመታት ታግዷል። የምኒሊክ ጦር 150 ዓመት በፊት መጥቶ አስተአደር እና ባህል ከሌላ ቦታ አምጥቶ የጨርጨር ኦሮሞ ማንነቱን ጠብቆ መኖር አልቻልም ነው። ለኔ ይህ አመለካከት የተወሰነ እውነታ አለው። ለሰው ልጅ የአካባቢ (local) ማንነቱ የተፈጥሮአዊ አስፈላጊነት አለው። የሰው ልጅ በተፈጥሮ ቤተሰብ እና መንደር ያስፈልገዋል። ይህ ተፈጥሮ ነው ብዬ አምናለሁ የሰው ልጅ ታሪክም ይህንን ይመሰክራል። አንዳንድ የጎሳ አስተዳደር ደጋፊዎች ይህን አስተዳደር የምንፈልገው የጎሳ ወይንም ይበልጥ የአካባቢ ማንነቴ እንዳይወረር ነው ሲሉ ይገባኛል። ተገቢ አመለካከት ይመስለኛል።
የማልስማማበት ነገር ግን የአካባቢ ማንነት በህግ ደረጃ የጎሳ ውየን የ«ብሄር ብሄርተሰቦች እና ህዝቦች» ይሁን በሚለው ነው። የምቃወምበት ምክንያቶችም ሁለት ቀላል እና ግልጽ ምክነያቶች ናቸው፤ 1) የአካባቢ ማንነት በጎሳ ከተመሰረተ አግላይ ነው፤ ሰውን በደም እና አጥንት ምክንያት ከአካባቢው በእኩልነት እንዳይቀላቀል ይከልላል እና 2) በጎሳ ከተመሰረተ ግጭት ያመጣል፤ ይህንን ደግሞ በቴኦሪም በ27 ዓመት ታግባር አይተነዋል አሁንም እያየነው ነው።
ስለዚህ እንዴት ነው የጨርጨር ኦሮሞ ባህሉን፤ ቋንቋውን እና የአካባቢ ማንነቱን የሚጠብቀው አስተዳደሩ የጎሳ ካልሆነ? ማለት የጎሳ አስተዳደር ደጋፊዎችን ግብ ለማሳካት እንምራ፤ ግቡን እናሳካ ግን በሌላ መንገድ። የአካባቢ ማንነት እንዲሰፍን እናድርግ ግን አለ ጎሳ አስተዳደር። እንዴት እናድርገው? አንድ ቀላል አማራጭ የዛሬውን ህገ መንግስትን ብዚህ መልኩ መቀየር ነው። «ብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች» የሚለውን በዜጋ ይቀየር። የክልል አወቃቀሩ እንዳለ ይሁኑ እንበል። ህገ መንግስቱ ላይ ለክልል ግን እጅግ ይበልጥ ለዞን እና ለወረዳ በርካታ ኃይሎች ይስጥ። ዛሬ ካለው ይልቅ አብዛኛው የመንግስት ኃይል ወደ ዞን እና ወረዳ ይውረድ። ይህ ከተደረገ የአካባቢ ማንነት በዘላቂነት ይጠበቃል።
ለምሳሌ አንድ ዞን አካባቢ አስተዳደር ቋንቋ እና የትምሕርትቤት ቋንቋ የመወሰን መብት ይኑረው። ምናልባትም የመሬት ፖሊሲ መብት ይኑረው። የአስተዳደር ዘዴ መብትም ይኑረው። ወዘተ። ብዙ መብቶች ወደ ታች ወደ ዞን እና ወረዳ መውረድ ይችላል። ይህን በማድረግ አካባቢዎች ኃይል እና ስልጣን እንዲኖራቸው ይደረጋል። መአከላዊ እና ክልላዊ መንግስቶች የራሳቸውን ፍላጎት እና ተጽዕኖ ዞን እና ወረዳዎች ላይ ተገቢ ያልሆነ ጫና ማድረግ ያችልም። የአካባቢ ባህል፤ ቋንቋ እና ማንነት በደምብ ይጠበቃል። መዓከላዊ እና ክልላዊ መንግስቶች እነዚህ ነገሮችን መንካት አይችሉም። የአካባቢ ማንነት autonomy ይጠበቃል።
አንዳንድ የጎሳ አስተዳደር ደጋፊዎች ይህ አሰራር የአከባቢ ማንነትን ሊያስከብር ያችልም ትሉ ይሆናል። በተለያየ መንገድ አዲስ አበባ፤ የምአከላዊ መንግስት፤ የክልል መንግስት ወዘተ በባህልም በሌላም ተጽዖን አድርጎ ማንነቱን ሊቀይር ይችላል ትሉ ይሆናል። ምናልባት። ግን እንዲህ ከሆነ የጎሳ አስተዳደርም ይሄንን ሊከላከል አይችልም! ጨርጨር የአካባቢ ማንነቱን ከክልሉ በጎሳ መልክ የሚቀበል ከሆነ ተቀባይ ነው ዴሞክራሲያዊ አይደለም። ስለዚህ ነጻነት የለውም። ግን ነጻነቱ ቢሰጠው እና በጎሳ ይልቅ በአካባቢ ቢሆን የጨርጨር ኦሮሞ አብዛኛ በመሆኑ አካባቢው በራሱ ባህል ይቀርጸዋል። እዛ የሚኖሩ ኦሮሞ ያልሆኑትም እኩል ዜጋ ስለሆን ደም እና አጥንታቸው ስለማይቆጠር ይህንን የአካባቢ ማንነት ይደግፉታል እና ይሳተፋሉ። Win-win ሁኔታ ነው።
እስቲ ይህን ሃሳብ አስቡበት። አውቃለሁ የኢትዮጵ ምሁራን የተማሩት በtextbook የምዕራባዊ ፍልስፍና ነውና ስለ localism፤ communitarianism ወዘተ ብዙ አስበንም ገብቶንም አናውቅም። የጎሳ መብት እንላለን ግን አሁንም ከላይ ወደ ታች መጫን ነው ፍላጎታችን። ሌላ አስተሳሰብ ግን ዞሮ ዞሮ ከላይ ወደታች። ግን እስቲ ለአካባቢዎች እውነተኛ ነጻነት እንስጣቸው። ማንም እንዳይጎዳ የዜግነት መንብት እንዲሰፍን አድርገን ግን በርካታ መብቶች ወደ ታች እናውርድ። ይህ ሃሳብ የጎሳ አስተአደር እና የዜግነት አስተዳደር ደጋፊዎችን የሚያስማማ ይመስለኛል።
(ለስህተቶች ይቅርታ በችኮላ ነው የጻፍኩት!)
የሰላም ክፍሌ ይትባረክ ብሎግ፤ ስለ ሀገራችን ኢትዮጵያ ያለኝን ትናንሽ ሀሳቦች በትህትና አቀርባለሁ። ለስሕተቶቼም በቅድሚያ ይቅርታ እጠይቃለሁ
Showing posts with label social capital. Show all posts
Showing posts with label social capital. Show all posts
Thursday, 3 January 2019
Monday, 15 October 2018
የአዲስ አበባ ወጣቶቻችን፤ Nameless and faceless
ዛሬ በመሃበራዊ ሚዲያ ለ«ታፈሱት የአዲስ አበባ ወጣቶች» ፍትህ መጠየቂአ ቀን ይመስላል። ጥሩ እቅድ ነው።
ግን ማናቸው እነዚህ «ወጣቶች»? መስላቸው የት አለ? ስማቸውስ? ቤተሰቦቻቸው የት አሉ? ልጆች አላቸው ይሆን? ወላጆቻቸው የት ናቸው? እየተፈለጉ ነው ወይ? ማን ስለነሱ በየቤቱ እያለቀሰ ነው?
እኔ እስከመቀው ለነዚህ ጥያቄዎች መልስ የለንም። ለምን የለንም? እንዴት በመቶዎች ወይንም በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ታፍሰው ወደ ወታደራዊ ካምፕ ሲወሰዱ ምስላቸው፤ ስማቸው፤ ቤተሰቦቻቸው አይመዘገቡም? አዲስ አበባ የአምስት ሚሊዮን ህዝብ ከተማ ናት። ልጆቿ እንዲህ አይነት ነገር ሲደርስባት እንዴት ዝርዝሩን አናውቅም? ኤንዴንት ቤተሰቦቻቸው ወይንም ወኪሎቻቸው በተለያየ ሚዲያ ወጥተው እንዲታዩ ወይንም እንዲናገሩ አይደረግም? ለምንድነው faceless ሆነው የሚቀሩት?
ለነዚህ ጥያቄዎች መሰረታዊ ምክንያቱ የአዲስ አበባ እና የኢትዮጵያ ህዝብ እንደዚህ አይነት ጥቃቄዎችንም የሚያስተናግድ እና የሚመልሱ አቅም ያላቸው የፖለቲካ እና ማህበራዊ ተቋሞች ስለሌለው ነው! እነዚህ ወጣቶች ከተታፈሱ በኋላ ሁላቸውም ከነ ምስላቸው፤ ስማቸው እና ቤተሰቦቻቸው ተመዝግበው እንደ አግባቡ በሚድያ መቅረብ ነበረባቸው። ወጣቶቹን የሚመዘግብ፤ ሁኔታቸውን የሚከታተል፤ ሰለነሱ የሚሟገት እና የአዲስ አበባ ህዝብን ሰለ ጉዳያቸው የሚያሳውቅ ድርጅት ሊኖር ይገባ ነበር! የአምስት ሚሊዮን ከተማ ነው፤ ይህ ሊሳነው አይገባም።
ስለዚህ ይህ ነው መሰረታዊ ችግሩ/ችግራችን። አልተደራጀንም። መደራጀት ለህልውናችን ግድ ነው። ይህ መሰረታዊ ችግር ካልተፈታ ህመሞቻችን ይቀጥላሉ! (If we don't address the fundamental cause we'll keep running after the symptoms and never catch up)።
ስለዚህ ጉዳይ ሌላ ነገር ላንሳ። እስቲ ስንቶቻችን ነን የነዚህ ወጣቶችን ቤተሰቦች አይዝዋችሁ እያልን የምንገኘው? የሚያስፈልጋቸው እርዳታ ካለ የምናረግላቸው? ለባለንጀራዬ ካላሰብኩኝ ለምን ሌላው ያስባል ብዬ አስባለሁ። በችግር ጊዜ ካልደረስኩለት ምን አይነት መተማመን እና ትብብር ይኖረናል? ይህ ሌላ መሰረታዊ ችግር ነው። የእርስ በርስ ግንኙነታችን (social capital) መንኗል። ፍትህ እና ሰላም ከፈለግን ይህ መታደስ አለበት።
https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2016/09/blog-post_14.html
https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/09/blog-post_97.html
ግን ማናቸው እነዚህ «ወጣቶች»? መስላቸው የት አለ? ስማቸውስ? ቤተሰቦቻቸው የት አሉ? ልጆች አላቸው ይሆን? ወላጆቻቸው የት ናቸው? እየተፈለጉ ነው ወይ? ማን ስለነሱ በየቤቱ እያለቀሰ ነው?
እኔ እስከመቀው ለነዚህ ጥያቄዎች መልስ የለንም። ለምን የለንም? እንዴት በመቶዎች ወይንም በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ታፍሰው ወደ ወታደራዊ ካምፕ ሲወሰዱ ምስላቸው፤ ስማቸው፤ ቤተሰቦቻቸው አይመዘገቡም? አዲስ አበባ የአምስት ሚሊዮን ህዝብ ከተማ ናት። ልጆቿ እንዲህ አይነት ነገር ሲደርስባት እንዴት ዝርዝሩን አናውቅም? ኤንዴንት ቤተሰቦቻቸው ወይንም ወኪሎቻቸው በተለያየ ሚዲያ ወጥተው እንዲታዩ ወይንም እንዲናገሩ አይደረግም? ለምንድነው faceless ሆነው የሚቀሩት?
ለነዚህ ጥያቄዎች መሰረታዊ ምክንያቱ የአዲስ አበባ እና የኢትዮጵያ ህዝብ እንደዚህ አይነት ጥቃቄዎችንም የሚያስተናግድ እና የሚመልሱ አቅም ያላቸው የፖለቲካ እና ማህበራዊ ተቋሞች ስለሌለው ነው! እነዚህ ወጣቶች ከተታፈሱ በኋላ ሁላቸውም ከነ ምስላቸው፤ ስማቸው እና ቤተሰቦቻቸው ተመዝግበው እንደ አግባቡ በሚድያ መቅረብ ነበረባቸው። ወጣቶቹን የሚመዘግብ፤ ሁኔታቸውን የሚከታተል፤ ሰለነሱ የሚሟገት እና የአዲስ አበባ ህዝብን ሰለ ጉዳያቸው የሚያሳውቅ ድርጅት ሊኖር ይገባ ነበር! የአምስት ሚሊዮን ከተማ ነው፤ ይህ ሊሳነው አይገባም።
ስለዚህ ይህ ነው መሰረታዊ ችግሩ/ችግራችን። አልተደራጀንም። መደራጀት ለህልውናችን ግድ ነው። ይህ መሰረታዊ ችግር ካልተፈታ ህመሞቻችን ይቀጥላሉ! (If we don't address the fundamental cause we'll keep running after the symptoms and never catch up)።
ስለዚህ ጉዳይ ሌላ ነገር ላንሳ። እስቲ ስንቶቻችን ነን የነዚህ ወጣቶችን ቤተሰቦች አይዝዋችሁ እያልን የምንገኘው? የሚያስፈልጋቸው እርዳታ ካለ የምናረግላቸው? ለባለንጀራዬ ካላሰብኩኝ ለምን ሌላው ያስባል ብዬ አስባለሁ። በችግር ጊዜ ካልደረስኩለት ምን አይነት መተማመን እና ትብብር ይኖረናል? ይህ ሌላ መሰረታዊ ችግር ነው። የእርስ በርስ ግንኙነታችን (social capital) መንኗል። ፍትህ እና ሰላም ከፈለግን ይህ መታደስ አለበት።
https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2016/09/blog-post_14.html
https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/09/blog-post_97.html
Thursday, 11 October 2018
የፌደራል መንግስት ዘመን አቆጣጠራችን (calendar) ይቀየር ይላሉ አቶ አብዱ አሊ ሂጅራ?!
ብስመ አብ! የፌደራል መንግስት ዘመን አቆጣጠራችን (calendar) ይቀየር ይላሉ አቶ አብዱ አሊ ሂጅራ?!
ከመአዛ አሸናፊ ጋር 10 ቀን በፊት ያደረጉትን ቋሚ ቃለ ምልልስ አሁን አዳመጥኩት (https://www.youtube.com/watch?v=s-ve5RiImNc)። ባጭሩ የቀን መቁጠርያችን እንደ ባህል እንጠብቀው፤ ለምሳሌ አዲስ አመትን አሁን እንደሚደረገው በመስከረም 1 ይከበር፤ ግን official ወይንም የመንግስት የቀን አቆጣጠር ወደ «ፈረንጁ» (Georgian calendar) አቆጣጠር ይቀየር። ምክነያቱ አብዛኛው ሀገራት በፈረንጁ አቆጣጠር ስለሚጠቀሙ በኢትዮጵያ አቆጣጠር መጠቀም ለበርካታ ስራ አይመችም። ሁልጊዜ ከአንዱ ወደ አንዱ መቀየር (convert) ስራን ያስተጓድላል አሉ አቶ አብዱ አሊ።
ይህ በብዞዎች ተቀባይነት ያለው አስተሳሰብ ነው። ግን ትክክል አይደለም… አይመስለኝም። ማንኛውም ትውፊታዊ ነገር እንደ ቀን መቁጠርያ እንደ «ባህል» ብቻ ይዘን በስራ ላይ ካልዋለ ቀስ ብሎ ይጠፋል! ለዚህም ነው ሀገራት የራሳቸውን ቋንቋ የሚጠብቁት። ከጃፓንኛ ወደ እንግሊዘኛ መከያየር ከባድ ስራ ነው። አብዛኛው የቴክኖሎጂ ነክ ነገሮች በእንግሊዘኛ ናቸው። ሆኖም ጃፓን በጃፓንኛ ቀልቋል። ያን ሁሉ ቴክኖሎሂ ነክ ስራዎችም ሲሰራ በጃፓንኛ ነው ያደረጉት። ድሮ የኮምፕዩተር ስራ በሌላ ቋንቋ መስራት በጣም ከባድ በሆነበት ዘመንም በጃፓንኛ ነበር የሰሩት። የማንነት ጉዳይ ስለሆነ እንደ ባህል አልትውትም። ሰሩበት አሁንም ይሰሩበታል። ይህ አስተያየት ለቋንቋ ብቻ ሳይሆን ለቀን መቁጠርያም ይሆናል።
በተዘዋዋሪ ኤርትራ የመንግስት የቀን መኩጠርያውን ሲቀይር እጅግ አዝኜ ነበር። ውጤቱ ዛሬ እና ነገ ይታያል እነ እንቁጣጣሽም እየተረሱ ይሄዳሉ።
ትንሽ ቃል ስለ ሃሳቡ ጠቅላላ መንፈስ ልጻፍ… ጣልያን ሀገር ብትሄዱ ሰንበት ሱቅ መከፈት የለበትም፤ እንደነ «ዎልማርት» አይነት ግዙፍ ሱቆች ሊኖሩ አይገባም፤ አማዞን ገደለን ወዘተ ይባላል። እነዚህ ነገሮች በማህበራዊ ኑሮ (including social capital)፤ ግለኝነት እና ብቸኝነት (individiualism and loneliness)፤ የትናንሽ ከተማ እና ሰፈር ህልውና፤ ወዘተ ላይ ያላቸው ሚና ይተቻሉ። ሁሉን ነገር 'rationalise' ማድረግ ጥቅም ብቻ ሳይሆን ጉዳትም እንዳሉእው ይታወቃል። በዚህ ምክንያት localism የሚባለው ርዕዮት ዓለም ባለፉት አስርት ዓመታት ወደ ልሂቃን መገናኛ ተመልሷል። ስለዚህ እንደዚህ አይነቱን ጉዳይ ላይላዩን ሳይሆን ጠልቀን መመርመር ይኖርብናል።
ከመአዛ አሸናፊ ጋር 10 ቀን በፊት ያደረጉትን ቋሚ ቃለ ምልልስ አሁን አዳመጥኩት (https://www.youtube.com/watch?v=s-ve5RiImNc)። ባጭሩ የቀን መቁጠርያችን እንደ ባህል እንጠብቀው፤ ለምሳሌ አዲስ አመትን አሁን እንደሚደረገው በመስከረም 1 ይከበር፤ ግን official ወይንም የመንግስት የቀን አቆጣጠር ወደ «ፈረንጁ» (Georgian calendar) አቆጣጠር ይቀየር። ምክነያቱ አብዛኛው ሀገራት በፈረንጁ አቆጣጠር ስለሚጠቀሙ በኢትዮጵያ አቆጣጠር መጠቀም ለበርካታ ስራ አይመችም። ሁልጊዜ ከአንዱ ወደ አንዱ መቀየር (convert) ስራን ያስተጓድላል አሉ አቶ አብዱ አሊ።
ይህ በብዞዎች ተቀባይነት ያለው አስተሳሰብ ነው። ግን ትክክል አይደለም… አይመስለኝም። ማንኛውም ትውፊታዊ ነገር እንደ ቀን መቁጠርያ እንደ «ባህል» ብቻ ይዘን በስራ ላይ ካልዋለ ቀስ ብሎ ይጠፋል! ለዚህም ነው ሀገራት የራሳቸውን ቋንቋ የሚጠብቁት። ከጃፓንኛ ወደ እንግሊዘኛ መከያየር ከባድ ስራ ነው። አብዛኛው የቴክኖሎጂ ነክ ነገሮች በእንግሊዘኛ ናቸው። ሆኖም ጃፓን በጃፓንኛ ቀልቋል። ያን ሁሉ ቴክኖሎሂ ነክ ስራዎችም ሲሰራ በጃፓንኛ ነው ያደረጉት። ድሮ የኮምፕዩተር ስራ በሌላ ቋንቋ መስራት በጣም ከባድ በሆነበት ዘመንም በጃፓንኛ ነበር የሰሩት። የማንነት ጉዳይ ስለሆነ እንደ ባህል አልትውትም። ሰሩበት አሁንም ይሰሩበታል። ይህ አስተያየት ለቋንቋ ብቻ ሳይሆን ለቀን መቁጠርያም ይሆናል።
በተዘዋዋሪ ኤርትራ የመንግስት የቀን መኩጠርያውን ሲቀይር እጅግ አዝኜ ነበር። ውጤቱ ዛሬ እና ነገ ይታያል እነ እንቁጣጣሽም እየተረሱ ይሄዳሉ።
ትንሽ ቃል ስለ ሃሳቡ ጠቅላላ መንፈስ ልጻፍ… ጣልያን ሀገር ብትሄዱ ሰንበት ሱቅ መከፈት የለበትም፤ እንደነ «ዎልማርት» አይነት ግዙፍ ሱቆች ሊኖሩ አይገባም፤ አማዞን ገደለን ወዘተ ይባላል። እነዚህ ነገሮች በማህበራዊ ኑሮ (including social capital)፤ ግለኝነት እና ብቸኝነት (individiualism and loneliness)፤ የትናንሽ ከተማ እና ሰፈር ህልውና፤ ወዘተ ላይ ያላቸው ሚና ይተቻሉ። ሁሉን ነገር 'rationalise' ማድረግ ጥቅም ብቻ ሳይሆን ጉዳትም እንዳሉእው ይታወቃል። በዚህ ምክንያት localism የሚባለው ርዕዮት ዓለም ባለፉት አስርት ዓመታት ወደ ልሂቃን መገናኛ ተመልሷል። ስለዚህ እንደዚህ አይነቱን ጉዳይ ላይላዩን ሳይሆን ጠልቀን መመርመር ይኖርብናል።
Tuesday, 2 October 2018
የአዲስ አበባ ተፈናቃዎች
የኛ የአዲስ አበባዎች አንዱ (ከብዙ) ድክመቶቻችን በዚህ ቪዲዮ ይገለጻል፤
https://www.youtube.com/watch?v=fhKBwe1wF2Y
ይህ ድክመት ከመሬታቸው የተፈናቀሉት ወንድሞች እይቶቻችን ጎረቤቶቻችንን ዞር ብለን አለማየት ነው። በመቶ ሺዎች «የብሎኬት ካሳ» ተሰጥተው ከቤታቸው ወደ ዳር ከተማ ባዶ የሆነ 70 ካራሜትር ተባርረዋል።
ሰፈር ከነ ማህበራዊ ኑሮ ተበታትነዋል። አብዮተኛ እርምጃ ተወስዶባቸዋል ማለት ይቻላል። ይህ ለተፈናቃዮች ብቻ ሳይሆን ለመላው የአዲስ አበባ ህዝብ ምን ያህል ጎጂ እንደሆነ ይታወቃል። "Social capital" ከሰረ፤ መተባበር ጠፋ፤ መተዋወቅ ጠፋ፤ መደጋገፍ ጠፋ፤ ማህበራዊ ግብረ ገብ ጠፋ፤ ኢ-ማህበራዊነት በዛ፤ ወንጀል በዛ ወዘተ።
አንዱ ለችግሩ መፍትሄ የመሬት ፖሊሲውን መቀየር ነው።
1. ካሁን ወድያ መንግስት መሬት መውሰድ የሚችለው ለመንግስት ጥቅም እንደ መብራት፤ ውሃ፤ መንገድ ወዘተ ይሁን። ካሳውም የ«ብሎኬት ዋጋ» ሳይሆን የመሬቱ ከነቤቱ የገበያ ዋጋ መሆን አለበት።
2. መሬት ለግል ጉዳይ እንደ ኢንቬስትሜንት ከተፈለገ ኢንቬስተሩ በግል ከመሬት ባለቤቶቹ መሬቱን ተደራድሮ ይግዛ። መንግስት ጣልቃ አይግባ። ገዥ እና ሻጭ ከተስማሙ ሁለቱም ደስተኛ ይሆናሉ። ኢንቬስተሩ የገበያ ዋጋ ስለከፈለ በመሬቱ አይቀልድም አዋጪ ነገር ላይ ያውለዋል። ሻጩም ተበድያለሁ አይልም በራሴ የወሰንኩትን አገኘሁኝ ብሎ ያምናል።
የሚጠቀም ሶስተኛ ወገኖችም አሉ። መላው የአዲስ አበባ ህዝብ ከመፈናቀል የሚያመጣው ጠቅላላ ህምሞች ይተርፋል። የመንግስት ሰራተኞችም ከሙስና ፈተና ይድናሉ። ማፈናቀል ወይንም የመሬት ፖሊሲው በጠቅላላ ካድሬዎች በረካሽ አፈናቅለው በውድ ለኢንቬስተር በመስጠት ሙስና የጋበዘ ስርዓት ነበር። ፖሊሲው ከተቀየረ ሁላችንም ከዚህ ሁሉ እንተርፋለን።
https://www.youtube.com/watch?v=fhKBwe1wF2Y
ይህ ድክመት ከመሬታቸው የተፈናቀሉት ወንድሞች እይቶቻችን ጎረቤቶቻችንን ዞር ብለን አለማየት ነው። በመቶ ሺዎች «የብሎኬት ካሳ» ተሰጥተው ከቤታቸው ወደ ዳር ከተማ ባዶ የሆነ 70 ካራሜትር ተባርረዋል።
ሰፈር ከነ ማህበራዊ ኑሮ ተበታትነዋል። አብዮተኛ እርምጃ ተወስዶባቸዋል ማለት ይቻላል። ይህ ለተፈናቃዮች ብቻ ሳይሆን ለመላው የአዲስ አበባ ህዝብ ምን ያህል ጎጂ እንደሆነ ይታወቃል። "Social capital" ከሰረ፤ መተባበር ጠፋ፤ መተዋወቅ ጠፋ፤ መደጋገፍ ጠፋ፤ ማህበራዊ ግብረ ገብ ጠፋ፤ ኢ-ማህበራዊነት በዛ፤ ወንጀል በዛ ወዘተ።
አንዱ ለችግሩ መፍትሄ የመሬት ፖሊሲውን መቀየር ነው።
1. ካሁን ወድያ መንግስት መሬት መውሰድ የሚችለው ለመንግስት ጥቅም እንደ መብራት፤ ውሃ፤ መንገድ ወዘተ ይሁን። ካሳውም የ«ብሎኬት ዋጋ» ሳይሆን የመሬቱ ከነቤቱ የገበያ ዋጋ መሆን አለበት።
2. መሬት ለግል ጉዳይ እንደ ኢንቬስትሜንት ከተፈለገ ኢንቬስተሩ በግል ከመሬት ባለቤቶቹ መሬቱን ተደራድሮ ይግዛ። መንግስት ጣልቃ አይግባ። ገዥ እና ሻጭ ከተስማሙ ሁለቱም ደስተኛ ይሆናሉ። ኢንቬስተሩ የገበያ ዋጋ ስለከፈለ በመሬቱ አይቀልድም አዋጪ ነገር ላይ ያውለዋል። ሻጩም ተበድያለሁ አይልም በራሴ የወሰንኩትን አገኘሁኝ ብሎ ያምናል።
የሚጠቀም ሶስተኛ ወገኖችም አሉ። መላው የአዲስ አበባ ህዝብ ከመፈናቀል የሚያመጣው ጠቅላላ ህምሞች ይተርፋል። የመንግስት ሰራተኞችም ከሙስና ፈተና ይድናሉ። ማፈናቀል ወይንም የመሬት ፖሊሲው በጠቅላላ ካድሬዎች በረካሽ አፈናቅለው በውድ ለኢንቬስተር በመስጠት ሙስና የጋበዘ ስርዓት ነበር። ፖሊሲው ከተቀየረ ሁላችንም ከዚህ ሁሉ እንተርፋለን።
Subscribe to:
Posts (Atom)