Thursday, 14 March 2019

ምሁⶂቻችን እና ልሂቃኖቻችን እንዴት እንደተደናቀፉ

ጣልያን፤ የፈረንጅ የቀለም ትምህርት እና ርዕዮት ዓለም አምልኮ፤ እና አብዮት እንዴት የምሁራን ማህበረሰባችንን እንደመነመነ።

https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/03/blog-post_38.html

ገንቢ ውይይት ከስዩም ተሾመ እና መንግስቱ አሰፋ

ይህን ገንቢ ውይይትን ተመልከቱ። ስዩም ተሾመ እና መንግስቱ አሰፋ ይህን ውይይታቸውን ዘውትር ቢያደርጉት ጥሩ ይመስለኛል። በተለይ የተለያዩ የህገ መንግስት ቅያሬዎችን ቢያሰላስሉ ጥሩ ይመስለኛል። ወደ እንደዛ አይነት ተግባራዊ ውይይት ሲገባ ደግሞ የተለያዩ እውነታዎች እና አስተያየቶች ይወጣሉና።

Tuesday, 12 March 2019

የአዲስ አበባ ህዝባዊ ድርጅት

በጄት፤ 100 ሚሊዮን ብር
አባል ቁጥር፤ አንድ ሚሊዮን
አደረጃጀት፤ አንድ ለአምስት
አካሄድ፤ ስልታዊ
ውጤት፤ ሰላም

ብራቮ ስዩም ተሾመ፤ ጸንፈኞቹ ተደራጅተው የኢትዮጵያዊነት ጎራው አለመደራጀት ነው ሀገራችንን የሚያጠፋው

ይህን ውይይት በድምብ አዳምጡት። ጸንፈኞቹ ገጀራ ይዘው ህዝቡንም መንግስትንም ሲያስፈራሩ የኢትዮጵያዊነት ጎራው ምንም ፖለቲካ ኃይል ያለው አደረጃጀት የለውም። እነ ዓቢይ ጸንፈኞቹን ትተው ኢትዮጵያዊነትን ቢከተሉ ኦዴፓ ሲዞርባቸው የሚመኩት የኢትዮጵያዊነት ኃይል የለም! ጎበዝ፤ እረ ቶሎ ብለን እንደራጅ።

፩) የ100 ሚሊዮን ብር ቡጀት
፪) አንድ ሚሊዮን አባላት
፫) አንድ ለአምስት አደረጃጀት

ይህን ካደረግን ሰላም ይሰፍናል።

«ዓቢይ ከዳን» የሚለው ትርከት ይጠቅመናል ወይ?

የኢሳት ተንታኞች ኤርሚያስ ለገሰ እና ሃብታሙ አያሌው አቢይ እየዋሸላቸው ኦዴፓ የክህደት ስራ ሰሩ የሚል ትርክት ጀምረዋል። ይህ ትርክት ለኢትዮጵያዊነት ኃይሉ እና ለአዲስ አበባ ህዝብ ትግል ይጠቅማል ዋይ ነው ጥያቄው?

እንደሚገባኝ ይህ ትርክት ሁለት አላማ አለው፤

፩) የአዲስ አበባ ህዝብ እና ሌላው የኢትዮጵያዊነት ጎራውን ለማስነሳት
፪) የዓቢይ መንግስት (እና ለማ እና ኦዴፓ) ላይ ጫና መፍጠር

እስቲ «ዓቢይ ከዳን» የሚለው ትርከት እነዚህን ግቦች ሊያሳካ ይችላል ወይ ብለን እንመልከት...

፩) «ጠላቶችን» በኃይል በመተቸት ህዝቡን ማነቃቃት እና ማስነሳት ኢሳት እና ሌሎች ለረዥም ዓመታት የሞከርነው ስልት ነው። አልሰራም ነው የምለው። የፖለቲካ ለውጡ የመጣው ህዝቡ የትግሬ የበላይነት እና የህወሓት ጭቆና ስለበቃው ነው። የበቃው ደግሞ «እየተቆንክ ነው» ስለተባለ አይደለም፤ የለት ኑሮው ስለሆነ ነው። ይህ የሚያሳየን የ«ለቅሶ ፖለቲካ» ማለትም ጨቋኝን መተቸት እና ስለ ጨቋኝ ማልቀስ ህዝቡን አያስነሳም። ስለዚህ አሁንም «አቢይ ከዳን» ማለት ህዝቡን አያስነሳም። ህዝቡ አሁን የሚያስፈልገው ጠላት አይደለም፤ ጠላቱን ያውቃል።

፪) የዓቢይ መንግስት ይህን አይነት ጫና አይመልስም። መንግስቱ/ኦዴፓ ጸንፈኞቹን የሚያስተናግደው አምኖበት ነው፤ ተገዶ ነው፤ ወይንም የረዥም እቅድ ስልት ይህን የወረ ጫና ምንም አይቀይረውም። በጸንፈኝነቱ አምኖበት ከሆነ ከኃይል በቀር ምንም አይመልሰውም። ተገዶ ከሆነ አሁንም ኃይል ነው አስገድዶ የሚመልሰው። ስልት ከሆነ ደግሞ አሁንም የኛን ጫና ignore ማድረግ ግድ ይሆንበታል ግቡ እስኪሳካ።

ሰልዚህ «ዓቢይ ከዳን» የሚለው ትርክት ግቦቹን አያሟላም። እርግት ለስሜታዊ ጩኸት እና እሮሮ ይመጫል። ግን ሰከን ብለን ካሰብነው ጥቅም የለውም።

አልፎ ተርፎ ጉዳት አለው። እንደተለመደው ገመደራጀት ስራችን distract ያደርገናል። ለ27 ዓመት እየጮህን ችግራችንን ህወሓት ላይ እያሳበብን መደራጀት አልቻልንም። እነ ዓቢይ መጥተው ህወሓትን አባረሩልን። አሁንም የመደራጀት አለምቻል በሽታችን ላይ ከማተኮር ፋንታ የ«አቢይ ከዳን» ትርክት ላይ ካተኮርን የትም እንቀራለን።

ሌላው ጉዳት ለፖለቲካዊ የዋህነት/ጅልነት እጃችንን መስጠት እና ትክክለኛ ግንዛቤ ማጣት ነው። የዓቢይ መንግስት የህወሓትን አገዛዝ ለመድገም ነው ከመጀመርያ የተነሳው ማለት እጅግ የተንሸዋረረ አመለካከት ነው። ፖለቲካ የalliance ጉዳይ ነው። ከማን ጋር ነው የምንጋራው እና ጥቅማችን የሚመሳሰለው የሚለውን ነገር አብጥረን ማወቅ አለብን። እና ዓቢይን ከነ ኦነግ ጋር መቀላቀል አደገኛ የዋህነት ነው።

ስለዚህ ሰከን እንበል። ይህ ሁሉ ችግር የመታው ባለመደራጀታችን ነው። የአንድ ዓመት እድል አልፎናል። እስካሁን የኢትዮጵያዊነት ኃይሉ እና/ወይንም የአዲስ አበባ ህዝብ 100 ሚሊዮን ብር በጄት ያለው እና ሚሊዮን አባል ያለው ድርጅት መፍጠር ነበረበት። የፓርቲ አባላትን አሰልጥኖ ቢያንስ አዲስ አበባን በአንድ ለአምስት መቆጣጠር ነበረበት። በየመዋቅሩ ሰው ነአ ድር መዘርጋት ነበረበት። ይህን ሁሉ አላደርገንም። ባልማረጋችን ነው ችግሮች የቀጠሉት። አሁንም «ዓቢይ ከዳን» ብለን ማልቀስ ይህንን ግብ አያመጣም። ዋና ግባችን ላይ ብናተኩር ይሻላል።

የሰከነ አስተያየት ስለ ዓቢይ እና ኦዴፓ

ስሜታዊ መሆን አይበጅም... ይህን የፍፁም ፈቃዱ ትክክለኛ ትንታኔ ያንብቡ።

(https://www.facebook.com/fitsum.fikadu.96/posts/2138544319567816)

ቁምነገሩ ጦርነቱን ማሸነፍ ነው

በቅድምያ በአደጋው ለተጎዳነው ሁሉ ፈጣሪ መፅናናት ይሁነን እላለሁ።አዎ እርሱው ፈጣሪ ኢትዮጵያዬን እንዲህ ካለው ሃዘን ሁሌም ይጠብቅልን እያልኩ በሰሞኑ የፖለቲካችን ፈተና ዙሪያ እንዲህ እንደሚከተለው ልል ወድጃለሁ።

የዶ/ር አብይ ቡድን ማለቴ ቲም ለማ ሃገርን አንድ ለማድረግ ከፍተኛ ትግልና ውጥረት ውስጥ ሆኖ ይታየኛል።ጁሃር (ኦነግ፣ ቄሮ) እነርሱን (ማለትም ቲም ለማን) ከኦሮሞ ህዝብ ጋር ለማጣላት ጠንክሮ እየሰራ መሆኑን አምናለሁ። እነርሱም ይህ ስለገባቸው ህውሃትን ቀስ በቀስ ድባቅ የመቱበትን ያንኑ የተለመደ ለዘብተኛ የሚመስል ግን ውስጠ ወይራ አካሄዳቸውን እየተገበሩበት ይገኛሉ። እነዚህ ብልህ መሪዎች መሬት እስከሚይዙ ድረስ ለህውሃት ተገዢና ተልመጥማጭ መስለው እንዴት አዘናግተው በጡረታ ስም ገሸሽ በማድረግ ከዚያም ጊዜ ጠብቀው እነዛኑ አይነኬ መሣይ የህውሃት መሪዎች ወደ ማሰር ውስጥ እንደገቡ ሳስብ፤ ይሄ በስሜት የሚነዳው ህዝባችን በሚፈልገው ፍጥነት ባለመሄድ ውስጥ ውጤት እንዳለ ያሳዩኛል።የእነዚህ ሰዎች አካሄድ ልክ እንደ ሺቭ ኬራ አባባል ዓይነት ነው።ማለትም፦ አሸናፊነት ማለት እያንዳንዱን የጦር ግንባር ማሸነፍ ማለት ሳይሆን ጦርነቱን ማሸነፍ ማለት ነውና።

ጁሃር በዚህም በእዛም ብሎ፤ "እኛ ከየኦሮሞ ህዝብ ጥቅምና አጀንዳ ይልቅ የምናስቀድመው የኢትዮጵያ ህዝብን አጀንዳና ጥቅም ነው" ብለው ዛሬውኑ በአደባባይ እንዲናገሩ ለማድረግ ያልወጋጋቸው ቦታ የለም። ም/ቱም ለእርሱ እንዲህ ማስባል ማለት እነርሱን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እስካሁንም በጥርጣሬ እያያቸው ካለው ከቄሮና ፅንፈኛ የኦሮሞ ብሄርተኞች ጋር ሙሉ ለሙሉ ማቆራረጥ እናም ቦታቸውን (ምርጫ ባስፈለገ ጊዜም ሆነ በአዘቦቱ ጊዜ) በኦነግ ማስቀማት ብሎም የእራሱን ርካሽ ተወዳጅነት በአክራሪ ኦሮሞ ብሄርተኞቹ መካከል ያለስጋት ማስፈን መሆኑን ስለሚያውቀው ነው።በከፍተኛ ፈተናና ጫና ውስጥ ያሉት ኢትዮጵያውያኑ ብልሆቹ መሪዎች ግን ገብቷቸዋልና፤ ቪዥናቸውን ከዳር ማድረስ እንዳለባቸው ስለሚያውቁ መረጋጋት ያለበትን በማረጋጋትና ባላንስ በመስራት ስራ ላይ ናቸው።

ኢትዮጵያውያኑ መሪዎች አዲስ አበባን ለኢትዮጵያውያን ሁሉ ብቻ በእኩል እንድትሆን እንደሚመኙ ግልፅ ማሳያው እኮ፤ መጀመሪያውኑ የኮንዶሚኒየም ዕጣ ማውጣታቸው ነው።ከዚህ በተጨማሪም አገር ሰላም ብሎ የኮንዶሚኒየም እጣ ያወጣው ደግሞ የኦዴፓ አባላቸው ማለትም ታከለ ሆኖ ሳለ ወዲያውኑ የጁሃር ጫጫታ ወደ ደም ማፋሰስ ሊሻገር መሆኑ ሲገባቸው፤ ፅንፈኞቹን ለማረጋጋትና የኦሮሞን ህዝብ ለማሳመኛ የሚሆናቸውን ጊዜ ለመግዛት የሆነ ዓይነት መግለጫ "በሌላኛው" የኦዴፖ ገፅ አውጥተው ጉዳትን ተከላክለዋል። ዳሩ ግና በስሜት የሚንቀለቀለው የህዝባችን አካል ጠረጠራቸው። እነርሱ ግን ምንተዳቸው፤ ግባቸው የብሄር ፖለቲካን ከኢትዮጵያ ምድር ለመጨረሻ ጊዜ ማጥፋት ነውና፤ ይኸው ውጥናቸው ሲሳካ ለሁሉ ምላሽ ይሆነናል በሚል ተስፋ አሁንም ዋና ስራቸው ላይ ናቸው። አዎ በብሄር ፖለቲካ ሃገራቸውን እንዲህ ቁምስቅሏን በማሳየት እያንገላታት ያለውን ኢህአዴግንም ሆነ ኦዴፓቸውን ፍርስርስ አድርገው በህብረብሄራዊ ፓርቲ መተካት ደግሞ፤ የለዘብተኛ መሳይ አካሄዳቸው የመጨረሻ ግብ በዚያውም የጁሃርም ሆነ የኦነግ አሊያም የወላጃቸው የህውሃት ወይም ደግሞ የሌሎች ዘረኛ መሰሎቻቸው ሁሉ ሃሳቦች ግብአተ መሬት እንዲሁም የኢትዮጵያዬ ትንሳዔ መሆኑ ገብቷቸዋልና፤ ለስኬቱ ትግልና ጫና ውስጥ ናቸው። እኛስ የት ነን?