Monday 24 October 2022

መልካም አስተዳደር በአማራ ክልል

 እንደሰማሁት ከ2011 ጀምሮ በአማራ ክልል በቀበሌ ደረጃ ህዝቡ የሚያስተዳድረውን የመንግስት ሹማምንቶችን በገምገም እና ካስፈለገ ማጋለጥ ጀመረ። ህዝቡ «መንግስት የህዝብ ተወካይ እና አገልጋይ ነው» ይሚለው መርህ ገብቶት መርህውን በተግባር ማዋል ጀመረ። መልካም አስተዳደር እንዲኖር እኛ እንደ ህዝብ ስራ መስራት አለብን ሃላፊነትም አለብን ብሎ አመነ። ጥሩ ንቃት ነው።

ይህን ተከትሎ ህዝቡ ሙሰኞችን መጠቆም እና ማጋለጥ ጀመረ። ግን እንደሰማሁት መንግስት ሙሰኞቹን ለፍርድ ከማቅረብ ይልቅ ወደ ሌላ ቦታ ወስዶ ሌላ ብዙ ጊዜ የተሻለ ሹመት ሰጣቸው። ህዝቡ ይህንን ተመልክቶ ታዝቦ ተስፋ ቆረጠ። በአስተዳደሩ ሃላፊነት አለብኝ ማለት ተወ እና ወደ ድሮ «አክሩፎ ዝምታ» ገባ። ሙስናው እንደገና ጀመረ።

በዚህ ታሪክ ማን ተጎዳ ብለን ከጠየቅን መልሱ ግልጽ ነው፤ ህዝቡ እና ክልሉ ነው ተጎጂው። መፍትሄ ደግሞ ከተጎጂ ነው መመንጨት ያለበት። መፍትሄው ቀላል ነው። ህዝቡ የኢ-ሙስና ትግሉን መቀታል እና ማጠንከር አለበት። ልሂቃኑ፤ ሚዲያ እና «አንቂው» ደግሞ ትግሉን መደገፍ አለበት። የፍርድ ሂደቱን ተከታትሎ ሙሰኞች የት እንደደረሱ ማጋለጥ እና ተካውሞ ማስነሳት አለበት። ተቃውሞ መንግስት ላይ ሳይሆን ሙሰኞቹ እና የሙሰኞቹ አገልጋዮች ላይ ማነጣጠር አለበት። «መንግስትን ስለምንደግግ ከነዚህ መንግስትን የማይወክሉ ሙሰኞች ልናጸዳው ይገባል» አይነት የስራ መፈክር (mission) ሊኖረው ይገባል።

ለአንድ ህብረተሰብ ጥንካሬ መልካም አስተዳደር ቁልፍ ነው። መተማመን ቁልፍ ነው። አንድነት ቁልፍ ነው። አለነዚህ ህዝቡ የተበታተነ እና ግለኛ ይሆናል ለጠላቶች ተጋላጭ ይሆናል። 

የአማራ ልሂቃን በዚህ ዋና ጉዳይ ላይ በሙሉ አቅሙ ቢሳተፍ እራሱንም ህዝቡንም ይጠቅማል። ሌሎች የማይጥቅሙ የሚጎዱ አጄንዳዎችን ትተን።

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!