Monday 20 December 2021

Not Yet In a Position Of Strength...

 ያለፈው ዓመት ታሪካችን መረጃዎቻችን የሚገልጹልን ነገር ይህን ነው፤ የኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ ገና ደካማ ነው እጅግ በጣም መጎልበት አለበት። በሁሉም ዘርፍ፤ ደህንነት፤ መከላከያ፤ አስተዳደር፤ ንቃተ ህሊና፤ አንድነት፤ ትብብር፤ መተማመን፤ ወዘተ። 

እያንዳንዱ መዋቅር፤ እያንዳንዱ ግለሰብ መድረስ ካለበት ደረጀ በታች ነው። አልፎ ተርፎ በርካታ ከሃዲ fifth column ዎች አሉን በተለይ «በተማረው» ክፍል። ለዚህ ነው ትንሿ ህወሓት 100 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ያላትን ሀገር ከባድ አደጋ ላይ የጣለችው። በድክመቶቻችን ምክንያት ነው።

ባለፈው አንድ ዓመት እጥፍ ድርብ እንደተሻሻልን አልዘነጋሁም። ሁላችንም ለውጡን አይተናል። ግን ጉዞው ገና መጀመሩ ነው። ረዥም ከባድ መንገድ ይቀረናል ጠንክረን ለኛም ለአካባቢአችንም ዘላቂ ሰላም ልናመጣ የምንችልበት ቁመና ላይ እስክንደርስ።

ስለዚህ የመንግስትም የህዝብም ዋና ትኩረትና ስራ ጠንካራ ለመሆን ስራ መስራት ላይ ነው። ሁሉም ሌሎች ጉዳዮች ከዚህ ዋና ግብ በታች መሆን አለባቸው። 

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!