Friday 5 July 2019

«መፈንቀለ መንግስት»

ፌደራል መንግስት «መፈንቀለ መንግስት» ያለው ጉዳዩን ለማካበድ እና የሚያደርገውን ኃይል እርምጃዎችን ሽፋን ለመስጠት ነው። ተገቢ ይመስለኛል።

የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት አቅሙን እጅግ ውስን ነው። የክልሎች መንግስታትም እንዲሁም። ኦነግ ባንክ ሲዘርፍ የቆየው መንግስት «ሆደ ሰፊ» ሆኖ ሳይሆን ለማስቆም አቅም ስለሌለው ነው። እርምጃ ከወሰደ ከውስጡ አቢዮት ሊነሳል ስለሚችል ብዙ የፖለቲካ ስራ በመስራት ቆይቷል። ሆኖም የሰመኑ ግድያዎች መንግስት ምን ያህል ደካማ እንደሆነ ያሳያል።

ለዚህ አይነት የደከመ መንግስት «መፈንቀለ መንግስት» የሚመጣው በdeath by a thousand cuts ነው። አሳምነው አማራ ክልልን ይቆጣጠራል። የመንግስት ደካማነት ያሳያል። መንግስት ውስጥ ያሉት ለምክዳት ዳር ያሉት ድፍረት ያገኛሉ። በሌሎች ቦታዎች አመጽ ይነሳል። ሁከት ይበዛል። እንዲህ እያለ መንግስት ይፈራርሳል። እንሆ መፈንቀለ መንግስት።

መንግስት ታላቅ የሰው ኃይል እጥረት አለው፤ ይህ ሁላችን የምናውቀው ነው። የህ የ50 ዓመት ውጤት ነው። የዓቢይ ፍላጎት ወደታች በደምብ አይደርስም። መሰረታዊ ችግር ነው። በዚህ ውክት ሁሉም ብሶተኛ ይህን ድክመት ተጠቅሞ ሁከት ማስነሳት ይሞክራል። ይህ ነው ያለፈው ዓመት ታሪክ። አሁንም ይቀጥላል።

መንግስት አሁን ስልቱን ገምግሞ ወደ ይበልጥ ኃይል እርምጃ እየገባ ይሆን ይሆናል። የአቢዮት እና ሁከት ምንጮችን አሳዶ ማስቆም ሂደቱ ሰባዊ ጉዳት ቢኖረውም። ማህበራዊ ሚዲያን ማገድ፤ ኢንተርኔትን ሳይሆን ማህበራዊ ሚዲያን። ይህ ስልት ይሰራ አይሰራ አላውቅም፤ ጉዳይ መሃል ውስጥ እና መረጃ ያላቸው እነ ዓቢይ ነው የሚያውቁት።

ግን ኢግዚአብሔር በሰላም መንግስት ሁከተኞችን ለሞቆጣጠር ይርዳቸው። መንግስት የ«ሁከተኞችን» ችግር እና ብሶት ደግሞ dismiss ከማድረግ ማዳመጥ እና ፍትህ መስጠት እንዲችል ይርዳው።

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!