Monday 10 December 2018

አዴፓ እና የመሬት ይዞታ ፖሊሲ


አቶ ንጉሱ ጥላሁን በዚህ ቃለምልልስ ዛሬ ያለው የመሬት ፖሊሲ አንዱ «ምሶሶአችን» ነው ብለዋል።

ይህን እሳቸውም ድርጅታቸውም ሌሎች አቋሞቻቸውን እንደፈተሹት እንዲፈትሹ እጠይቃለሁ። መሬት የግል ይሁን ይሉ አልልም የፖለቲካ ሁኔታው ለዛ አይነት ድምዳሜ ዛሬ የሚመች አይሆንምና። ግን አቋሙ ምሶሶ ነው አይበሉ። እየፈተሹት እየተዉት ይሄዱ።

የአማራ ገበሬ እራሱን ማሻሻል ያልቻለው እና ዝቅተኛ እስረኛ ሆኖ የቀረው ከጎረቤቱ መሬት ገዝቶ መስፋፋት እና በራሱ ላይ ኢንቬስት ማረግ ባለመቻሉ ነው። በተጨማሪ መሬት የመንግስት ይሁን የሚለው ፖሊሲ ጸንፈኛ የሆነ ዓለም ዙርያ ከአንድ ሁለት ሀገር በቀር የማይታይ ፖሊሲ ነው። አዴፓ ለዘብ ያለውን መካከለኛ መንገድ በዚህም ጉዳይ እንዲከተል እጠይቃለሁ።

https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/03/blog-post_47.html

https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/blog-post_94.html

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!