Showing posts with label brainwashing. Show all posts
Showing posts with label brainwashing. Show all posts

Tuesday, 14 December 2021

Brief Note: Ethiopian Elites and the West

Ethiopia should pursue a rational and credible foreign policy. It should rationally, not emotionally and out of revenge, re-assess its relationship with the West and engage in cooperation where interests align. But it should also credibly punish the West for what it has done. At the same time, Ethiopia should reward allies such as China who stood by it while it was under attack. Ethiopia should completely re-assess its long term geostrategic policy in light of the West's attack on it and in light of current geopolitical realities.

One of the problems Ethiopia will have as it engages in revising its foreign policy is the ideological and emotional attachment of much of its elite with the West. Before and after the Cold War, the West used its soft power, including propaganda, to capture the hearts of elites all around the world. Ethiopia was no exception. The basics of the propaganda was that the West is moral and altruistic - exceptional. It wants the best for all the world. Shocking that we believed such obviously simplistic propaganda, but we did. We developed a dangerous, irrational, emotional attachment to the West.

For the sake of peace and survival, our elite has to rid itself of this emotional irrational perception of the West. All our silly assumptions should be swept away.

Thankfully, today, most of Ethiopia has realised that the West is not any more altruistic or moral than any place else. It can be cruel and nonsensical. Its ideological Messianic complex (neocolonial impulse) can make it extremely dangerous. This realisation has to set firm roots in our psyche. For the sake of our survival and peace in our region, we should never again be so naïve.

Thursday, 14 March 2019

ምሁⶂቻችን እና ልሂቃኖቻችን እንዴት እንደተደናቀፉ

ጣልያን፤ የፈረንጅ የቀለም ትምህርት እና ርዕዮት ዓለም አምልኮ፤ እና አብዮት እንዴት የምሁራን ማህበረሰባችንን እንደመነመነ።

https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/03/blog-post_38.html

Sunday, 10 February 2019

በ«ቤተሰብ ምጣኔ» ስም የሚፈጸመው ጉዳት



 

በ«ቤተሰብ ምጣኔ» ስም በአማራ ክልል እየተፈጸመ የነበረው ማህበረሰባዊ ጉዳት ይህ ደብዳቤ / መመርያ ይገልጻል። አንብቡት።

ከዚህ ደብዳቤ የምንረዳው ዋና ነገሮች እነዚህ ይመስሉኛል፤

፩፤ የመጀመርያ ነጥብ የድርጅቱ አንዱ ግብ (target) የወሊድ መቆጣጠርያ የሚጠቀሙ ሴቶች ቁጥር መጨምር እንደሆነ ግልጽ ያደርጋል። እነዚህ ግቦች የሚመነጩት ደግሞ ከጤና ጥበቃ ቢሮ ብቻ ሳይሆኑ በዋና ደረጃ ከለጋሾቻቸው ማለትም ከተለያዩ የውጭ ሀገር ለጋሾች እንደ ኢዩ እና ዩኤሴይድ (አንድ ምሳሌ፤ http://www.healthpolicyproject.com/index.cfm?ID=country-Ethiopia)። ይህ ማለት የክልሉ መንግስት፤ የጤና ጥበቃ ቢሮ ሃላፊዎች፤ እና የጤና ቢሮ በታቾች ለገንዘብ ብለውም እንደዚህ አይነት ጉዳት የሞላው ፖሊሲ ፈጽመዋል። አዲሱ ቅኝ ግዛት እንዲህ ነው የሚሰራው።

፪፤ እነዚህን ግቦች ለመምታት በጣም ግልጽ የሆኑ ስህተቶች ተፈጽመዋል። ለምሳሌ በሁለተኛ፤ ሶስተኛ እና አምስተኛ ነጥቦች እንደሚገለጸው በረጅም ጊዜ መቆጣጠርያ ላይ የማይሆን ትኩረት ተደርጓል። የጤና ተቋሙ ገንዘቡን ለማምጣት ጸንፈኛ የሆነ አቋም እና ፖሊሲ ለማራመድ ወደኋላ አላለም። ለምሳሌ ሁሉንም ሴቶች የወሊድ መቆጣጠርያ ተጠቃሚ የማድረግ ታርጌት እና ፖሊሲ ከጫፍ የያዙ ጽንፈኝነት በቀር ሌላ ቃል ሊሰጠው ያችልም።

፫፤ ነጥብ ሰባት የጤና ጥበቃ ቢሮው እንደ ተቋምም ሰራቶኞቹም ለገንዘብ ብለው የተለያዩ የወሊድ መቆጣጠርያ እንደሚያስተዋወቁ እና ሴቶች ላይ እንደሚጭኑ በግልጽ ያስረዳል። ፖሊሲው የሚመራው ለህዝቡ ጤንነት ምን ይበጃል በሚለው መርህ ሳይሆን ምን ገንዘብ / ጉቦ ያመጣልናል በሚለው ነው። ስለዚህ የፖለሲው እና የተግባሩ አለቆች እና ወሳኞች የውጭ ሀገር ለገሾች እና የወሊድ መቆጣጠርያ ሳጭ ኩባኒያዎች ናቸው ማለት ነው።

፬፤ ይህ የብሉሹ እና የበሰበሰ አሰራር የጤና ተቋሙ ሚስኪን ሴቶች ላይ የቅስቀሳ ዘመቻ እያካሄዱ የሴቶቹ ስነ ልቦና እና ጤና የሚጎዳ ነገሮች እንዲያደርጉ እንደሚያደርግ ነጥብ ስምንት ያረጋግጣል። የጤና ጥበቃ ቢሮ ቢሮው ገንዘብ እንዲአገኝ፤ ሰራተኞቹም ለግላቸው ገንዘብ / ጉቦ / ስኮላርሺፕ እንዲያገኙ ጉዳት እንደሚፈጽሙ ግልጽ ነው።

፭፤ የአማራ ህዝብ ልሂቃኑን በደምብ መፈተሽ እና ማስተካከል እንዳለበት ግልጽ ነው። ከላይ ደጋግሜ የገንዘብ ሚና እንዴት የአማራ ጤና ጥበቃ ቢሮ የውጭ ሀገር ለጋሾች እና የመድሃኔት ሻጮች መሳርያ እንዲሆን እንዳደረገ ገለጽኩኝ። ገን ከዚም አልፎ ተርፎ በርካቶች በርዕዮት ዓለም ደረጃ በዚህ ጸንፈኛ ፖሊሲ የሚያምኑ የአማራ «የተማሩ» ልሂቃን አሉ። ከሁሉም በላይ ይህ ነው የሚያሳዝነው። ልሂቃኖቻችን በበአድ አስተሳሰብ አዕምሮአቸው ተገዝቷል። ወደ ኋላ ብለው የጠጡትን ፕሮፓጋንዳ መፈተሽም አይችሉም። የህዝብ ቁጥር ምጣኔ ከሌላ አንጻር መመልከትም አይችሉም። ህዝቡ እራሱ የራሱን የቤተሰብ ምጣኔ መወሰን እንደሚችል፤ ሃብታም በሆነ ቁጥር እራሱ የሚወልደውን ቁጥር እንደሚቀንስ፤ የቤተሰብ ምጣኔ የህዝብ ቁጥርም መቀነስ ጉዳይ አለመሆኑ፤ ወዘተ መገንዘብ የማይችል ልሂቃን ተፈጥሯል። የህዝቡን ስነ ልቦና እና ማህበረሰባዊ እሴቶች የማያውቅ ልሂቃን ተፈጥሯል። በዚህ ላይ ብዙ ስራ ሊሰራ የሚያስፈልግ ይመስለኛል።

Thursday, 10 January 2019

በምሁራችን ተስፋ እንቁረጥ?

እስቲ ይህን የምጸሃፍ ትችት ያንብቡ፡ https://www.ethiopiaobserver.com/2019/01/06/book-review-overcoming-agricultural-and-food-crises-in-ethiopia/

የመጸሃፉ ጸሃፊ የኢትዮጵያ የእርሻ ምርት ችግር የኦርቶዶክስ ኃይማኖት ነው ይላል? ምሁራኖቻችን ከዚህ የፈረንጅ ማርክሲስት የ60 ዓመት በፊት አስተሳሰብ መውጣት አቅቷቸዋልን? ያሳዝናል።

ለ40 ዓመታት ኢትዮጵያ የተመራቸው በዚህ አይነት አስተሳሰብ ነው። የእርሻ ምርታችን እንደወረደ ነው። ታድያ አሁንም ምክንያቱ ቤተ ክርስቲያን ነው? እስቲ ምሁራን ትንሽ indoctrinate ካደረጋችሁ መጸሃፍት ውጡ እና imaginative ሁኑ። ምናልባት ወደ ወጋችን ብትመለሱ እና እሴቶቻችንን ብትመለከቱ መናባችሁ መስራት ይጀምር ይሆናል።

እስቲ ገበሬዎቻችንን እግዚአብሔር የሰጣቸውን ነጻነት እንስጣቸው። ከ43 ዓመት በፊት የነጠቅናቸውን መሬት እንመልስላቸው። ባለቤት እናንተ ናችሁ እንበል። ከዛ እንተዋቸው ድጋር ካስፈለጋቸው እንርዳቸው። እርስ በርስ መሻሻጥ ከፈለጉ ያድርጉት። ህበረቶች መፍጠፍ ከፈለጉ ያድርጉ። መንግስት/ወረዳ/ቀበሌ ጉዳያቸውስጥ አይግባ። እስቲ በዚህ እንጀምር።

ገቤሮዎቻችን የባህል እስረኞች አይደሉም። ለ43 ዓመት የመንግስት የማርክሲዝም የሞደርኒዝም እስረኞች ሆነው ቆይተዋል። በራሳቸው መሬት እና ክህሎት ኢንቬስት እንዳያደርጉ ተደርግዋል። ምሁራኖቻችን በትዕቢት የራሳቸውን ፍላጎት ጭነውባቸዋል። ከዛ ደግሞ ባህላቸውን እና ወጋቸውን ይተቻሉ! ህም።

Wednesday, 21 March 2018

«ሴኩላሪዝም»

ትንሽ አመታት በፊት አንድ የመንግስት ስራተኛ የሆነ ዘመዴ የኦርቶዶክስ መዝሙር ከመስሪያቤት ኮምፕዩተሩ ላይ ማዳመጥ ክልክል እንደተደረገ ነገረኝ። ለምን ብዬ ስጠይቀው ክርስትያኑም ሙስሊሙም የሚፈልገውን መዝሙር፤ ስብከት፤ ትምሕርት እያዳመጠ እና ኮምፕዩተሩ ላይ ሥዕል እየለጠፈ የሰራተኞች እርስ በርስ ግጭት ሊፈጥር ይችላል ተብሎ ተከለከለ አለኝ። የሚገርመው ነገር ግን 1) ከመስሪያቤቱ እንደዚህ አይነት ግጭቶች አልነበሩም እና 2) ክልከላው በተራ ትዛዝ ሳይሆን ከከፍ ያለ የአስተዳደር ደረጃ በመመርያ ምልክ የተላለፈ ነበር። የመመርያው ርዕስ ደግሞ «ሴኩላሪዝም» ነበር።

ይህን ታሪክ ስሰማ እጅግ አዘንኩኝ። መቼ ነው መንግስቶቻችን፤ ምሁሮቻችን እና ልሂቆቻችን የምዕራብ ዓለም ርዕዮት ዓለምና ፍልስፍና ይዘው አገራችን ላይ መጫን የሚያቆሙት? ካለፉት የ100 ዓመታት ታሪካችን አይማሩምን?

እስቲ «ሴኩላሪዝም» ባጭሩ ምን እንደሆነ እንመልከት። «ሴኩላሪዝም በዓለማችን እግዚአብሔር የለም/አይሳተፍም ብሎ ማሰብ ነው»። ሴኩላሪዝም እግዚህብሔር ሊኖር ላይኖርም ይችላል ግን ከዓለማችን ከሕይወታችን ከለት ኑሮአችንም አይሳተፍም የሚለው አመለካከት ነው። እግዚአብሔር ካለ እዛው ከዙፋኑ ወይንም ገነቱ ተቀምጦ ይመለከተናል። በሃይማኖት እና በእግዚአብሔር በግል ምርጫችን ልናምንባቸው የምንችል የእምነት ሥርዓቶች ናቸው። በሀሳብ ደረጃ ነው የምናምንባቸው ካላሰኘን ደግሞ ከሀሳባችን እናስወግዳቸዋለን!

ይህ አስተሳሰብ በተለያየ መንገድ ወደ ክርስትያን የሆነውን አስተሳሰብ ገብቷል። «ዓለማዊ» እና «መንፋሳዊ» የምንላቸው ቃላት በተሳሳተ መንገድ እንጠቀማለን። ዓለማዊ ስንል ስራችን፤ ትምሕርታችን፤ ገበያችን፤ ንግዳችን ወዘተ ነው። እግዚአብሔር እነዚ ነገሮች ውስጥ እንዳለ አናምንም። ስለዚህም ነው በነዚህ የህይወት ዘርፎቻችን ኢ-ክርስትያናዊ ነገሮች እያደረግን እያለን አማኞች ነን የምንለው። እሁድ እሁድ ግን ቤተ ክርስትያን ሄደን ወደ መንፈሳዊስ ዓለም እንሸጋገራለን። እዛ ጨዋ ነን፤ ጥሩ ስነ መግባር አለን፤ ጭንቀቶቻችንን አስተንፍሰን ወደ ዓለማችን እንመለሳለን።

ይህ ግን የውሸት ክርስትና ነው። በእምነታችን እግዚአብሔር በሁሉም ቦታ በሁሉም ነገር አለ። «እኔ የቅርብ አምላክ ነኝ እንጂ የሩቅ አምላክ አይደለሁም። ሰው በስውር ቢሸሸግ፥ እኔ አላየውምን? ሰማይንና ምድርንስ የሞላሁ እኔ አይደለሁምን? ይላል እግዚአብሔር።» ኤር 23:23-24።

ስለዚህ ትምሕርት ቤት ብሄድ፤ መስሪያ ቦታ ብሄድ፤ እርሻዬ ላይ ብሆን፤ ትራንስፖርት ላይ ብሆን፤ መጠጥ ቤት ብሄድ፤ በሁሉም ቦታ እግዚአብሔር አለ። ሕይወታችንን እግዚአብሔር ያለበትና የሌለበት ብለን ልንከፋፍለው አንችልም። በሁሉም ቦታ በሁሉ ደቂቃ ከኛ ጋር ነውና።

ይህ የሚያሳየን የሰው ልጅ ክርስትያንም ሴኩላሪስትም አብሮ ሊሆን አይችልም። ብዙዎቻችን ወደዚህ ስህተት ብንገባም ሊሆን የማይችል ነገር ነው። ለክርስትያኖች እግዚአብሔር ልኬት የለውምና። በተጨማሪ ሴኩላሪዝም እግዚአብሔርን ከለት ኑሮአችን ማጥፋት ስለሚፈልግ የክርስትና ተቃራኒ ብቻ ሳይሆን ጠላት እንደሆነ ግልጽ ነው።

«እናንተ ኦርቶዶክሶች፤ ሙስሊሞች፤ ፕሮቴስታንቶች አብሮ መኖር አትችሉም። ስለዚህም (እግዚአብሔራን ተክቼ!) ከላያችሁ ሆኜ አስተዳድራችኋለሁ» ይላል ሴኩላሪዝም / ሴኩላሪስቱ። «እኔ ነኝ ስልጡኑ፤ ከማንም ጋር የማልጋጨው፤ ከሁሉም ጋር የምግባባው፤ ሁሉንም የማከብረው» ይላል። እውነቱ ግን ሴኩላሪስቱ እንደዚህ ሲል ሁሉንም በሰላም ለመጠበቅ ሳይሆን አላማው ይህን አስመስሎ «እግዚአብሔር የለም» የሚባለውን ሃይማኖትን ለማስፋፋት ነው። እግዚአብሔር ከአዕምሮአችን ብቻ ነው ያለው እንጂ ከስራ ቦታችን፤ ገበያ ቦታችን፤ መንገዶቻችን፤ ሚዲያዎቻችን፤ ከለት ኑሮአችን የለም ብለን ካመንን ቀጥሎ እግዚአብሔር የትም የለም ማለት የሚቀጥለው ቀላል እርምጃ ነውና!

በተጨማሪ እግዚአብሔር ከለት ኑሮአችን ከሌለ የማህበረሰብ የአገራችን ድንጋጌዎች ከየት ሊመጡ ነው? ከሴኩላሪዝም ርዕዮት ዓለም ከ«እግዚአብሔር የለም» ሃይማኖት ሊመጡ ነው! አያችሁ ሴኩላሪዝም እራሱን ገለልተኛ አድርጎ እንዴት «እግዚአብሔር የለም» ሃይማኖትን ሰተት ብሎ እንደሚያሰፍን።

ኢትዮጵያ የሃይማኖት አገር ናት። ታሪካችን ትውፊታችን ከዚህ የተያያዘ ነው። ማንነታችን ይህ ነው። ሴኩላሪዝም ደግሞ የህን አፍርሶ «እግዚአብሔር የለም» ሃይማኖትን ነው ማስፈን የሚፈልገው። ይህ ሂደት እንዴት እንደሚሰራ ለማወቅ የምዕራብ ዓለሙን ያለፈውን 400 መቶ ዓመት ታሪክ መመልከት ነው። ስለዚህ ሴኩላሪዝም ኢ-ኢትይጵያዊ እንደሆነ ተረድተን ወደ አገራችን ሰተት ብሎ እንዳይገባ መጠንቀቅ አለብን። በተለይ ደግሞ ወደ ልባችን ሰተት ብሎ እንዳይገባ መጠንቀቅ አለብን።

Friday, 16 February 2018

ጨቋኝና ተጨቋኝ

እንደተረዳሁት ባለፈው ባወጣው መግለጫ ኦህዴድ የኢትዮጵያ መሰረታዊ የጭቆና ታሪክ የ«መደብ ጭቆና» ነበር እንጂ የ«ብሄር ጭቆና» አልነበረም ብሏል። ለዚህ አቋማቸው ኦህዴድን አደንቃለው አመሰግናለውም። ከረዥም ዓመታት የተሳሳተ እምነታቸው መቀየር ከባድ ነውና ጥንካሬና ህሊና ይጠይቃል። ዛሬ በሃገራችን ያለውን ከፍተኛና ኢ-ጤናማ የጎሳ ውጥረትንም ተገንዝበው የተሳሳተ ርእዮተ ዓለማቸውን ገምግመው ሃሳባቸውን ቀይረው ይህንን በይፋ ማውጣታቸው ትልቅ ነገር ነው። ደግሞ ከሌሎች አጋር ፓርቲዎቻቸው ቀድመው ይህን ማድረጋቸውም ሊደነቅላቸው ይገባል። እነ ለማ መገርሳ ለኢትዮጵያዊነት ታላቅ አስተዋጾ እያደረጉ ነው።

ሆኖም ይህ ዜና በሃገራችን መሰረታዊ የሆነ አሳዛኝ አስተሳሰብ አሁንም እንዳለ ይገልጻል? «ጨቋኝ» እና «ተጨቋኝ» እራሱ የተሳሳተ ቋንቋ ነው። ጽንሰ ሃሳብ የመጣው ከውሸትና ኢባህላዊ የሆነ የምእራባዊ የኮምዩኒስት አስተሳሰብ የመነጨ ነው። እስቲ አንድ እርምጃ ወደ ኋላ ተመልሰን ለምንድነው የሰው ታሪክ በ«ጨቋኝና ተጨቋኝ» የሚለው አስተሳሰብ መወሰን ያለበት? እንደዚህ አይነቱ አስተሳሰብ በሃሳብም ደረጃ በተግባርም ግጭት፤ ቅሬታ፤ ቂም፤ ጦርነት፤ ግድያ፤ አብዮት ወዘተ የሚያስገድድ ነው። አንድነት፤ ፍቅር፤ ይቅርታ፤ ትህትና፤ መስማማት ወዘተ የሚቃረን አስተሳሰብ ነው።

አልፎ ተርፎ ማን ግለሰብም ህብረተሰብም ፍፁም ንፁሃን ፍፁም ጥፋተኛ የሆነ የለም። እያንዳዳችን ጨቁነናል ተጭቁነናል፤ በድለናል ተበድለናል፤ ወደናል ተወደናል፤ ተስማምተናል ተጣልተናል፤ ተሳስተናል ስታታችንን አምነን ይቅርታ ጠይቀናል፤ ቂም ይዘናል ይቅርታን ተቀብለናል። በዚህ ዓለም እኔ ነኝ ንጹ ተጨቋኝ የሚል የራሱን ጥፋት ስለማይመለከት ወደ ከባድ ጥፋጡስት ይገባል ሰፊ በደልም ይፈጽማል።

በዚህ ጉዳይ ታላቅ የሩሲያ ደራሲ አለክሳንደር ሶልዠኒትሲን ያሉትን በደምብ ሊገባን ይገባል፤
ከእስርቤታችን አልጋ የሆነው የበሰበሰው ገለባ ላይ ጋደም ብዬ ነው ለመጀመርያ ከውስጤ የበጎ መንፈስ የተሰማኝ። ቀስ በቀስ መረዳት የጀመርኩት ይህ ነው፤ ጥሩና ክፉን የሚለየው መስመር በሀገሮች፤ መደቦች፤ የፖለቲካ ፓርቲዎችም መካከል አይደለም የሚያልፈው፤ ይህ መስመር የሚያልፈው በያንዳንዱ የሰው ልብ መኻል ነው። መስመሩ እድሜአችን በሙሉ ከውስጣችን ወደፊት ወደኋላ ይላል። በክፉ የተሞሉ ልቦችም ቢያንስ ቅንጣት ያህል ጥሩነት ይኖራል፤ ከሁሉም ጥሩ ከሚባለውም ልብ ከአንድ ጥጓ ትንሽ ክፉነት ይኖራል።
በየቦታው እየዞሩ ያሉ ክፉ ስራ የሚሰሩ ክፉ ሰዎች ቢኖሩና እነሱን ከኛ መለየትና ማጥፋት ብቻ ቢሆን ኖሮ እንዴት ቀላል ነበር? ግን ጥሩና ክፉን የሚለየው መስመር ከያንዳንዱ የሰው ልጅ ልብ መካከል ነው የሚያልፈውና ማን አለ ከራሱ ልብ ቁራጭ ቆርጦ ለማጥፋት ፈቃደኛ ይሆነ?
ሶልዘኒትሲን ኮምዩኒስት የነበሩ ወታደር የነበሩ ስታሊን ለዓመታት በሞት እስር ቤት (ጉላግ) ያሰራቸው ከሩሲያ ወደ ኦርቶዶክስ ሃይማኖታቸው የተመለሱ የሩሲያ ጀግና ነበሩ። ተጨቋኝ ነኝ ማለት የሚገባቸው ነበሩ። ለሃገረቸው ጦርነት ተዋግተው በማግስቱ የታሰሩ ናቸው። አለምንም ጥርጥር ተጨቋኝ ነኝ ማለት የሚገባቸው ነበር። ግን እስር ቤት የሌሎችን ሳይሆን የራሳቸውን ኃጢያት እንዲገለጽላቸው አደረገ! የሰው ልጅ እውነተኛ ባሕርይ እንዲረዱ አደረገ። የሰው ልጅ ችግርም እንዴት መቅረፍ እንደሚቻል ገባቸው። በጦርነት፤ በማስወገድ፤ በማባረር፤ በመወገን ሳይሆን በንስሃ፤ በመስማማት፤ በመከባበር፤ በመቻቻል ነው።

ይህ ሩሲያዊ ሶልዠኒትሲን የዘመኑን «ጭቋኝና ተጨቋኝ» አስተሳሰብን ትተው የእውነትን ባህላዊ የኢትዮጵያዊ አስተሳሰብ ነው የገለጹት። ሩሲያዊው ኦርቶዶክስ ባህላችንን ያስታውሱን። ለምንናውም የኢትዮጵያ ባህል፤ ማንኛውም ሃይማኖት፤ ይህ የ«ጨቋኝና ተጨቋኝ» ርእዮተ ዓለም በአድ ነው። በአድ ነው። ሚስኪኖቹ የጃንሆይ ተመሪዎች ወደ ሃገራችን ከምእራብ ሃገራት ያመጡት መርዝ ነው። መርዙን እናውጣው። ወደ እራሳችን እንመለስ።

Friday, 10 November 2017

The News Makes Us Dumb (and serfs)

My father was, I think it's safe to say, an intellectual - an Ethiopian intellectual. Like in many homes of Ethiopian intellectuals, in our home, amateur politics and philosophy was often the topic of conversation. Between my father and I, our friends and guests, during visits, lunches, and dinners, it was a time when, where two or three (Ethiopian men) are gathered, politics is present.

We also watched the news. Not much else. Maybe a comedy here, and perhaps a cowboy and Indian show for nostalgia's sake. But news was king. And when we moved to North America, then we really got our fill of news. And plenty of political commentary.

As you might expect, we thought of ourselves as quite smart. We were the news watchers. We knew what was going on. We were serious. We were cosmopolitan. We were intellectuals. Our neighbours couldn't even point out Mexico on a map, and there we knew most of the world capitals. We even watched the US presidential debates - of the nominees! How smart we were.

Of course, this was all nonsense. We followed "the news" in exactly in the same way as the housewife followed soap operas or the youth followed sports. We were passive onlookers onto an activity on which we had no influence and had no stake, but fooled ourselves into thinking that merely watching meant something! But no, the news, was really a form of entertainment - mindless (and heartless) entertainment and escapism. Gossip that pretended to be something else. Passive and numbing brainwashing. No better than a soap opera. Actually worse - most soap opera watchers are under no illusion that they are doing something worthwhile!

Today, I don't watch TV and don't follow the news. On the internet, once in a while I quickly browse the headlines on a few sites - none of them mainstream. But sometimes, I find myself entranced and feeling the urge to delve a little into the news/gossip, and I have to stop myself.

Nevertheless, it was on the internet of course that I stumbled upon this old article: Why The News Makes Us Dumb. I encourage you all to read it. And turn off the news. Never watch CNN; if you see it on a television screen where you happen to it, flee!  Don't let your mind be colonized. If you have the spare time to burn, go have a chat with your neighbour. It would do you and him much more good than staring at the TV.

Tuesday, 7 November 2017

The Ethiopian Intellectual - Lost and Adrift

A Facebook post that I read yesterday reminded me of something that's been repeated in Ethiopian intellectual circles for decades, but still bears repeating because the problem its speaks of is still among our major problems, if not the most important problem in Ethiopia.

With age and experience, being a product of 'modern' education, that is, modern as an ideology, with every passing year I realize more and more how much our minds - the minds of Ethiopian 'intellectuals' (the quotes are for me) - have been colonized by what we might call modern or foreign (mostly Western) education. Even those of us who decry modernity's influence on Ethiopia, who decry our maladaptation of foreign mindsets, theories, and practices, are so much formed by these influences that are foreign to Ethiopia that we even express our concerns in foreign terms!

The problem with the foreign and modern mindset is not just that it is foreign and modern. The problem is that it is alien and therefore goes against the inertia of thousands of years of  Ethiopianness - however one defines Ethiopianness.

Let's take the idea of the modern 'democracy', an idea that most of us have fallen in love with at some time or another,  as an example. First of all, to even define and understand the idea properly, one would need to be immersed in the context in which the idea evolved. That is, an Ethiopian academic born and raised in Ethiopia, even if he was educated in the West, and even if his father, and even his grandfather, were products of Western education, cannot understand the idea of democracy in a way that a Briton or American can. The Ethiopian's understanding will always be somewhat superficial and so his application of these ideas will always be somewhat flawed.

Secondly, at the level of the society at large, not just the Western educated intellectuals, the understanding of democracy would be even more superficial because the idea, as it is, is so foreign. I say 'as it is', because of course there are ideas within democracy that are also part of Ethiopian tradition, or that are even universal, but the total idea of Western democracy remains foreign and difficult for the Ethiopian to fully absorb, let alone practice.

Third, and most importantly, the foreignness of Western democracy means that, sui generis, it cannot be a good fit in Ethiopia. That is, it did not evolve out of Ethiopian tradition, to address Ethiopian needs, to address Ethiopian problems, etc. It may have excellent ideas - it may itself be an excellent idea - but, as a whole idea, it remains foreign and as such cannot be a  prescription for an Ethiopian problem or any Ethiopian problems. That is not to say that something that looks like democracy may not be good for Ethiopia, but this something, whatever it is, will not come about by bringing the idea of democracy into Ethiopia, or adjusting it to Ethiopia. It will come about by looking at Ethiopia as it is and thinking about what social change, if any, would be good for it.

Ironically, those intellectuals who have warned us against being colonized by Western mindsets were often foreigners themselves. One of them, the great Donald Levine, summarised these sentiments in one of my favourite quotes:
“The vitality of a people springs from feeling at home in its culture and from a sense of kinship with its past. The negation of all those sentiments acquired in childhood leaves man adrift, a prey to random images and destructive impulses… The most productive and liberating sort of social change is that built on continuity with the past.”
Levine used to always recount a conversation he had with a modern Ethiopian intellectual or student in the 1960's. This student, presumably upset by the injustice of the policies of the Imperial Government, and at the same time suitably brainwashed, like most of his contemporaries, by some version of communism, remarked to Levine that the best thing for Ethiopia would be communism. Levine, like an elder of sorts, reminded the modern Ethiopian that communism requires revolutions that usually cost tens of thousands of lives. The modern Ethiopian replied that let alone tens of thousands of lives, millions of lives would not be too great a sacrifice to bring about communism to Ethiopia! Levine, as a lover of Ethiopian tradition, was shocked and alarmed to hear such a sentiment from the cream of Ethiopia's crop.

You see, Ethiopian intellectuals, given a background of relative poverty and backwardness from the point of view of the world today and the inferiority complex that comes with it, in order to run as fast as we can away from our seemingly insurmountable problems, run blindly, like a deer chased by a lion, into the arms of foreign ideas and ideologies. And then, we quickly become more Catholic than the Pope, so to speak. We become the most radical Communists, or radical ethnic nationalists, or worshippers of 'democracy', etc. We become so attached to these 'pretty', foreign, ideas. This, if not anything, illustrates how dangerous and incompatible foreign ideas are with being Ethiopian.

So I, myself, I try to flee back, back to being Ethiopia. I try my best to cling to my childhood sentiments, so to speak, even if my modern mindset rebels. It is the safe, the tried and true, the resilient and robust approach. I ask Ethiopian intellectuals to do the same. And I hope and pray that those not infected by modern education can avoid the infection!