Friday 11 November 2022

ቅራኔአችሁን እንፍታላችሁ!

በተለይ ከ1997 ከቅንጅት ዘመን በኋላ ምእራባውያን ማለትም መንግስታት፤ ኤንጂኦዎች፤ ወዘተ ኢትዮጵያዊያን የግትርነት እና የቅራኔ ማባባስ ባህል አላቸው ብለው ያወሩ ነበር። በአንጻሩ እኛ ምእራባውያን በጠቅላላ የፖለቲካ ስልጣኔ በተለይም በቅራኔ መፍታት conflict resolution ጎበዝ ስለሆንን እናንተን ኢትዮጵያውያን እናስተምራችሁ አሉ። በርካታ ስብሰባዎች ትምሕርቶች በብዙ ገንዘብ ወጪ ተካሄዱ። ውጤቱ....

(በነገራችን ላይ እኔም በግሌ ይህ ባህላዊ ችግር አለን ብዬ አምኜ የፈረንጆቹን እርዳታ እንጠቀም ከሚሉት አንዱ ነበርኩኝ።)

ባህል ውስብስብ ነገር ነው። የእገሌ ባህል እንዲህ ነው የእገሌ ባህል እንዲያ ነው በደፈናው ማለት አይቻልም። ሁኔታዎች ሁሉንም ግለሰብም ቡድኖችንም ይቀይራል። እንሆ እነዚህ የቅራኔ መፍታት ባለሙያዎች ምእራባውያን ዛሬ ትክክለኛ ግትርነት ምን እንደሆነ እያሳዩን ነው። በከንቱ ዓለምን ንዩክሊየር ጦርነት ጫፍ ላይ አድርሰዋልና!

እኛ ኢትዮጵያውያን ወዲህ ወድያ ከማየት እራሳችንን ከምእራባውያን ይሁን ከምስራቃውያን ከማነጻጸር ወደ ራሳችን ተመልክተን በራሳችን እሴቶች ተጠቅመን እራሳችን ላይ ብንሰራ ይበጃል። ከሌሎች ጥሩ ነገር መማር ጥሩ ነው ተፈጥርዋዊም ነው። ግን ብዙ ጊዜ ይህ ከጥሩ ነገር መማር አልፎ ወደ ማነጻጸር ይሻገራል እና ሁለት «ኮምፕሌክሶች» ያሳድራል፤ 1) ሌሎች በደፈናው ይበልጡናል ብሎ ማሰብ 2) የራስን እሴቶችን አለማየት። እና ማነጻጸር አደገኛ ልምድ ይሆናል ከእውነታ እንድንርቅ ያደርገናል። ስለዚህ ብዙ ግራ ከኝ ሳንመለከት ችግራችንን በራሳችን በቂ የሆኑ እሴቶች መፍታት ጥሩ አካሄድ ይመስለኛል።

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!