Monday 29 August 2016

ፑቲኖቻችን የት አሉ?

2008/12/6 ዓ.ም. (2016/8/12)

የሶቪዬት ህብረት ከወደቀ ብኋላ ምእራቡ ዓለም በተለይ አሜሪካ ሩሲያኖችን እንረዳችኋለን፤ ኤኮኖሚአችሁ እንዲታደስና እንዲያድግ እንረዳችኋለን፤ ወደ ዓለም ኤኮኖሚ በቀላሉ እንድትቀላቀሉ እናደርጋለን፤ የቀዝቃዛ ጦርንነትን ለማፍረስ ስለተባበራችሁን ሩሲያ በጠቅላላ እንድትበለጽግ እናደርጋለን ብለው ቃላቸውን ሰጡ። ነገር ግን ቃላቸውን አጥፈው በሩሲያ ሀገር አፍራሽና ህዝብ ጎጂ የሆነ አመራርና መርህ በሀገሪቷ እንዲሰፍን ገፋፉ። በዚህ ምክንያት የሩሲያ ህዝብ የአስር ዓመት በላይ የስቃይ ዘመን አሳለፈ። ስቃይ ስል ህዝቡ ደህይቶ የሚበላውን ያጣበት፤ ወንጀልና ሽብርተኝነት የሰፈነበት፤ ህዝቡ ጤና አጥቶ የአማካኝ የህይወት እድሜ ከ70 ወደ60 የወረደበት፤ ሙስናና የማፊያ (ትብብር ወንጀል) ሥረዓት የሞላበት ሀገር ሆና ነበር ሩሲያ።

በዚህ የሩሲያ ስቃይ ዘመን የሀገሪቷ መሪ ፕሬዚደንት ቦሪስ ዬልትሲን ነበሩ። በ1991ዓ.ም. ከስልጣን በፈቃዳቸው ወረዱና ምክትላቸውን ቨላዲሚር ፑቲንን ፕሬዚደንት እንዲሆን ወከሉ። የዬልትሲን ደጋፊዎች የሆኑት በመንግስት አመራር ውስጥ የነበሩት ትላልቅ ባለ ሀብቶች የውጭ ሀገር «ንጂኦ» አንቀሳቃሾች የምዕራብ ሀገር መንግስታት ሁሉም ፑቲን በአስተሳብም በርዕዮት ዓለምም በእምነትም የዬልትሲን ተቃራኒ እንደሆነ ዓገር ወዳጅ እንደሆነ አልጠረጠሩም ነበር! በኢትዮጵያ ሁናቴ ለማምሳሰል ያህል መለስ ዜናዊ ይልቃል ጌትነትን ወይም ሌላ ተቃዋሚ ሾሙ እንደማለት ነው!

ይህ እንዴት ሊሆን ቻለ? እንዴት ዬልትሲንና ዙሪያቸው ያሉት መሪዎች ደጋፊዎች ባለሟሎችና የውጭ ሀገር መንግስታት የፑቲንን የእውነት ባህሪና አቋም አላወቁም? ምክንያቱ ቀላል ነው፤ ፑቲን እራሱን አላገለጠም። ማንነቱን በሚያስፈልገው መጠን ሰውሮ ነበር። ይልቁኑ በዬልትሲን መንግስት በተለያየ ቦታዎች ሲያገለግል ጎልማሳው ፑቲን በታታሪነትና በዓለቃን ማክበርና በተለይ ለዓለቃ ያለው ታማኝነት ነበር የሚታወቀው። ከአመራር ወስጥ ያሉትና ከየሀገሩ ገዥ የነበሩት ባለሃብቶች («የሩሲያ ቢሊዮኔሮች» የተባሉት) በደምብ ይግባባ ነበር። ከመጠን በላይ ብልጥም ፖሊቲካ የገባውም ነበር። በፍጹም አልተጠረጠረም!

ቨላዲሚር ፑቲን ፕሬዚደንትም ሲሆኑ የእውነት አቋሞቻቸውን ወድያው አላሳዩም። በመጀመርያ ስልጣናቸውን ቀስ በቀስ አጠናከሩ። ጓደኛ እንጂ ጠላት የማያፈራ መርህዎችን አራመዱ። አሸባሪዮችን አጠቁና የጦርሰራዊት የፖሊስና የጸጥታ ኃይሎችን ድጋፍ አረጋገጡ። ከምዕራብ ሀገሮች ጋር በጸረ ሽብርተኝነት ሩሲያ በደምብ እንድትተባር አደረጉና የምዕራብ መንግስታትንም ድጋፍ አገኙ። ከዚያ ቆይተው ፑቲን ስልጣናቸውን ካረጋገጡ በኋላ በዬልትሲን ዘመን በዝርፍያና በሙስና ያደጉት ባለሀብቶችን በማሳሰር በማሳመን ስልጣናቸውን ነጠቁ አጠፉ። እነዚህ እርምጃዎች የፑቲንን የህዝብ ድጋፍ መጠን በጣም እንዲልቅ አደረጉ (ስልጣን ከያዙ ጅምሮ ከ65 እስቀ 80 በመቶ ድጋር አላቸው)።

ከዬልትሲን ወደ ፑቲን የተካሄደው የሩሲያ ለውጥ ከሞላ ጎደል ሰላማዊ ነበር። እንዲሁም በኢትዮጵያ የሚፈለገው ሰላማዊ፤ ማንም የማይጠቃበት፤ ሀገር የማይረበሽበት፤ ጥላቻ የማይሰፍንበት፤ ቅራኔ የምያሳንስና መግባባት ለዘብተኝነት መቻቻል የምያጠቃልል ለውጥ ነው።

እንደዚህ አይነት ለውጥ የሚመጣው ከዓብዮት ሳይሆን ከውስጣዊ ቀስ በቀስ የሚመጣ ለውጥ ነው። ለንደዚህ አይነት ለውት የነባር መንግስት ውስጥ በርካታ የለውጥ አጋሮች ያስፈልጋሉ፦ ፑቲኖች ያስፈልጋሉ! ሥርዓቱ ሲናጋ ውግያና ሁከት ለማምጣት ወደኋላ የማይሉ አክራሪዮች ስልጣን እንድይዙ ውይም በውሳኔ ላይ እንዲያመዝኑ ያደርጋል። ይህ እንዳይከሰት እነዚህ የውስጥ ለውጥ የሚፈልጉ ለዘብተኛ የሆኑት አስፈላጊ ናቸው። አክራሪውም በለዘብተኛው እንደተከበበ ሲያይ ግድ ይመለሳል።

ነገር ግን እንደዚህ ሰርጎ ገብተው የሚያገለግሉ ሰዎች የራሳቸውን ህልውና ለመጠበቅና ይበልጥ ረጅም አላማቸው እንዳይከሽፍ ብለው እራሳቸውን መደበቅ አለባቸው። እዚህ ላይ ብልጠት ያስፈልጋል። መሪዎቻቸውን መምሰል አለባቸው። አለጊዘው ስልጣናቸውና የስልጣን ድራቸውን በቂ ሳያስፋፉ ሳያጠነክሩ ጠንካራ አቋም መውሰድ የለባቸውም። እንደ ፑቲን ስያስፈልግ አንገታቸውን ደፍተው መኖር አለእባቸው። «እንደ እባብ ብልዖች እንደ ርግብ የዋሃን ሁኑ» ውይም «ዛሬ ህይወትን ካጡ ወደፊት መታግል አይቻልም» እንደሚባለው።

በዚህ ጊዜ ብዙሐናም «ተቃዋሚዎች»ም ብልህ መሆን አለባቸው። ከውስጥ የስውር ጠቃዎሚዎች በይፋ እየተሟገቱ በስውር መተባበር አለባቸው። አንድ ነገር ማስታወስ አለብን፤ ዋናው የኢትዮጵያ ፖሊቲካ ችግር የተሳትፎ ጉዳይ ነው። ህዝቡ መሪውን ሲጠላ ከመንግስት ወስጥ ከመሳተፍ ይርቃል። «ፖለቲካና ኮሬንቲ» የሚባለው ስሜት ያመዝናል። ይህ ማለት በርካታ የኢትዮጵያ ህዝብ ወገኑን ውይም የሃሳብ አጋሩን ከመንግስት ወስጥ የለም። በታችኞቹ የመንግስት አካሎችም እንደ ቀበሌና ወረዳ ለመሳትፍ አይፈልግም ቤተሰቡም ዘመዱም እንዲሳተፍ አይፈልግም። መንግስትን «ለሌሎች» ትቶት በብአድ እየተገዛ ነው። ይህ አስተሳሰብ ተገቢ የሆነ የታሪክ ምክንያት ቢኖረውም ትክክል አይደለምም እጅግ ጎጂም ነው። አለመሳተፍ አክራሪነትንና ዓብዮትን የሚጋብዝ ለዘብትኘትና ትብብርን ቦታ የሚያሳጣ አስተሳሰብ ነው።

«እንዴት ኢህአዴግ ውስጥ መስራት ይቻላል፤ ሕሊናን መሸጥ ወይም ጥቃትን መቀበል ያስፈልጋል» ሊባል ይችላል። ታድያ በሰሞኑን የጎንደር ተቃውሞ ላይ የኃይል እርምጃ እንዳይወሰድ ያደረጉት ማን ናቸው? አልፎ ተርፎ በኢትዮጵያ ጦር ሰራዊት ወስጥ ያሉት በዝቅተኛ የስልጣን ደረጃ ያሉት ወታደሮች በአብዛኛው ማናቸው ከየት ናቸውም? በየቀበለውና ወረዳ የሚያስተዳደሩት (ከትግራይ ክልል በስተቀር) ማናቸው? የታወቀው ኢህአዴግን ለቆ የወጣው ኤርሚያስ ለገሰ ማን ነው? አምባሳደር ሆኖ በግዞት ወደ ቱርኪ የተላኩት አቶ አያሌው ጎበዜ ማን ናቸው? ለነገሩ ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ማናቸው? እነዚህ በሙሉ የለውጥ አጋሮች ወይም ሁኔታዎች ሲፈቅዱ የለውጥ አጋሮች ሊሆኑ የሚችሉ ናቸው!

መርሳት የለለብን የኢህአዴግ መንግስት የአናሳ መንግስት እንደሆነ ነው (በዚህ ካልተስማማን የህዝበ ድጋፍ አላቸው ብለን አመንን ማለት ነው!)። ኢህአዴግ መላ የኢትዮጵያን ህዝብን እንወክላለን ባይ ነው ግን ተቃዋሚዎችና በርካታ ህዝብ የትግራይ መንግስት ነው ብሎ ይከሰዋል። አናሳ ነው ብለን ከተቀበልን ማውቅ ያለብን አናሳ መንግስት ሀገርን መግዛት የሚችለው ሌላው ህዝብ ከፈቀደለትና በደምብ ከተባበረው ብቻ ነው! ኢህአዴግ እንደ ደርግ አለብልሃት በመጭፍለቅ ብቻ መግዛት አይችልም። ኢህአዴግ የሌላው አለመተባበር ውይም ከፖሊቲካ መራቅ ውይም በፈቃደኝነት መገዛት ያስፈልገዋል። ይህ ውነታን በግልፅ የሚያንጸባርቀው ኢህአዴግ ፓርቲውም ጦርሰራዊቱም በቁጥር ደረጃ በአብዛኛው የትግርኛ ተናጋሪ አለመሆኑ ነው።

ስለዚህ ኢህአዴግ ውስጥ ገብቶ ወዲያው ሳይሆን ከስ ብሎ ልውጥ ማምጣት ካልሆነም የለውጥ አጋር መሆን እንደሚቻል ግልፅ ነው። ህዝቡ ይግባ፤ ይሳተፍ፤ ሲያስፈልግ አንገቱን ደፍቶ እሺ ይበል፤ ቀስ ብሎ በስልጥ አብዛኛነትን ያረጋግጥና ጊዘው ሲደርስ ለውጥ ያመጣል።

ከፑቲን የምንማረው ትምህርት የህ ነው። ፑቲን ለዬልትሲን መንግስት ሲያገለግል ብቸኛ የውስጥ ተቃዋሚ አልነበሩም ሊሆኑም አይችሉም ነበር። ፕሪዚደንት ፑቲን ሲሾሙ እንድርሱ አንገታቸውን ደፍተው የመትፎ አገዛዙን ውስጥ ለውስጥ የሚሸረሽሩ ሀገር ወዳድ ይሆኑ ትናንሽ ፑቲኖች አብረው ተነሱና ፑቲንን ደግፈው አላማቸውን አራመዱ። ፑቲን ብቻቸውን ቢሆኑና የሳቸውን አላማ የሚደግፍ ከሥርዓቱ ውስጥ ባይኖሩ የትም አይደርስም ነበር።

በተዘዋዋሪ በሰሞኑ በአማራ ክልል በተካሄደው ተቃውሞ ሰልፎች ምክንያት አንዳንድ የህወሓት ተንታኒዎች ብአዴን በሰላይዎችና በከሃዲውች የተሞላ ነውና ጽዳት (በሌላ ቃል እስራና ግድያ) ያስፈልገዋል ብለው ይተቻሉ! ውነት ነው ህወሓት ለ26 ዓመት በመግዛቱ በፖሊቲካ ስልጥ ከሌላው ልቋልና እንደዚህ አይነት ነገር ቶሎ ነው የሚገባው። ሌላውም ሊገባው ይገባል።

መጀመርያ የታተመው ከዚህ

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!