Sunday 21 October 2018

የዜግነት ፖለቲካ ከባድ ነው!

አንታለል፤ የዜግነት ፖለቲካ ከባድ ነው። የንጉሳዊ አገዛዝ እና ማርክሲዝምን የለመደ ህብረተስብን ወደ ዜግነት ፖለቲካ ማስገባት ግዙፍ ሸክም መጎተት ማለት ነው። የዜግነት ፖለቲካ እንደ ጎሳ ፖለቲካ ተጨቁነናል፤ ተንቀናል፤ ደምና አጥንታትችን አንድ ነው፤ ሀገሪቷ ችግር ውስጥ አለች እና እየተጠቃን ነው ስለዚህ ወደኛ ተሸግሸጉ፤ ወዘተ ብሎ ድጋፍ መሰብሰብ ያችልም።

1. የዜግነት ፖለኢትካ primordial አይደለም። ህዝብን ሆ! ብሎ መሰብሰብ አይችልም። ስልት ያስፈልገዋል። ስልት አያስፈልገኝም እና በstreet ፖለቲካ ልሳተፍ ማለት አይችልም። ይህ ውድቅ የነ አካሄድ ነው።

2. የዜግነት ፖለቲካ ከጎሳ ፖለቲካ ጋር ያለው ግንኝነት asymmetric ነው። ከጎሳ ፖለቲካ ጋር በተመሳሳይ ታክቲክ ፊትለፊት ግብ ግብ ልግባ ካለ ይሸነፋል። ምክንያቱ የጎሳ ፖለቲካ የስሜታዊ advantage አለው። ለምሳሌ 1) የጎሳ ፖለቲካ ከተተቸ «ጎሳዬ እየተጠቃ ነው» ብሎ ይጮሃል። እንዲህ ሲጮህ ለዘበተኞቹንም ወደሱ ሊያመጣ ይችላል። 2) የሀገሪቷ ጠቅላላ ሁኔታ (ፖለቲካ፤ ኤኮኖሚ፤ ጸትታ ወዘተ) እየተበላሸ ከሄደ የጎሳ ፖለቲካ «የነሱ የጠላቶቻችን ጥፋት ነው» ይላል። «ወደኛ ተሸሸጉ» ይላል። እንዲህ በማለት ተከታይ ይሰበስባል። ስለዚህ ይህን asymmetric ሁኔታ ተገንዝበን ተገቢውን ስልት መጠቀም አለብን።
ሁሉም የኢትዮጵያ ፖለቲካ ከቅራኔ መፍታት ዘገምተኝነት በሽታ ይጠቃል (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/09/blog-post_21.html)። ምቀኝነት፤ በግልጽ አለመነጋገር፤ አለመቆርቆር (empathy)። መጠርጠር። ሃሳብ እና ግለሰብን ማቆራኘት። ወገናዊነት። ስም ማጥፋት። ቂም። ግትርነነት ወዘተ። በነዚህ ምክንያት በርካታ ጊዜ የራሳችንን ጥቅምንም እንጎዳለን ሌላውን ለማጥቃት ስንል! በዚህ ምክንያት ነው አብሮ መስራት፤ ቅራኔ መፍታት እና win-win ሁኔታዎችን ማየት እና መፍጠር የሚያቅተን። ይገ ዜግነት ፖለቲካም የጎሳ ፖለቲካም እነዚህን ችግሮችን ማሸነፍ አለባቸው። ግን ለጎሳ ፖለቲካ ይቀላል። «ጠላት አለን» የሚባለው ነገር ሰውን ሳይፈልግም እንዲተባበር ያደርጋል። የሚአይተባበሩ ደግሞ ሀውሓት፤ ሻዕቢያ፤ ኦነግ ሌሎች የጎሳ ድርጅቶች እንዳሳዩት በቀላሉ ይረሸናሉ። የ 'survival' ጉዳይ ነው ተብሎ ይሳበባል። የዜግነት ፖለቲካ ግን ይህን አማራጭ የለውም። ከባድ የሆነውን የፖለቲካ ባህል ለውጥ ስራን ግድ መስራት አለበት።

3. የዜግነት ፖለቲካ ለዘብተኛ እና መካከለኛውን መንገድ መውሰድ አለበት። ጽንፈኝነት በጎሰኞቹ ተቆጣጥሯልና። የዜግነት ፖለቲካ ሁሉንም አይነት ፍላጎት በተቻለ ቁጥር ሚዛን ላይ አድርጎ ማስተናገድ አለበት። «ትልቅ ዛንጥላ» መሆን አለበት፤ አቃፊ መሆን አለበት። የዜግነት ፖለቲካ የማስወገድ፤ የመግደል፤ የመረሸን፤ የመጨቆን፤ የማጥቃት ወዘተ አማራጭ የለውን። እንዲዚህ ነገር ውስጥ ከገባ የዜግነት ፖለቲካ ማንነቱን ያጣልና የጎሰኝነት ፖለቲካውን ይሆናል። በጎሳ ፖለቲካው ይሸነፋል። ምሳሌ ልስጥ፤ ዛሬ ዜግነት ፖለቲካ ደጋፊዎች ሁለት አይነት አስተሳሰብ አለ ስለ ጎሳ ፖለቲካ። የአንዱ አቋም «ህገ መንግስቱ ዛሬውኑ ካልተቀየረ አቃቂ ዘራፍ» የሚል ነው። ብዚህ ጉዳይ ድርድር የለም ይላል። ሌላው ጎራ ደግሞ «ህገ መንግስቱ መቀየር አለበት ግን ይህን ለማድረግ ገና አሁን ወቅቱ አይደለም፤ መጀመርያ ንግግር እና ድርድር ማድረግ አለብን» ይላል። ሁለተኛው ነው ለዘብተኛውም ሚዛናዊውም መንገድ። ይህ ለዜግነት ፖለቲካ ግድ ነው።

4. ችግር እና ሁከት የዜግነት ፖለቲካን ይጎዳል የጎሳ ፖለቲካን ያጠነክራል። (ያው ይህ ይሚያስኬደው እንደ ኢትዮጵያ አይነት የጎሳ ፖለቲካ ያለበት ሀገር ነው።) ችግር ሲኖር ሰው ወደ ጎሳ የመሸግሸግ ባህሪ አለው። የደርግ ሁከት እነ ሻዕቢያ፤ ህወሓት እና ኦነግን በጣም አጠነከረ። ዛሬም አማራ ላይ ጥቃት ሲፈጸም የአማራ ብሄርተኝነት ንቅናቄ እየጠነከረ ይሄዳል። ስለዚህ የዜግነት ፖለቲካ በአብዮት መምጣት አይችልም አብዮት ሁከት ነውና። ብዙዎቻችን ኢህአዴግ በአብዮት («ስር ነቀል ለውጥ») መገልበጥ አለበት ስንል የአብዮቱ ውጤት የዜግነት ፖለቲካ ይሆናል ብለን አስበን ነበር። ይህ ታላቅ ስህተት ነው። ዛሬም የዜግነት ፖለቲካ ጭላንጭል ማየት የቻልነው ለውጡ አለ አብዮት ስለመጣ ነው። አለ ሁከት ስለመጣ ነው።

5. ሁላችንም እንደምናውቀው የዜግነት ፖለቲካ አራማጆች እስካሁን ታሪካችን ጥሩ አይደለም። ፖለቲከኞቻችን፤ ጋዜጠኞቻችን አክቲቪስቶቻችንም አብሮ መስራት አልቻሉም። የቅንጅት ታሪክ ይህን ታላቅ ሽንፈታችንን በድምብ ይገልጻል። ይህ በመሆኑ ዛሬ የዜግነት ፖለቲካ ድርጅቶች እጅግ ደካማ ናቸው። የዜግነት ፖለቲካ የሚደግፈው ብዙሃን ብዙ ነው፤ ይህ የቅንጅት ታሪክም ይመሰክራል። ግን ይህ ግዙፍ ብዙሃን በድርጅት፤ ልሂቃን እና ፖለቲከኛ በአግባቡ አልተወከለም። ስለዚህ ዛኢረ የዜግነት ፖለቲካ የመጀመርያ ግብ መዋቅር ማለትም ድርጅትን ማጠንከር ነው መሆን ያለበት። አለ በቂ መደራጀት ምንም ማድረግ አይቻልምና። ሁሉም የዜግነት ፖለቲካ ተቀናቃኞች ሙሉ አቅማቸውን (resources) በዚህ ጉዳይ ላይ ማዋል አለባቸው። ምርጫ የለም። ሌሎች የጊዜያዊ ስራዎች ውሃ ቀዳ ውሃ ድፋ ነው የሚሆነው። ለዜግነት ፖለቲካ strong organizations are a precondition to any success።

6. የዜግነት ፖለቲካ ገና መደራጀት ላይ ስለሆነ ጠላትን ማፍራት የለበትም። እንደ ጠ/ሚ አቢይ ሁሉንም ማቀፍ መቻል አለበት። ጠላት ካፈራ የመደራጀት ስራው ይደናቀፋል። ስለዚህ ሌሎችን በአግባቡ በጥሩ ሁኔታ ይዞ የራሱን ስራ መስራት ነው ያለበት። ይህ basic ፖለቲካ ነው ግን አንዳንዶቻችን ፖለቲካን እንደ ሃይማኖት ጥቁር እና ነጭ አድርገን ስለምናይ ወደ ቀላል ስህተት እንገግባለን። ገና ሳንደራጅ፤ ገና ሳንጠነክር ወደ ጦርነት ካልገባን እንላለን። ይህ ለዜግነት ፖለቲካ አይሆንም።

7. «የወሬ ፖለቲካ» ለዜግነት ፖለቲካ አይሆንም። የወሬ ፖለቲካ ማለት ተቃራኒዎችን በወሬ ዘመቻ ማጥቃት እና የራስን ወገን እንደ ሰለባ አድርጎ ማውራት። የጥላቻ ፖለቲካ ማለት ነው። የወረ ፖለቲካ አላማው ህዝቡ ተናዶ እንዲነሳ ማድረግ ነው። ካላይ እንዳስረዳሁት ህይ አይነት አካሄድ ለጎሳ ፖለቲካ ነው የሚጠቅመው እንጂ የዜግነት ፖለቲካ (ስሜታዊ ስላልሆነ) እንዲህ አይሰራም። ለዚህ ደግሞ የ27 ዓመት ማስረጃ አለን። ለ27 ዓመት እኛ ተቃዋሚዎች ወያኔ ሴጣን ነው ብለን ብንቾህ ምንም አልሰራም። ለውጡ የመጣው ህዝቡ የትግሬ የባላይነት በተግባር ሰልችቶት ነው እንጂ ኢሳት ስለነገረው አይደለም። ለ27 ዓመት ስለ ወያኔ ከማውራት አቅማችንን በመደራጀት ስራ ብናውል ወያኔ ገና ድሮ ወርዶ ነበር።

8. አንዱ ከላይ ከጠቀስኳቸው የፖለቲካ «ጎጂ ባህሎች» የሁሉም አሸናፊ (win-win) ውጤት አለማወቅ ነው። ይህ እንዳልኩት የዜግነት ፖለቲከኞች እና ተቀናቃኞች ይበልጥ የሚጠቁበት በሽታ ነው። (የጎሳ ፖለቲከኞች በጎሳ ስሜት ስለሚቆጣጠሩ ይህ ችግር ቢኖራቸውም አነስተኛ ነው።) ይህ በቅንጅት እና ቀጥሎ ባለው ታሪክ በደምብ ይታያል። ገና ትንካሬ ሳይሰበሰብ ስለ ፖለቲካ ክፍፍል ማሰብ፤ ስለ ስልጣን ማሰብ። ትንሽ ስልጣን በግዙፍ መዋቀር ከሚኖረኝ ትልቅ ስልጣን በባዶ መዋቀር ይሻላል የሚል አስተሳሰብ ነው። ይህን ማስወገድ ማለት አለብን። አብሮ ከሰራን ትልቁን ውጤት አምጥተን ለሁላችንም በቂ ስልጣን ይኖራል (ፖለቲከኞች)።

9. ባለፉት የ50 ዓመት የፖለቲካ ታሪካችን በተለይም አብዮት እና ሁከት የዜግነት ፖለቲካ ወይንም የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ልሂቃን ጎራ ተገድሎ፤ ተሰድዶ፤ እርስ በርስ ተፋጅቶ ቁጥሩ መንኗል (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/03/blog-post_38.html)። የዜግነት ፖለቲካ መዋቅሮቻችን የደከሙበት ምክነያት አንዱ ይህ ነው። እነ ኃይሉ ሻውል፤ ብርሃኑ ነጋ እና ልደቱ አያሌው የቅንጅት ዋና መሪዎች ሆነው ሲገኙ በሺዎች የሚቆጠሩ የፖለቲካ ልሂቃን ሞትዋል፤ ተሰዷል ወይን ፖለቲካ ኮሬንቲ ነው ብሎ ትቶታል። ስለዚህ እነ ብርሃኑ ነጋ ከዚህ የተረፉት ጥቂቶች ናቸው። እነሱ ሲደናቀፉ የሚደግፋቸው ወይንም ቦታቸውን የሚወስድ ማንም አልነበረም። የህ የልሂቃኑ መመንመን ዛሬም ሚና ይጫወታል። ሁለት የዜግነት ፖለቲካ ልሂቃን ትውልድ ነው ያጣነው። አዲሱ ትውልድም «አለ አሳዳጊ» ነው ያደገው። ይህን ችግር ተገንዝብን የሚያስፈልገውን የአካሄድ ለውጦች ማድረግ ይኖርብናል።

10. እውናትዊ የዜግነት ፖለቲካ ለብዙ አይነት ሃሳቦች መቆርቆር አለበት (empathy)። ሚዛናዊ መሆን ስላለበት። አንዱ የብዙ የዜግነት ፖለቲካ ተከታዮች ችግር ለጎሳ ፖለቲካ ምንም አለመቆርቆር ነው። የጎሳ ፖለቲካ ከዘረኝነት ውጭ ምን እንደሆነ አይገባንም ወይንም ሊገባን አንፈልግም። ይህ ታልቅ ድክመት ነው። ሌላውን አለማወቅ፤ ተቃራኒውን በአግባቡ አለማወቅ ታልቅ ሽንፈትን ያመጣል። የጎሳ ፖለቲካ ዓለም ዙርያ ያለ ነገር ነው ከነ አውሮፓ እና ሰሜን አሜሪካ። «ዘረኝነት ነው» ብሎ መሰየሙ የውሸት ማቅለልያ ነው (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2017/11/whats-ethnic-nationalism-again.html)። እውነት ነው በርካታ ዘረኞች የሆኑ ጎሳ ብሄርተኞች አሉ። ግን «ዘረኝነት» የጎሳ ፖለቲካን ሙሉ በሙሉ አይገልጸውም። የጎሳ ብሄርተኝነት ጎሳውን እንደ ሀገር (nation) ማየት ማለት ነው። ይህ ደግሞ ስሜት ነው፤ ማንነት ነው። እንደዚህ አይነት ነገር በlogical ሙግት አይቀየርም። ስልት ያስፈልጋል። ለዘብተኞቹን ማቀፍ ያስፈልጋል። ህዝብን በመቀላቀል አንዱ የሌላውን ቋንቋ እንዲያውቅ ብማድረግ የሃገር ውስጥ መዘዋወር እንዲጨምር በማድረግ ህዝብ እንዲወሃድ መባድረግ ነው ችግሩ የሚፈታው። ዝም ብሎ መጮህ ጉዳት ነው የሚያመጣው። የለዘብተኛ (moderate) አስተሳሰብ ነው እንዲህ አይነቱን ነገር ሊገነዘብ የሚችለው።

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!