…ከእሾህ ወይን ከኩርንችትስ በለስ ይለቀማልን?
ሌላ ሰውን በኛን ሃሳብ ለማሳመን ስንሞክር ከአንደበታችን ይልቅ ስራችን ማለትም ምሳሌአችን ነው ዋና ሚና የሚጫወተው። ምንም ጥሩ ሃሳቦች ቢኖሩን፤ ምንም ጥሩ አቀራረብ ቢኖረንም፤ ሃሳባችንን በተግባር የምናውል ጥሩ ምሳሌ ካልሆንን ማንም አይሰማንም፤ አያምነንም፤ አይከተለንም።
በ«ኢትዮጵያዊነት» ወይንም በ«ኢትዮጵያ ብሄርተኝነት» የምናምነው ይህን ነጥብ ጠንቅቀን ብናሰብበት ጥሩ ይመስለኝም። የኛም የኢትዮጵያም ህልውናን ይመለከታልና። የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ፖለቲካ ታሪካችን የእርስ በርስ (አለ ጥሩ ምክንያት) መቃረን እና መጋጨት ነው (http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/07/blog-post_31.html)። በኃይለ ሥላሴ ዘመን ሹማምንቶቹ እየተጣሉ ለፍርድ እና ለዳኝነት ጃንሆይ ደጅ ረዥም ሰልፍ ይሰለፉ ነበር። ዛሬም የፖለቲካ ድርጅቶቻችን ከሚገባው ማለትም ብዙሃን ደጋፊዎቻቸው ቁጥር አንጻር እጅግ ደካማ ናቸው የመሰባሰብ፤ መወያየት፤ መስማማት እና መተባበር አቅማችን ደካማ ስለሆነ። ይህ የሚያሳየው የኛ የኢትዮጵያ ብሄርተኞች የረዥም ዓመታት የንትርክ፤ የመጣላት፤ የአለመተማመን ወዘተ ታሪክን ነው።
ይህን ታሪክ ሁሉም አይቶታል እና ያውቀዋል። በተለይም የጎሳ ብሄርተኞች (ጸንፈኛም ለዘብተኛም) የሚባሉት ከኛ «ተቃራኒ» የፖለቲካ አቋም ያላቸው ይህንን የኛ ደካማ የፖለቲካ ጠባይ አይተውታክ። ንቀውናልም ማለት ይቻላል። በአንጻሩ እኛ እነሱን «ዘረኛ አትሆኑ»፤ «በግለሰብ እኩልነት እና መብት እመኑ፤ «ከኛ ሰላማዊ እና ፍትሃዊ አቋም ተማሩ» ወዘተ እንላቸዋለን። ግን በጎሳ አስተዳደር የሚያምኑት እኛን የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ሲያዩ እርስ በርስ ስንጣላ እና ስንለያይ ነው የሚያዩት። ከኛ ጥሩ ምሳሌ አያዩም። ታድያ እንዴት እኛ የምንለውን ሊያምኑ እና ሊከተሉ ይችላሉ። ይከብዳቸዋል።
ግን እኛ ጥሩ ምሳሌ ብንሆን፤ የፖለቲካ ጎራችን ንፁ ቢሆን፤ እርስ በርስ ያለን ግንኙነት በፍቅር እና በሰላም የተሞላ ቢሆን የጎሳ ብሄርተኞችም ሌሎችም ወደኛ አቋም ይበልጥ ይሳቡ ነበር። «የነሱ አስተሳሰብ ይህንን ሰላም እና ስልጣኔ የሚያመጣ ከሆነ እኛም ወደነሱ እንጠጋ እና ከዚህ ብልጽግና እንካፈል» ይሉ ነበር። «እውነትም ፖለቲካ አቋማቸው ልክ መሆን አለበት» ይሉ ነበር።
ስለዚህ አሁን ባለው እና በሚመጣው የፖለቲካ ግንባታ እና ውድድር በደንብ ከመግባታችን በፊት እኛ የኢትዮጵያ ብሄርተኞች መጀመርያ እራሳችንን መፈተሽ አለብን። ቀጥሎ የነ ጠ/ሚ አብይን ምሳሌ ተከትለን ንስሃ ገብተን ይቅርታ መጠየቅ ያለብን ይመስለኛል በህዝቡ ዘንድ እምኔታ ለማግኘት እና ህሊናችንን ለማርካት። እኛ ፍፁም ነን ችግሩ ከኢህአዴግ፤ ህወሓት፤ ደርግ ወዘተ ነበር ማለቱ ልክ አይደለምም አዋጪም አይደለም። እውነታ የሆነውን የኛ ታሪካዊ ጥፋቶችን ልክ እንደ ጠ/ሚ አብይ አምነን፤ ተቀብለን መናገር አለብን። ከዚህ በኋላ ነው የፖለቲካ እንቅስቃሴአችን ውጤታማ መሆን የሚችለው።
የሰላም ክፍሌ ይትባረክ ብሎግ፤ ስለ ሀገራችን ኢትዮጵያ ያለኝን ትናንሽ ሀሳቦች በትህትና አቀርባለሁ። ለስሕተቶቼም በቅድሚያ ይቅርታ እጠይቃለሁ
Showing posts with label እራስን መመርመር. Show all posts
Showing posts with label እራስን መመርመር. Show all posts
Friday, 14 September 2018
Sunday, 15 July 2018
የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ጥፋታችንን ካላመንን ካላስተካከልን ኢትዮጵያን ዳግም እንሸጣታለን
ያለፉት 60 ዓመት የኢትዮጵያ ብሄርተኛ የፖለቲካ ጎራው ታሪክ እጅግ አሳዛኝ እና አሳፋሪ ነው። ከዛ በፊት እስከ ወደ 1955 ሀገራችን ዓለም ዙርያ የተከበረች ነበረች። በዲፕሎማሲ፤ በሀገራዊ ኃይል ወዘተ ከአቅሟ በላይ የምትሰራ ነበረች። አንድ አንድ ምሳሌዎች፤
1. የበርካታ የዓለም ሀገሮች ተቃውሞ በላቀ የዲፕሎማሲ ስራ አሸንፋ ኤርትራን ወደ ኢትዮጵያ መለሰች። ይህ የዲፕሎማሲ ድል ከሀገራችን ከአቅማችን አስር እጥፍ በላይ ነበር ግን አደረግነው።
2. የአፍሪካ ቁንጮ ሆንን ሁሉም የአፍሪካ ሀገራት እኛን እንደ ምሳሌ ያይን ነበር። በዲፕሎማሲ እና ሀገር ኃይል ደረጃ ብቻ ሳይሆን በታሪክ እና ባህል። ይህ ክብሬታ ለኢትዮጵያ ብዙ ጠቅሟታል።
3. በዓለም ዙርያ ያሉት ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያኖች ስብሰባ አቀደች የኦሪዬንታል ኦርቶዶክስ ስብሰባውን አከናወነች ስምምነቶች አስፈጸመች።
ከ1955 አካባቢ በኋላ ግን እኛ የኢትዮጵያ ብሄርተኖች እርስ በርስ በመጣላት ሀገራችንን ድራሹን አጥፍተናል። መጀመርያ አስፈላጊ የፖለቲካ ለውጦች ባለማድረግ ቀጥሎ ልዩነቶቻችንን በጡንቻ በማካሄድ ሀገራችንን አሳልፈን ለጎሳ ብሄርተኞች ሰጠን። የመጨረሻ ውጤት ምን ሆነ ሻዕብያ እና ወያኔ የሀገራችን 10%ን ወክለው ኢትዮጵያን ተቆጣጠሩት። ይህ ለኛ 90% እጅግ አሳፋሪ ክስተት ነበር አሁንም ነው።
ይህ ታሪክ እንዳለ ሆኖ አሁን ያለፉትን ስህተቶቻችንን ለማርም የሀገራችን ሆደ ሰፊ ብዙሃን እና እግዚአብሔር ዳግም ለማረም እድሉን ሰጥተውናል። ሆንም አንታረምም ብለናል። ዋናው እና መሰረታዊ ችግራችን ያለፉትን አሳፋሪ ድርጊታችንን አለማመናችን ነው ሰው ችግሩን ካላመኑ መፍትሔ አያገኝምና። ጥፋቶቻችንን ላለማምን እና ለመደበቅ ብለን ይመስለኛል ሁል ጊዜ ለችሮቻችን ወያኔ፤ ሻዕብያ፤ ኦነግ፤ «አሜሪካ»፤ ሩሲያ፤ ኤርትራ፤ «አራብ ሀገራት» ወዘተን የምንወቅሰው። እኛ የገዛ ቤታችንን በር ከፍተን እነዚህ ደብተው እንደፈለጉት ሲያደርጉ በራችንን እንዴት ተከፈተ እንዝጋው ከማለት ለሚን ይገባሉ ብለን መጮህ! ዋናው ጣፍቱ የኛ እንደሆነ እናውቃለን ግን እፍረታችን ከባድ ነው መሸሽ ብቻ ነው የምንፈልገው።
ለማስተዋስ ያህል ባለፈው ኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት አንድ የኤርትራ የጦር አዛዥ ያለው ነገር አለ። አንድ ኤርትራዊ አስር ኢትዮጵያዊ ዋጋ አለው ብሎ ፎከረ። ይህ አዲስ ፉከራ አልነበረም በደርግ ጦርነት ላይ የተመሰረተ ነው። የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ምን ያህል እንደተናቁ ነው የሚያሳየው። ድሮ ኤርትራ በሰላም ያጠቃለልን ዛሬ ይቀልዱምን ጀመረ። እስከ ዛሬ በጦር ሜዳ ብቻ ሳይሆን በሌሎች የፖለቲካ ዋይንም የንግድ ዘርፎች በሙሉ ኤርትራዊዎችም ትግሬዎችም እደዚህ ያስባሉ። እኛ ደደብ አህዮች እነሱ አስር እጥፍ ጎበዝ። ከኢትዮጵያዊዎች ብልጥ፤ ጠንካራ፤ የተማርን ወዘተ ነን ብለው ያስባሉ። ይህ የተሳሳተ አስተሳሰብ ግን የነሱ ጥፋት አይደለም። በፍፁም የነሱ ጥፋት አይደለም። እኛ እርስ በርስ ተጨራርሰን እራሳችንን ከታላቅ ህዝብ እና ሀገር ወደ ደካማ ለማኝ ስላወረድን እነሱ የሚያዩትን እውነታ ነው የሚናገሩት። ይህ ለኛ እጅግ አሳፋሪ ነው።
የሰው ልጅ ግን እፍረቱ ስለሚያሳምመው ሊደብቀው ይፈልጋል። ለችግሮቹ ሃላፊነት ከመውሰድ ሁል ጊዜ በውነትም በውሸትም ሌሎችን ይወነጅላል። እኛም አሳፋሪ ድርጊቶቻችንን እና ውድቀታችንን ለመደበቅ ያህል ለ27 ዓመት መጀመርያ ሻዕብያን፤ ኦነግን፤ ወያኔን ወዘተ እየወቀስን ቆይተናል። አሁንም እግዚአብሔር የማይገባንን ጠንካራ የድሮ ዘመን አይነት ኢትዮጵያዊ መሪ ልኮልን አሁን ላሉን ችግሮች ህወሓትን እንወቅሳለን! እንደ ወቀሳችን መጠን ህወሓት ማንም የማይሳነው ግዙፍ ኃይል እንዲመስለን አድርገናል! (ግን 6% ነው የሚወክለው እንላለን!) የራሳችንን ድክመንት ለመሸፈን ላለማየት ለህወሓት የሌለውን አቅም ፈጠርንለት የሌለውን ጥንካሬ ሰየምንለት።
አሁንም እዛው ላይ ነን። አሁንም ከኢትዮጵያ ብሄርተኛ ፖለቲከኛ ተንታኝ አስር ጽሁፎች ካነበብን አስሩም ስለ «ሌሎች»፤ ወያኔ፤ ጎሰኞች፤ ኦነጎች ወዘተ ለቅሶ ነው። እንጂ አንድም ስለራሳችን ጥፋቶች እና ማረምያኦች የሚናገር የሚጽፍ የለም። ኢሳትን ከተመለከትን ስለ«ጠላት» ለቅሶ ነው። ጋዜቶች ሌሎች ማህበራዊ ሚዲያዎች እንዲሁ። የኛ የ«ተፎካካሪ» ድርጅቶች ወሬም እንዲሁ ምናላባትም ይብሳል። እንደ ሚና እና አቅም የሌላው ተጨቋኞች ማልቀስ፤ ማልቀስ፤ ማልቀስ።
እንደዚህ በማድረግ ለራሳችን ጥልቅ የሆነ የእፍረት ጉድጓድ ቆፍረናል። የራሳችን ህልውና በራሳችን ሳይሆን በሌሎች የተቆጣጠረ ነው ብለናል። እነዚህ ሌሎች ደግሞ ከኛ እጅግ አናሳ የሆኑ ናቸው። ይህ አስተሳሰብ ግልጽ የሆነ የዝቅተኝነት መንፈስ እንዲያድርብን አድርጓል። እውነት ነው በተፈጥሮ ሻ'ዕብያዎች፤ ወያኔዎች፤ ኦነጎች ወዘተ ከኛ ይሻላሉ ይበልጣሉ ብለን አምነናል! ይህን የተሳሳተ እምነት የገባንበት ለችግሮቻችን በሙሉ እነሱን ፈላጭ ቆራች እራሳችንን አቅመ ቢስ ስለምናደርግ ነው። ይህ የዝቅተኝነት መንፈስ የሚፈጥረውን እፍረት ለመሸፈን ደግሞ እንደገና እነሱ ላይ እንወርዳለን ከእፍረታችን ለመሸሽ ብለን። ይህ "vicious cycle" ሆኖናል ማቆም ያልቻልነው ሱስ ሆኖናል። የድሮ መሪዎቻችን (ከነ ስህተቾቻቸው) ይህን ቢያዩ ኢትዮጵያዊ መሆናችንን የሚያምኑ አይመስለኝም።
እግዚአብሔር ችር ነው እና አሁን በራሱ የሚኮራ፤ ሃላፊነት የሚወስድ፤ ጥፋቱን የሚያምን፤ ለጥፋቶቹ ንስሃ ገብቶ ይቅርታ የሚጠይቅ፤ ሌሎችን ለራሱ ጥፋቶች እና ችግሮች ከመውቀስ እራሱን በተገቢው ወቅሶ መፍትሔውን ፈልጎ አግኝቶ ስራ ላይ የሚያውል ጀግና መሪ ሰጥቶናል። ለኛ ለኢትዮጵያ ብሄርተኞች ምሳሌ ሊሆን የሚገባን መሪ። ከ60 ዓመት ጥፋታችን በኋላ አሁንም እራሳችንን ለማረም እድል ተሰጥቶናል። ይገርማል!
አሁን የ60 ዓመት ጥፋታችን ውጤት ግልጽ ሊሆንልን ይገባል። እኛ የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ተዝናንተን አድሃሪ፤ ተራማጅ፤ ደርግ፤ ኢዲኡ፤ ኢህአፓ፤ ሜሶን ወዘተ እየተባባልን ተጨራረስን። ባቃጠልነው ባዶ ሜዳ የጎሳ ብሄርተኞች ገቡ። አሁንም የሀገራችን ታላቅ የፖለቲካ ችግር የጎሳ ብሄርተኝነት ነው ብለን እናምናለን ላለፉት 27 ዓመት ያመጣውን ግጭቶች አይተናልና። ስለዚህ የእርስ በርስ መጣላታችን የመስማማት እና አብሮ መስራት አለመቻላችን ምን አይነት ውጤት እንደሚያመጣ እናውቃለን። በዚህ ምክንያት ጎሰኝነትን ለመቀነስ ለማጥፋት ከፈለግን እኛ የሀገር ብሄርተኞች አንድ መሆነ እንዳለብን የእርስ ብሰር ችግሮቻችንን መፍታት መችሃል እንዳለብን ለጋራ ጥቅም አብሮ መሰለፍ እንዳለብን ግልጽ ሊሆንልን ይገባል። ግልጽ ብቻ ሳይሆን ብቸኛ መንገዳችን እንደሆነ ሊገባን ይገባል። አማራጭ የለንም።
ካሁን ወድያ ከማህላችን ጣት መጠቆም ስለ ሻዕብያ፤ ወያኔ፤ ጎሰኞች ወዘተ ማልቀስ ክልክል ይሁን! ክልክል ይሁን! ይህ አስተሳሰብ ነው ወደ ኋላ የሚጎትተንና። እንደ ጠ/ሚ አብይ ችግር ሲያጋጥምን እራሳችንን ምን አድርገን ነው ይህ ችግር የገጠመን ነው ማለት ያለብን። ወሬዎቻችንን፤ አነጋገራችንን፤ አስተሳሰባችንን፤ ጽሁፎቻችንን እንቀይር። ሌሎች አጎልብተን ስለነሱ በኛ ያላቸውን ሚና ከማውራት እራሳችንን አጎልብትን እንገኝ እራሳችን ለራሳችን አለቃ ነን ችግር ካለን እንፈታለን እንበል። ያህን አይነት ባህል ማዳበር አለብን የ60 ዓመት የውድቅ ልምድ ለመቀየር። ታላቅ ስራ ነው ግን እድለኛ ነን እንደ አብይ አይነቱ የጎላ ምሳሌ ሰጥቶናል።
በመጨረሻ አንድ የጠ/ሚ አቢይ ምሳሌ ልጥቀስላችሁ። ከኢሳያስ ጋር ያለውን ግንኝነት እንየው። እራሱን እንደ ታናሽ ወንድም ትሁት አድርጎ ነው የሚያሳየው። እራሱን ዝቅ ያደርጋል ለምሳሌ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሲመጣ እራሱ ጠቅላይ ሚኒስጤር ሆነ ይቀበላል። የ100 ሚሊኦን ህዝብ መሪ ሆኖ ወደ ስድስት ሚሊዮንዋ ኤርትራ መጀመርያ እሱ ነው የሄደው። ለምን። ይህን ማድረግ የሚችሉ በራሱ ስለሚተማመን ነው። ሁኔታውን እራሱ እንደሚቆጣጠር ስለሚያውቀው የራሱን አጀንዳ ማስረገጥ እንደሚችል ስለሚያውቅ እራሱን ዝቅ ማድረግ ምንም አይመስለውም። በራሱ የሚኮራ ብቻ ነው እራሱን ዝቅ ማድረግ የሚችለው። ሌሎቻችን በራሳችን የምናፍር ሰውው ገበናችንን ያቅብናል ብለን የውሸት ጭምብል አድርገን እንኮፈሳለን። አያችሁ እንዴት በራስ ሃላፊነት መውሰድ ሌሎችን ለራስ ችግር ሌሎችን አለመወንጀል እራስን እንደሚያጎለብት። ሌላው መንገድ እራስን አቅመ ቢስ ያደርጋል። ለራስ ሃላፊነት መውሰድ ግን ያጎለብታል። ዶ/ር አብይም የፖለቲካውን ጉልበት ከዚህ ነው የሚያገኘው። እስቲ ትንሽም እንማር!
1. የበርካታ የዓለም ሀገሮች ተቃውሞ በላቀ የዲፕሎማሲ ስራ አሸንፋ ኤርትራን ወደ ኢትዮጵያ መለሰች። ይህ የዲፕሎማሲ ድል ከሀገራችን ከአቅማችን አስር እጥፍ በላይ ነበር ግን አደረግነው።
2. የአፍሪካ ቁንጮ ሆንን ሁሉም የአፍሪካ ሀገራት እኛን እንደ ምሳሌ ያይን ነበር። በዲፕሎማሲ እና ሀገር ኃይል ደረጃ ብቻ ሳይሆን በታሪክ እና ባህል። ይህ ክብሬታ ለኢትዮጵያ ብዙ ጠቅሟታል።
3. በዓለም ዙርያ ያሉት ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያኖች ስብሰባ አቀደች የኦሪዬንታል ኦርቶዶክስ ስብሰባውን አከናወነች ስምምነቶች አስፈጸመች።
ከ1955 አካባቢ በኋላ ግን እኛ የኢትዮጵያ ብሄርተኖች እርስ በርስ በመጣላት ሀገራችንን ድራሹን አጥፍተናል። መጀመርያ አስፈላጊ የፖለቲካ ለውጦች ባለማድረግ ቀጥሎ ልዩነቶቻችንን በጡንቻ በማካሄድ ሀገራችንን አሳልፈን ለጎሳ ብሄርተኞች ሰጠን። የመጨረሻ ውጤት ምን ሆነ ሻዕብያ እና ወያኔ የሀገራችን 10%ን ወክለው ኢትዮጵያን ተቆጣጠሩት። ይህ ለኛ 90% እጅግ አሳፋሪ ክስተት ነበር አሁንም ነው።
ይህ ታሪክ እንዳለ ሆኖ አሁን ያለፉትን ስህተቶቻችንን ለማርም የሀገራችን ሆደ ሰፊ ብዙሃን እና እግዚአብሔር ዳግም ለማረም እድሉን ሰጥተውናል። ሆንም አንታረምም ብለናል። ዋናው እና መሰረታዊ ችግራችን ያለፉትን አሳፋሪ ድርጊታችንን አለማመናችን ነው ሰው ችግሩን ካላመኑ መፍትሔ አያገኝምና። ጥፋቶቻችንን ላለማምን እና ለመደበቅ ብለን ይመስለኛል ሁል ጊዜ ለችሮቻችን ወያኔ፤ ሻዕብያ፤ ኦነግ፤ «አሜሪካ»፤ ሩሲያ፤ ኤርትራ፤ «አራብ ሀገራት» ወዘተን የምንወቅሰው። እኛ የገዛ ቤታችንን በር ከፍተን እነዚህ ደብተው እንደፈለጉት ሲያደርጉ በራችንን እንዴት ተከፈተ እንዝጋው ከማለት ለሚን ይገባሉ ብለን መጮህ! ዋናው ጣፍቱ የኛ እንደሆነ እናውቃለን ግን እፍረታችን ከባድ ነው መሸሽ ብቻ ነው የምንፈልገው።
ለማስተዋስ ያህል ባለፈው ኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት አንድ የኤርትራ የጦር አዛዥ ያለው ነገር አለ። አንድ ኤርትራዊ አስር ኢትዮጵያዊ ዋጋ አለው ብሎ ፎከረ። ይህ አዲስ ፉከራ አልነበረም በደርግ ጦርነት ላይ የተመሰረተ ነው። የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ምን ያህል እንደተናቁ ነው የሚያሳየው። ድሮ ኤርትራ በሰላም ያጠቃለልን ዛሬ ይቀልዱምን ጀመረ። እስከ ዛሬ በጦር ሜዳ ብቻ ሳይሆን በሌሎች የፖለቲካ ዋይንም የንግድ ዘርፎች በሙሉ ኤርትራዊዎችም ትግሬዎችም እደዚህ ያስባሉ። እኛ ደደብ አህዮች እነሱ አስር እጥፍ ጎበዝ። ከኢትዮጵያዊዎች ብልጥ፤ ጠንካራ፤ የተማርን ወዘተ ነን ብለው ያስባሉ። ይህ የተሳሳተ አስተሳሰብ ግን የነሱ ጥፋት አይደለም። በፍፁም የነሱ ጥፋት አይደለም። እኛ እርስ በርስ ተጨራርሰን እራሳችንን ከታላቅ ህዝብ እና ሀገር ወደ ደካማ ለማኝ ስላወረድን እነሱ የሚያዩትን እውነታ ነው የሚናገሩት። ይህ ለኛ እጅግ አሳፋሪ ነው።
የሰው ልጅ ግን እፍረቱ ስለሚያሳምመው ሊደብቀው ይፈልጋል። ለችግሮቹ ሃላፊነት ከመውሰድ ሁል ጊዜ በውነትም በውሸትም ሌሎችን ይወነጅላል። እኛም አሳፋሪ ድርጊቶቻችንን እና ውድቀታችንን ለመደበቅ ያህል ለ27 ዓመት መጀመርያ ሻዕብያን፤ ኦነግን፤ ወያኔን ወዘተ እየወቀስን ቆይተናል። አሁንም እግዚአብሔር የማይገባንን ጠንካራ የድሮ ዘመን አይነት ኢትዮጵያዊ መሪ ልኮልን አሁን ላሉን ችግሮች ህወሓትን እንወቅሳለን! እንደ ወቀሳችን መጠን ህወሓት ማንም የማይሳነው ግዙፍ ኃይል እንዲመስለን አድርገናል! (ግን 6% ነው የሚወክለው እንላለን!) የራሳችንን ድክመንት ለመሸፈን ላለማየት ለህወሓት የሌለውን አቅም ፈጠርንለት የሌለውን ጥንካሬ ሰየምንለት።
አሁንም እዛው ላይ ነን። አሁንም ከኢትዮጵያ ብሄርተኛ ፖለቲከኛ ተንታኝ አስር ጽሁፎች ካነበብን አስሩም ስለ «ሌሎች»፤ ወያኔ፤ ጎሰኞች፤ ኦነጎች ወዘተ ለቅሶ ነው። እንጂ አንድም ስለራሳችን ጥፋቶች እና ማረምያኦች የሚናገር የሚጽፍ የለም። ኢሳትን ከተመለከትን ስለ«ጠላት» ለቅሶ ነው። ጋዜቶች ሌሎች ማህበራዊ ሚዲያዎች እንዲሁ። የኛ የ«ተፎካካሪ» ድርጅቶች ወሬም እንዲሁ ምናላባትም ይብሳል። እንደ ሚና እና አቅም የሌላው ተጨቋኞች ማልቀስ፤ ማልቀስ፤ ማልቀስ።
እንደዚህ በማድረግ ለራሳችን ጥልቅ የሆነ የእፍረት ጉድጓድ ቆፍረናል። የራሳችን ህልውና በራሳችን ሳይሆን በሌሎች የተቆጣጠረ ነው ብለናል። እነዚህ ሌሎች ደግሞ ከኛ እጅግ አናሳ የሆኑ ናቸው። ይህ አስተሳሰብ ግልጽ የሆነ የዝቅተኝነት መንፈስ እንዲያድርብን አድርጓል። እውነት ነው በተፈጥሮ ሻ'ዕብያዎች፤ ወያኔዎች፤ ኦነጎች ወዘተ ከኛ ይሻላሉ ይበልጣሉ ብለን አምነናል! ይህን የተሳሳተ እምነት የገባንበት ለችግሮቻችን በሙሉ እነሱን ፈላጭ ቆራች እራሳችንን አቅመ ቢስ ስለምናደርግ ነው። ይህ የዝቅተኝነት መንፈስ የሚፈጥረውን እፍረት ለመሸፈን ደግሞ እንደገና እነሱ ላይ እንወርዳለን ከእፍረታችን ለመሸሽ ብለን። ይህ "vicious cycle" ሆኖናል ማቆም ያልቻልነው ሱስ ሆኖናል። የድሮ መሪዎቻችን (ከነ ስህተቾቻቸው) ይህን ቢያዩ ኢትዮጵያዊ መሆናችንን የሚያምኑ አይመስለኝም።
እግዚአብሔር ችር ነው እና አሁን በራሱ የሚኮራ፤ ሃላፊነት የሚወስድ፤ ጥፋቱን የሚያምን፤ ለጥፋቶቹ ንስሃ ገብቶ ይቅርታ የሚጠይቅ፤ ሌሎችን ለራሱ ጥፋቶች እና ችግሮች ከመውቀስ እራሱን በተገቢው ወቅሶ መፍትሔውን ፈልጎ አግኝቶ ስራ ላይ የሚያውል ጀግና መሪ ሰጥቶናል። ለኛ ለኢትዮጵያ ብሄርተኞች ምሳሌ ሊሆን የሚገባን መሪ። ከ60 ዓመት ጥፋታችን በኋላ አሁንም እራሳችንን ለማረም እድል ተሰጥቶናል። ይገርማል!
አሁን የ60 ዓመት ጥፋታችን ውጤት ግልጽ ሊሆንልን ይገባል። እኛ የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ተዝናንተን አድሃሪ፤ ተራማጅ፤ ደርግ፤ ኢዲኡ፤ ኢህአፓ፤ ሜሶን ወዘተ እየተባባልን ተጨራረስን። ባቃጠልነው ባዶ ሜዳ የጎሳ ብሄርተኞች ገቡ። አሁንም የሀገራችን ታላቅ የፖለቲካ ችግር የጎሳ ብሄርተኝነት ነው ብለን እናምናለን ላለፉት 27 ዓመት ያመጣውን ግጭቶች አይተናልና። ስለዚህ የእርስ በርስ መጣላታችን የመስማማት እና አብሮ መስራት አለመቻላችን ምን አይነት ውጤት እንደሚያመጣ እናውቃለን። በዚህ ምክንያት ጎሰኝነትን ለመቀነስ ለማጥፋት ከፈለግን እኛ የሀገር ብሄርተኞች አንድ መሆነ እንዳለብን የእርስ ብሰር ችግሮቻችንን መፍታት መችሃል እንዳለብን ለጋራ ጥቅም አብሮ መሰለፍ እንዳለብን ግልጽ ሊሆንልን ይገባል። ግልጽ ብቻ ሳይሆን ብቸኛ መንገዳችን እንደሆነ ሊገባን ይገባል። አማራጭ የለንም።
ካሁን ወድያ ከማህላችን ጣት መጠቆም ስለ ሻዕብያ፤ ወያኔ፤ ጎሰኞች ወዘተ ማልቀስ ክልክል ይሁን! ክልክል ይሁን! ይህ አስተሳሰብ ነው ወደ ኋላ የሚጎትተንና። እንደ ጠ/ሚ አብይ ችግር ሲያጋጥምን እራሳችንን ምን አድርገን ነው ይህ ችግር የገጠመን ነው ማለት ያለብን። ወሬዎቻችንን፤ አነጋገራችንን፤ አስተሳሰባችንን፤ ጽሁፎቻችንን እንቀይር። ሌሎች አጎልብተን ስለነሱ በኛ ያላቸውን ሚና ከማውራት እራሳችንን አጎልብትን እንገኝ እራሳችን ለራሳችን አለቃ ነን ችግር ካለን እንፈታለን እንበል። ያህን አይነት ባህል ማዳበር አለብን የ60 ዓመት የውድቅ ልምድ ለመቀየር። ታላቅ ስራ ነው ግን እድለኛ ነን እንደ አብይ አይነቱ የጎላ ምሳሌ ሰጥቶናል።
በመጨረሻ አንድ የጠ/ሚ አቢይ ምሳሌ ልጥቀስላችሁ። ከኢሳያስ ጋር ያለውን ግንኝነት እንየው። እራሱን እንደ ታናሽ ወንድም ትሁት አድርጎ ነው የሚያሳየው። እራሱን ዝቅ ያደርጋል ለምሳሌ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሲመጣ እራሱ ጠቅላይ ሚኒስጤር ሆነ ይቀበላል። የ100 ሚሊኦን ህዝብ መሪ ሆኖ ወደ ስድስት ሚሊዮንዋ ኤርትራ መጀመርያ እሱ ነው የሄደው። ለምን። ይህን ማድረግ የሚችሉ በራሱ ስለሚተማመን ነው። ሁኔታውን እራሱ እንደሚቆጣጠር ስለሚያውቀው የራሱን አጀንዳ ማስረገጥ እንደሚችል ስለሚያውቅ እራሱን ዝቅ ማድረግ ምንም አይመስለውም። በራሱ የሚኮራ ብቻ ነው እራሱን ዝቅ ማድረግ የሚችለው። ሌሎቻችን በራሳችን የምናፍር ሰውው ገበናችንን ያቅብናል ብለን የውሸት ጭምብል አድርገን እንኮፈሳለን። አያችሁ እንዴት በራስ ሃላፊነት መውሰድ ሌሎችን ለራስ ችግር ሌሎችን አለመወንጀል እራስን እንደሚያጎለብት። ሌላው መንገድ እራስን አቅመ ቢስ ያደርጋል። ለራስ ሃላፊነት መውሰድ ግን ያጎለብታል። ዶ/ር አብይም የፖለቲካውን ጉልበት ከዚህ ነው የሚያገኘው። እስቲ ትንሽም እንማር!
Friday, 13 July 2018
በረከት ስምዖን ይዙር!
በረከት ስምዖን አማራ ክልልን እየዞረ ገንዘብ እያደለም ድጋፍ እየሰበሰበ ነው ይባላል? ታድያ ምን አለ ይህን ቢአደርግ። ምንድነው የምንፈራ። ሰዎቻችንን ይገዛል ብለን ነው? ያሳምናል ብለን ነው?
በረከት በገንዘብ እና ሀሳብ የራሳችንን ሰዎች ከገዛ ካሳመነ ይህ ስለኛ ምን ይነግረናል። ምን አይነት ህዝብ ነን ማለት ነው? በገንዘብ እና ውሸት የምንገዛ ህዝብ ነን? እንዲህ ከሆነ ደግሞ መሰረታዊ እና መታረም ያለው ችግር የበረከት መዞር ነው ወይንም የኛ በገንዘብ እና በ ውሸት መገዛት ነው?
ግልጽ ነው፤ ችግሩ እኛ ነን መፍትሄው እራሳችንን ማስተካከል ነው። አለበለዛ የኛ ህዝብ በገንዘብ እና ውሸት ሀሳብ ስለሚገዛ በረከትን እናባረው ከሆነ መሰረታዊ ችግራችንን አንፈታም። በርከት ቢጠፋ ሌላ ደግሞ ይመጣል። ሌላ ተቃዋሚ፤ ሌላ የ«አማራ ጠላት»፤ ሌላ ሽብርተኛ ወዘተ። የራሳችንን ችግር ካልፈታን ለአደጋ እና ክህደት ሁልጊዜ የተጋለጥን እንሆናለው። ልድገመው፤ የራሳችንን ችግር ካልፈታን ለአደጋ እና ክህደት ሁልጊዜ የተጋለጥን እንሆናለው።
ለኔ ስለ በረከት ዙረት መቸገር እጅግ እጅግ አሳፋሪ ነው። አንድ ህዝብ የማይወደው አማራ ነኝ ኤርትራዊ እየዞራ ሊበጠብጣችን ይችላል ማለት እኛ እጅግ ደካማ እና ቀሽም ነን ማለት ነው። ባሁኑ ጊዜ ያውም ሰፃነት የሰፈነበት በረከት ምንም ጡንቻ የሌለበት እንዴት ነው የምንፈራው? ያስንቃል።
ወንድሞች እህቶች እንደዚህ አይነት አስተሳሰብ ያስንቃል። ያስንቃል። እንደዚህ ነው እነ ህወሓትን ያሞላቀቅናቸው። ትንሽ ሆነው በቀላሉ ሊገዙን እንደሚችሉ ያመኑት ገና አንዳቸውን ስናይ ሊበጠብጠን ነው ብለን ስንሸማቀቅ ሲያዩ ነው። ይህን ውሸት ማድረግ አለብን። በረከት ስምዖን እየዞረ ሰውን እያሳመነ ከሆነ እኛ ያን ሰው አንዳያምን ማድረግ አለብን። የክህደት መንፈስ፤ የመታለል መንፈስ፤ የመገዛት መንፈስ ከኛ እንዲጠፋ ማድረግ አለብን።
ድሮ ኩሩ ህዝቦች ነበርን። አንድ ሽፍታ ያጠፋናል ብለን አንፈራም ነበር። በራሳችን በራሳችን ህዝብ እንኮራ እንተማመን ነበር። አንድ ወቅት ግን እርስ በርስ መፈጃጀት ስንጀምር በራሳችን መተማመኑን ያቆምን ይመስለኛል። ከዛ ወዲህ በአንድ ክፍል ውስጥ 100 ሆነን ተግኝነት አንድ «ጠላት» ከመጣ ያንን አንድ ጠላት እንደ 100 ሃይል መፍራት ጀመርን። ይህን አስተሳሰብ ካልቀየርን ኢትዮጵያም አማራም አዲዮስ። በተዘዋዋሪ ለዚህ ነው እነ ሻ'ዕብያ እና ወያኔ አንዳችን የ10 አማራ ዋጋ አለው የሚሉት። ትንሽ ሆነን እናሸማቅቃቸዋለን የሚሉት።
ስለዚህ በረከት ስምዖን ይዙር። ከተማ ለከተማ ይዙር ጉቦ ይስጥ ወሬውን ያውራ። መብቱ ነው። እኛ ለህልውናችን ግዴታ የሆነውን ራሳችንን እናስተካክል እናስተምር አንድነት እናምጣ። ልድገመው፤ አንድነት እናምጣ። አንድ ከሆንን እንደ ብረከት አይነቱ 10,000 ሆነውም እየዞሩ ጉቦዋቸውን ቢያድሉ ዋጋ አይኖረውም። ይህ አይነት አንድነት ከሌለን ለዘላለም በቀላሉ የምንሸነፍ ሰዎች ነው የምንሆነው።
Labels:
በረከት ስምዖን,
ብአዴን,
አማራ,
አንድነት,
እራስን መመርመር,
እራስን ማስተካከል,
ድክመት
Tuesday, 25 October 2016
የአንድ ዲያስፖራ ኑዛዜ
2009/2/15 ዓ.ም. (2016/10/25)
በአንድ ዲያስፖራ የተጻፈ…
ችግርን ለመፍታት በመጀመሪያ የችግሩ ዋና ምክንያቶች በትክክሉ መገኘት አለባቸው። እነዚህ ምክንያቶች ተገኝተው ሲፈቱ ነው ዋናው ችግር የሚፈታው። የችግሩ ምክንያቶች ወይም ምንጮች በትክክሉ ካልተገኙ ችግሩ መቼም አይፈታም። ይህን ሁላችንም የምናውቀው እውነታን በመጀመርያ የምጠቅሰው እኔ ከሀገሬ ኢትዮጵያ የፖለቲካና መሃበረሰባዊ ችግሮች ምክንያቶች አንዱ ነኝ ብዬ ስለማምን ነው።
ከማልፈልገው መንግስት ለመሸሽ «ኑሮ ለማሸነፍ» ብዬ ያሳደገችኝን ሀገሬ ኢትዮጵያን ትችያት ወጣሁኝ። በምሳሌ ደረጃ ቤቴን ትቼ ወጣሁኝ ማለት ይቻላል፤ በጣም በመቸኮሌም የቤቴን ቁልፍ ለማንም በአደራነት አልተውኩም። ባዶና አለ ጠባቂ የተውኩትን ቤት ሌላ ሰው ገብቶ ማስተዳደር ጀመረ። የቤቱን እቃ በሚፈልገው መልክ አሸጋሸገ፤ የማይፈልገውን እቃ ሸጠ ወይም ጣለ፤ የሚፈልገውን አዲስ እቃ ደግሞ ገዛና አስገባ። እኔ ከሩቅ ከዲያስፖራ ሆኜ እመለከተለሁ አዝናለው እናደዳለው እጮሃለውም። ቤቴን በመጀመሪያው ባልተውኩኝ ኖሮ።
በርካታ የትምህርት ጓደኞቼ እንደኔ ውጭ ሀገር ናቸው። አቃቸዋለሁ፤ ጥሩ ችሎታ ያላቸው ደህና ሰዎች ናቸው። ዩኒቨርሲቲ ለመግባት የበቁ የሀገራችን ምርጥ ተማሪዎች ነበሩ፤ ሀገሪቷን በደምብ ማገልገል የሚችሉ። ግን ዛሬ ሀገራቸውን ለቀው ውጭ ናቸው፤ አሜሪካንን ያገለግላሉ፤ ወይ ስዊድንን ያገለገላሉ። ታድያ እነዚህ ሁሉ ከሀገር ወጥተው ማን ነው የቀረው? እኔ ከሀገራችንን ከሚመሩት የተሻልኩኝ፤ እንደነሱ ክፉ ያልሆንኩኝ፤ ሀገር ወዳድ ነኝ ብዬ የማምን ከሆነ ከሀገሬ መውጣቴ ምን ይባላል። እራሴን አውጥቼ ሀገሬን ለክፉ ናቸው የምላቸው ሰዎች ትችያታለሁ ማለት ነው። ትልቅ ጥፋት አለብን።
አንድ አስተማሪ የቤተ ክርስትያን ተረት ልንገራችሁ… በአንድ ወክት የቤተ ክርስትያን አመራርና ካህናት በከባድ የመንፈሳዊ ፈተና ተይዘው ነበር። በካህናቱ መካከል የእምነት ጉድለት፤ የስነ መግባር ጉድለት፤ የሙስና ብዛት፤ ወዘተ ይታይ ነበር። እጅግ ከባድ ዘመን ነበር። በዚህ ጊዜ አንድ ደህና ኑሮ ያላት ሴት ወይዘሮ ወደ አንድ የታወቁ መንፈሳዊ አባት ለራስዋ ጉዳዮች ምክር ለማግኘትና ንስሀ ለመግባት ትሄዳለች። ከኚህ አባት ጋር ቁጭ ብላ መወያየት ስትጀምር ግን ዋና ጉዳይዋን ትታ ስለ ቤተ ክርስቲያን አመራሮችና ካህናት ችግር ብቻ ታወራለች ታጉረመርማለችም። የምታማክራቸው አባት በትዕግስት አቤቱታዋንና ወሬዋን እስክትጨርስ ድረስ አዳመጧት። ሁሉንም ተችታና ኮንና ጨረሰች። ቀጥሎ እኚህ ታላቅ አባት ልጆች እንዳሏት ጠየቋት። አዎን ሁለት ሴቶችና ሁለት ወንዶች አሉኝ አለች። ከነዚህ ወንድ ልጆችሽ አንዱ ቄስ ቢሆንስ ብለው ጠየቋት። በፍጹም፤ እንዴት ይሆናል ብላ ተቆጣች። እንዴት ለልጀ ገንዘብም እውቀጥም የሌለውን ስራ እመኝለታለሁ አለች! ታድያ የራስሽ ልጆች ካህን እንዲሆኑ ካልፈለግሽ ማን ነሽ በፈቃዳቸው ካህን እንሆናለን ያሉትን የምትኮንኙ ብለው ታላቁ አባት ወቀሷት አስተማሯትም።
ሀገር ችግር ላይ በሆነበት ጊዜ መሸሽ ክህደት ነው ማለት ይቻላል። እኔ ሀገሬን ከድጂያታለሁ ለማለት ወደኋላ አልልም። ጥፋትንና ድክመትን ማመን የመጀመሪያ የችግርን መፍታት እርምጃ ነው። አንድ ሰው ቤተሰብ ውስጥ ችግር ካለ ቤተሰብነቱን ክዶ ሸሽቶ አይሄድም። ልጀ ካስቸገረኝ ልጄ አይደለህም ብዬ አላባርረውም። ካባረርኩት ካድኩት ማለት ነው። ሀገርም እንደዚህ ነው። ሀገር ወዳድ ነኝ ማለትና ሀገር ችግር ላይ ስትወድቅ መሸሽ ተጻራሪ ናቸው!
እውነት ነው፤ አንዳንዴ ሽሽት ግድ ነው። ድንግል ማርያም ልጇን ክርስቶስን ይዛ ሸሽታለች። ግን ሽሽቱ አላማን ለማሳካት ነው እንጂ ለመሸሽ አይደለም። እውነቱን ለመናገር እኔ ግን ወደ ዲያስፖራ የመጣሁት ለመሸሽና የሀገሬን ችግር ለሌሎች ለመተው ነው። ለሀገሬ አላማ ኖሮኝ አይደለም። ኢትዮጵያ ያሉት ታግለውልኝ ደህና መንግስት ሲያመጡ እመለሳለሁ ብዬ ነው። ግን ያም ቢሆን የምመለስ ይመስላችኋልን? ከሃዲ ነኝ፤ እውነት ነው፤ ጥፋቴን አምናለሁ።
ግን ሀገሬን እውዳለሁ፤ ፖለቲካዋ እንደዚህ ወይም እንደዛ መሆን አለበት፤ መሃበረሰቧም እንደዚህ ወይም እንደዛ መምሰል አለበት፤ ህዝቡ መሰልጠን አለበት፤ መንግስትም አሰራሩ እንደዚህ መሆን አለበት ብዬ አስባለሁ እለፈልፋለውም። ሀሳብና ወሬ ብቻ ሀገር ወዳድ የሚያደርግ ይመስለኛል።
ሀገር ወዳድ ሆኜ ግን እንዴት ነው ተግባሬ ያንን የሀገር ፍቅርን ሊያንጸባርቅ የሚችለው? ልጆቼን እንኳን ቋንቋቸውን አላስተማርኳቸውም። ሀገረ ወዳድነት ይህ ነው? ያውም «አላስተማርኳቸውም» የሚለው ቃል በቂ አይገልጸውም፤ አላስተማርኳቸውም ሳይሆን እንዳይማሩ ከልኪያቸዋለሁ። ሌላው ሁሉ መጤ፤ ሂስፓኒኩ፤ ቻይናው፤ ሶማሌው፤ ጣሊያኑ፤ ወዘተ ቋንቋውን ከቤት እየተናገረ ልጆቻቸው በተዘዋዋሪ ቋንቋቸውን ይችላሉ። እኔ ግን ከቤቴ በደምብ የማልችለውን እንግሊዘኛ (ወይም ጀርመን ስዊድኛ ወዘተ) እየተናገርኩኝ ልጆቼ ቋንቋቸውን እንዳይችሉ አረጋለሁ። ባህላቸውን ወጋቸውንም ላይላዩን ብቻ ነው የማስተምራቸው። እውነቱን ለመናገር ልጆቼን ፈረንጅ እንዲሆኑ አድርግያለሁ። ኢትዮጵያዊ ትውልድ በኔ ቆሟል። ታድያ ምን አይነት ሀገር ወዳድ ነኝ?
ወደ ክህደቴ ልመለስና… እርግጥ እራሴን ለማጽናናት ያህል አንዳንድ ግዜ ለክህደቴ ስበቦችና አጉል ምክንያቶች እፈጥራለሁ። አንዱ «ከሀገሬ ብቆይ እታሰር ነበር» ነው። «ህሊናዬን ሽጥቼ ካልሆነ ሀገሬ መስራት አልችልም።» ታድያ ሀገር ቤት ያሉት ወገኖቼ በሙሉ ወይ ታስረዋል ወይ ህሊናቸውን የሸጡ አደርባዮች ሆኖዋል ማለት ነው? ወይ ፍርድ! በአንድ በኩል ገዥው መንግስት የአናሳ ህዝብ ነው እላለሁ። በሌላው በኩል ሁሉንም ይቆጣጠራሉ እላለሁ። እነዚህ የሚጻረሩ ሀሳቦች ናቸው! እውነቱ እንደዚህ ነው፤ አብዛኛው ህዝብ ክፉ ላለማድረግ ከወሰነ ከተባበረ በሀገሪቷ ያለውን ክፋት ይጠፋ ነበር። እራሴን እንደዚህ ማታለል አልችልም፤ ከሀገሬ ሆኜ ለሀገሬ በርካታ ጠቃሚ ነበር አፈራ ነበር።
አንዳንድ ጊዜ ደግሞ ክሀገሬ የሸሸሁት ኑሮ አሸንፌ ቤተሰቤን ለመርዳት ነው ብዬ እራሴን ማጽናናት እሞክራለሁ። ከቅዠቴ ስነቃ ግን ለዚህም አጉል ምክንያት መልስ አለኝ። ሀገር የሚያድገው ገንዘብ ሲያገኝ ነው ወይም ህዝቡ በእውቀትና ችሎታ ሲበለጽግ ነው? ጃፓን ምንም ተፈጥሮ ሃብት ሳይኖራት ህዝቧን በእውቀትና ችሎታ እንዲበለጽግ አድርጋ ነው ያደገችው። ሳውዲ ደግሞ በተፈጥሮ ሃብት ምክንያት በገንዘብ ሃብታም ሆና ግን በህዝብ ደሃ ናት። ገንዘብ ለቤተሰቤ መላክ ምን ያህል ሀገሪቷንም እነሱንም ይጠቅማል? እርገጥ አንዳንድ ቤተሰብ ገንዘቡን ለዘላቂ ነገር ለትምህርት ለንግድ ወዘተ ይጠቅምበታል። በርካታው ደግሞ ለለት ኑሮ ይጠቀምበታል። ምንም ቢሆን ገንዘቤ እኔን አይተካም ሊተካም አይችልም ይተካል የሚለው አስተሳሰብም ጎጂ ነው። ማንም በድጎማ አይበለጽግም። ይህ ከሀገር ለመሸሽ ምክንያቴ ሊሆነ አይገባም።
አዎን ለክህደቴ ምንም ስበብ የለም። አምኛለሁ። ንስሀ ገባለሁም። እግዚአብሔር ሀገር ቤት እንድመለስና ከወገኖቼ አብሬ ደስታቸውንም ችግራቸውንም እንድካፈል ብርታቱ ይስጠኝ። እራሴንም ማታለል እንዳቆም ይርዳኝ። አሜን።
በአንድ ዲያስፖራ የተጻፈ…
ችግርን ለመፍታት በመጀመሪያ የችግሩ ዋና ምክንያቶች በትክክሉ መገኘት አለባቸው። እነዚህ ምክንያቶች ተገኝተው ሲፈቱ ነው ዋናው ችግር የሚፈታው። የችግሩ ምክንያቶች ወይም ምንጮች በትክክሉ ካልተገኙ ችግሩ መቼም አይፈታም። ይህን ሁላችንም የምናውቀው እውነታን በመጀመርያ የምጠቅሰው እኔ ከሀገሬ ኢትዮጵያ የፖለቲካና መሃበረሰባዊ ችግሮች ምክንያቶች አንዱ ነኝ ብዬ ስለማምን ነው።
ከማልፈልገው መንግስት ለመሸሽ «ኑሮ ለማሸነፍ» ብዬ ያሳደገችኝን ሀገሬ ኢትዮጵያን ትችያት ወጣሁኝ። በምሳሌ ደረጃ ቤቴን ትቼ ወጣሁኝ ማለት ይቻላል፤ በጣም በመቸኮሌም የቤቴን ቁልፍ ለማንም በአደራነት አልተውኩም። ባዶና አለ ጠባቂ የተውኩትን ቤት ሌላ ሰው ገብቶ ማስተዳደር ጀመረ። የቤቱን እቃ በሚፈልገው መልክ አሸጋሸገ፤ የማይፈልገውን እቃ ሸጠ ወይም ጣለ፤ የሚፈልገውን አዲስ እቃ ደግሞ ገዛና አስገባ። እኔ ከሩቅ ከዲያስፖራ ሆኜ እመለከተለሁ አዝናለው እናደዳለው እጮሃለውም። ቤቴን በመጀመሪያው ባልተውኩኝ ኖሮ።
በርካታ የትምህርት ጓደኞቼ እንደኔ ውጭ ሀገር ናቸው። አቃቸዋለሁ፤ ጥሩ ችሎታ ያላቸው ደህና ሰዎች ናቸው። ዩኒቨርሲቲ ለመግባት የበቁ የሀገራችን ምርጥ ተማሪዎች ነበሩ፤ ሀገሪቷን በደምብ ማገልገል የሚችሉ። ግን ዛሬ ሀገራቸውን ለቀው ውጭ ናቸው፤ አሜሪካንን ያገለግላሉ፤ ወይ ስዊድንን ያገለገላሉ። ታድያ እነዚህ ሁሉ ከሀገር ወጥተው ማን ነው የቀረው? እኔ ከሀገራችንን ከሚመሩት የተሻልኩኝ፤ እንደነሱ ክፉ ያልሆንኩኝ፤ ሀገር ወዳድ ነኝ ብዬ የማምን ከሆነ ከሀገሬ መውጣቴ ምን ይባላል። እራሴን አውጥቼ ሀገሬን ለክፉ ናቸው የምላቸው ሰዎች ትችያታለሁ ማለት ነው። ትልቅ ጥፋት አለብን።
አንድ አስተማሪ የቤተ ክርስትያን ተረት ልንገራችሁ… በአንድ ወክት የቤተ ክርስትያን አመራርና ካህናት በከባድ የመንፈሳዊ ፈተና ተይዘው ነበር። በካህናቱ መካከል የእምነት ጉድለት፤ የስነ መግባር ጉድለት፤ የሙስና ብዛት፤ ወዘተ ይታይ ነበር። እጅግ ከባድ ዘመን ነበር። በዚህ ጊዜ አንድ ደህና ኑሮ ያላት ሴት ወይዘሮ ወደ አንድ የታወቁ መንፈሳዊ አባት ለራስዋ ጉዳዮች ምክር ለማግኘትና ንስሀ ለመግባት ትሄዳለች። ከኚህ አባት ጋር ቁጭ ብላ መወያየት ስትጀምር ግን ዋና ጉዳይዋን ትታ ስለ ቤተ ክርስቲያን አመራሮችና ካህናት ችግር ብቻ ታወራለች ታጉረመርማለችም። የምታማክራቸው አባት በትዕግስት አቤቱታዋንና ወሬዋን እስክትጨርስ ድረስ አዳመጧት። ሁሉንም ተችታና ኮንና ጨረሰች። ቀጥሎ እኚህ ታላቅ አባት ልጆች እንዳሏት ጠየቋት። አዎን ሁለት ሴቶችና ሁለት ወንዶች አሉኝ አለች። ከነዚህ ወንድ ልጆችሽ አንዱ ቄስ ቢሆንስ ብለው ጠየቋት። በፍጹም፤ እንዴት ይሆናል ብላ ተቆጣች። እንዴት ለልጀ ገንዘብም እውቀጥም የሌለውን ስራ እመኝለታለሁ አለች! ታድያ የራስሽ ልጆች ካህን እንዲሆኑ ካልፈለግሽ ማን ነሽ በፈቃዳቸው ካህን እንሆናለን ያሉትን የምትኮንኙ ብለው ታላቁ አባት ወቀሷት አስተማሯትም።
ሀገር ችግር ላይ በሆነበት ጊዜ መሸሽ ክህደት ነው ማለት ይቻላል። እኔ ሀገሬን ከድጂያታለሁ ለማለት ወደኋላ አልልም። ጥፋትንና ድክመትን ማመን የመጀመሪያ የችግርን መፍታት እርምጃ ነው። አንድ ሰው ቤተሰብ ውስጥ ችግር ካለ ቤተሰብነቱን ክዶ ሸሽቶ አይሄድም። ልጀ ካስቸገረኝ ልጄ አይደለህም ብዬ አላባርረውም። ካባረርኩት ካድኩት ማለት ነው። ሀገርም እንደዚህ ነው። ሀገር ወዳድ ነኝ ማለትና ሀገር ችግር ላይ ስትወድቅ መሸሽ ተጻራሪ ናቸው!
እውነት ነው፤ አንዳንዴ ሽሽት ግድ ነው። ድንግል ማርያም ልጇን ክርስቶስን ይዛ ሸሽታለች። ግን ሽሽቱ አላማን ለማሳካት ነው እንጂ ለመሸሽ አይደለም። እውነቱን ለመናገር እኔ ግን ወደ ዲያስፖራ የመጣሁት ለመሸሽና የሀገሬን ችግር ለሌሎች ለመተው ነው። ለሀገሬ አላማ ኖሮኝ አይደለም። ኢትዮጵያ ያሉት ታግለውልኝ ደህና መንግስት ሲያመጡ እመለሳለሁ ብዬ ነው። ግን ያም ቢሆን የምመለስ ይመስላችኋልን? ከሃዲ ነኝ፤ እውነት ነው፤ ጥፋቴን አምናለሁ።
ግን ሀገሬን እውዳለሁ፤ ፖለቲካዋ እንደዚህ ወይም እንደዛ መሆን አለበት፤ መሃበረሰቧም እንደዚህ ወይም እንደዛ መምሰል አለበት፤ ህዝቡ መሰልጠን አለበት፤ መንግስትም አሰራሩ እንደዚህ መሆን አለበት ብዬ አስባለሁ እለፈልፋለውም። ሀሳብና ወሬ ብቻ ሀገር ወዳድ የሚያደርግ ይመስለኛል።
ሀገር ወዳድ ሆኜ ግን እንዴት ነው ተግባሬ ያንን የሀገር ፍቅርን ሊያንጸባርቅ የሚችለው? ልጆቼን እንኳን ቋንቋቸውን አላስተማርኳቸውም። ሀገረ ወዳድነት ይህ ነው? ያውም «አላስተማርኳቸውም» የሚለው ቃል በቂ አይገልጸውም፤ አላስተማርኳቸውም ሳይሆን እንዳይማሩ ከልኪያቸዋለሁ። ሌላው ሁሉ መጤ፤ ሂስፓኒኩ፤ ቻይናው፤ ሶማሌው፤ ጣሊያኑ፤ ወዘተ ቋንቋውን ከቤት እየተናገረ ልጆቻቸው በተዘዋዋሪ ቋንቋቸውን ይችላሉ። እኔ ግን ከቤቴ በደምብ የማልችለውን እንግሊዘኛ (ወይም ጀርመን ስዊድኛ ወዘተ) እየተናገርኩኝ ልጆቼ ቋንቋቸውን እንዳይችሉ አረጋለሁ። ባህላቸውን ወጋቸውንም ላይላዩን ብቻ ነው የማስተምራቸው። እውነቱን ለመናገር ልጆቼን ፈረንጅ እንዲሆኑ አድርግያለሁ። ኢትዮጵያዊ ትውልድ በኔ ቆሟል። ታድያ ምን አይነት ሀገር ወዳድ ነኝ?
ወደ ክህደቴ ልመለስና… እርግጥ እራሴን ለማጽናናት ያህል አንዳንድ ግዜ ለክህደቴ ስበቦችና አጉል ምክንያቶች እፈጥራለሁ። አንዱ «ከሀገሬ ብቆይ እታሰር ነበር» ነው። «ህሊናዬን ሽጥቼ ካልሆነ ሀገሬ መስራት አልችልም።» ታድያ ሀገር ቤት ያሉት ወገኖቼ በሙሉ ወይ ታስረዋል ወይ ህሊናቸውን የሸጡ አደርባዮች ሆኖዋል ማለት ነው? ወይ ፍርድ! በአንድ በኩል ገዥው መንግስት የአናሳ ህዝብ ነው እላለሁ። በሌላው በኩል ሁሉንም ይቆጣጠራሉ እላለሁ። እነዚህ የሚጻረሩ ሀሳቦች ናቸው! እውነቱ እንደዚህ ነው፤ አብዛኛው ህዝብ ክፉ ላለማድረግ ከወሰነ ከተባበረ በሀገሪቷ ያለውን ክፋት ይጠፋ ነበር። እራሴን እንደዚህ ማታለል አልችልም፤ ከሀገሬ ሆኜ ለሀገሬ በርካታ ጠቃሚ ነበር አፈራ ነበር።
አንዳንድ ጊዜ ደግሞ ክሀገሬ የሸሸሁት ኑሮ አሸንፌ ቤተሰቤን ለመርዳት ነው ብዬ እራሴን ማጽናናት እሞክራለሁ። ከቅዠቴ ስነቃ ግን ለዚህም አጉል ምክንያት መልስ አለኝ። ሀገር የሚያድገው ገንዘብ ሲያገኝ ነው ወይም ህዝቡ በእውቀትና ችሎታ ሲበለጽግ ነው? ጃፓን ምንም ተፈጥሮ ሃብት ሳይኖራት ህዝቧን በእውቀትና ችሎታ እንዲበለጽግ አድርጋ ነው ያደገችው። ሳውዲ ደግሞ በተፈጥሮ ሃብት ምክንያት በገንዘብ ሃብታም ሆና ግን በህዝብ ደሃ ናት። ገንዘብ ለቤተሰቤ መላክ ምን ያህል ሀገሪቷንም እነሱንም ይጠቅማል? እርገጥ አንዳንድ ቤተሰብ ገንዘቡን ለዘላቂ ነገር ለትምህርት ለንግድ ወዘተ ይጠቅምበታል። በርካታው ደግሞ ለለት ኑሮ ይጠቀምበታል። ምንም ቢሆን ገንዘቤ እኔን አይተካም ሊተካም አይችልም ይተካል የሚለው አስተሳሰብም ጎጂ ነው። ማንም በድጎማ አይበለጽግም። ይህ ከሀገር ለመሸሽ ምክንያቴ ሊሆነ አይገባም።
አዎን ለክህደቴ ምንም ስበብ የለም። አምኛለሁ። ንስሀ ገባለሁም። እግዚአብሔር ሀገር ቤት እንድመለስና ከወገኖቼ አብሬ ደስታቸውንም ችግራቸውንም እንድካፈል ብርታቱ ይስጠኝ። እራሴንም ማታለል እንዳቆም ይርዳኝ። አሜን።
An Exercise in Empathy
2009/2/15
(Ethiopian calendar)
2016/10/25
(European calendar)
(pdf)
[Note:
An Amharic version of this post will appear sometime!]
In
the next few posts, I will attempt, just attempt, an exercise in
empathy. I will try and put myself in the shoes of Ethiopia's various
political groups and constituencies and describe the truth about
Ethiopian politics how they see it – from their perspective. I will
start with either Oromo ethnic nationalists or the EPRDF, or maybe
just the TPLF. And I'll keep going as much as I can.
Why
this exercise? I'll first answer from within the 'conflict
resolution' paradigm. Empathy – trying to grasp the point of view,
the feelings, the thoughts, etc of others – is an important tool,
perhaps the most important, in conflict resolution. The idea is that
if you can empathize, you can communicate better, that is you can
communicate in a way that your opponents can understand, and of
course you can better envision solutions that your opponents can
accept. Empathy also builds trust and understanding, which needless
to say are important for living together peacefully.
Second,
as this blog is written from an Orthodox Christian perspective, I'll
explain from this point of view as well. Empathy is basic
Christianity. Our fundamental belief is that Christ came and died for
us out of compassion – to share our suffering and redeem it. This
is similar to empathy, but greater, as it involves not only sharing
the Other's experience, but doing so with the hope of bring about
something better. Further, avoiding judgement is a basic teaching of
the Church. “To judge sins is the business of one who is sinless,
but who is sinless except God?... To judge a man who has gone astray
is a sign of pride, and God resists the proud.” says St Dorotheus
of Gaza. So, following Christ's example of compassion and his command
not to judge, a Christian as a matter of course must try to be
empathetic.
I
hope my little exercise will help shed some light on solutions for
Ethiopia's problems. So, I'll give it a try over my next few
articles. Your feedback as always is much appreciated.
Thursday, 13 October 2016
ኦርቶዶክስ ክርስትናና ፖለቲካ
2009/2/3
ዓ.ም.
(2016/10/13)
«እግዚአብሔር በሁልም ስፍራ አለ በሁሉም ነገርም ይገኛል» (God is everywhere present and in all things) አንድ የኦርቶዶክስ ሃይማኖት መሰረታዊ እምነት ነው። ይህ አባባል እግዚአብሔር የፈተራት ዓለም በሁለት በ«አለማዊ» እና በ«ሃይማኖታዊ» ስፍሮች እንዳልተከፈለች ይገልጻል። ወደ ቤተሰባችን፤ ስራችን፤ ንግዳችን፤ ዘፈናችን፤ መዝኒያናችን፤ ስፖርታችን፤ ትምህርትቤታችን፤ እርሻችን፤ ፖለቲካችንም ስንሄድ እግዚአብሔርንና እምነታችንን ትትን መሄድ አይቻላም! እግዚአብሔር በነዚ ስፍሮች ሁሉ አለና። ግድብ የለውም። ስለዚህ ፖለቲካና ክርስትና የተለያዩና የማይገናኙ ናቸው ማለት አይቻልም።
ስለዚህ ክርስትያኖች በፖለቲካ ልንሳተፍ እንችላለን። የማህበራዊ ኑሮ ፖለቲካን ስለሚይካትት ብንፈልግም ባንፈልጉም በተወሰነ ደረጃ ቢሆንም ፖለቲካ ውስጥ ተሳትፈናል። ሁለት ምሳሌዎች ልስጣችሁ፤ ቀረጥ መክፈል ማለት ገንዘብ ለመንግስት መስጠት ነው። የዚህን ገንዘብን አጥቃቀም የሚወስኑት ፖለቲከኞች ናቸው። በገንዘባችን ለሚያደርጉት ግን ተጠሪ ነን ግንዘባችን ነውና። በቀበሌ ወይም በማንኛውም የምንግስት መሥሪያቤት ስንገለገል ፖለቲከኞች የዘረጉትን የአስተዳድራዊ ዘዴ መቀበል ማለት ነው። ብለት ኑሮአችን ፖለቲካ አይጠፋም። ፖለቲካ አንዱ የህይወታችን ዘርፍ ነው።
ታድያ የአንድ ክርስትያን ፖለቲካዊ ኑሮ እንዴት መሆን አለበት? ይህን ለመመለስ በመጀመርያ አንዳንድ መሰረታዊ የሆኑ የክርስትና እምነቶች እንመልከት። ከላይ እግዚአብሔር ከሁሉም አለ የሚለውን አባባል ጠቅሽያለሁ። ቀጥሎ «በዐይነህ ውስጥ ያለውን ግንድ ሳትመለከት፤ በወንድምህ ዐይን ያለውን ጉድፍ ለምን ታያለህ» የሚለውን እስቲ እንመልከት። ባለንጀራችሁን እንደራሳችሁ ውደዱ ይበልጥ ደግሞ እኔ እንደምወዳችሁ ያህል ውደዱት ብሎ ክርስቶስ አዞናል። ይህን አባባልንም እንመልከት።
ሌላ አባባል፤ ቅዱስ ባስሊዮስ እንደዚህ አሉ፤ « የባለንጀራህ ሀጥያት ብቻ ከሆነ የሚታይህ ያንን ብቻ ከማየት ይልቅ በፊትም አሁንም የሚያደርገውን ጥሩ ነገሮች እንዳሉ ተገንዘብ። መፍረድን ትተህ ይህን ለማድረግ ስትሞክር ጭራሽ እርሱ ካንተ የተሻለ እንደሆነ ትረዳለህ።» ይህ አባባል ሁለት መሰረታዊ እምነቶታችንን ይገልጻል፤ እግዚአብሔር የፈጠረው ሁሉም ሰው ትንሽም ቢሆን ጥሩነት ስላለው በሌላ ሰው መፍረድ ተገቢ አይደለም።
ክርስቶስ «እኔ በልቤ የዋህና ትሑት ነኝ» ብሎ እኛም እንደሱ እንድንሆን አዞናል። ትሕትና የቀደመውና ዋናው ሀጥያታችን «ትዕቢት» ተቃራኒና መድሀኒት ስለሆነ የሃይማኖት አባቶች የምያተኩሩበት መልካ መግባር ነው። አባ ይስሐቅ ዘሶሪያ እንዲህ ብለዋል፤ «ጨው ለምግብ እንደሚሆን ትህትና ለሁሉ መልካ መግባር ይሆናል።»
የክርስትያን ፖለቲካ ኑሮ ከላይ በጠቀስኳቸው አባባሎች የሚያስተምሩን መልካ መግባሮች ነው መካተትና መመራት አለበት፤ 1) እግዚአብሔር ከሁሉም አለ፤ 2) የሌላውን ሀጥያት ከማየት ፋንታ የራሳችንን ሀጥያት አይተን ንስሃ እንጋባ እናርማቸውም፤ 3) ባለንጀራችንን ክርስቶስ እንደሚወደን እንውደድ፤ 4) በሰው አንፍረድ፤ ትሑት እንሁን ከትዕቢትና ትምክህት እንራቅ።
በዛሬው የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሁኔታ አንድ ክርስትያን እነዚህን እምነቶች ተከትሎ ምን ሊያደርግ ይገባዋል? አትፍረዱ፤ ትሑት ሁኑ፤ የራሳችሁን ሀጥያት ተመልከቱ፤ አብዛኞቻችን በፖለቲካ ዙርያ የሌላው ሰው፤ ወገን፤ ጎሳ፤ ፓርቲ ጥፋት ብቻ ነው የሚታየን። የኢህአዴግ፤ የህወሓት፤ የኦነግ፤ የሻእቢያ፤ የኢዴፓ፤ የደርግ፤ የኢሀፓ፤ የኃይለ ስላሴ፤ የዘንድሮ ተቃዋሚ፤ የዲያስፖራ፤ ወዘተ። አንድ ክርስትያን እራሱን ሳይመረምር የራሱን ጥፋቶች ተረድቶ ንስሀ ሳይገባ የማንንም፤ የኢህአዴግንም፤ ጥፋትና ስህተትን ላይ ማተኮር የለበትም።
ግን ምን የፖለቲካ ሀጥያት አለብኝ ብለን የምንጠይቅ ብዙ ነን። ከበርካታ ሰዎች ከገደለው ካሰቃየው ኢህአዴግ፤ ደርግ፤ ወዘተ ምኔ ሊወዳደር ይችላል። እስቲ ይህን ጥያቄ በምሳሌዎች ለመመለስ ልሞክር።
ጎረቤቴ ለ«ኢንቬስተር» ተብሎ መሬቱን ሲነጠቅ ረዳሁትን? ትንሽም ነገር አደረግኩለት?የምፍረአቸውን የሰፈሬን ዱሪዬዎችን ለመርዳትና ጥሩ መስመር ለማስያዝ ያረግኩት ነገር አለ? ወይም የራሳቸው ጉዳይ ብዬ ዞር ብዬም አላያቸውም። ችግር እስኪያመጡ። በፖለቲካ ዙሪያ «ኦሮሞ» ሲባል በልቤ ፍርሃትና ጥርጣሬ አይሰፍንም? ነው በንጹ ልቦና ጉዳዩን እመለከታለሁ? «እነሱ ከሚገዙን ወያኔ ይግዛን» ብዬ አስቤ አላቅምን? ግን አንድ ቀንም «ከነሱ» ጋር ቁጭ ብዬ ተወያይቼ አላቅም። ከጎረቤቶቼ ጋር ድሮ ተጣልቼ አሁንም አልተቀየምኳቸውም? በዚህ ጥላቻ ምክነያት እንኳን ለፖለቲካ ለውጥ ለምንም ነገር ከነሱ ጋር መተባበር አልችልም አይደ? ከባልደረባዬ ምሁር በትንሽ አስተሳሰብ ልዩነት ምክነያት ጠላቶች አልሆንም? እንኳን አብረን ለመስራት መተያየትም አንፈልግም አይደለምን? ስራተኞቼን እንደ ሰው ቆጥሬ አላውቅም እሁድ ቤተክርስትያን ለመሄድም እድል አልሰጣቸውም! ዘላለማዊ ቂም አልፈጠርኩባቸውም? ኢህአዴግ ይህንን ቂም ተጠቅሞ እነዚህን ሰራተኞቼን እኔን ለመግዳት ወይም የኔን አቋም ለማዳከም መጠቀም አይችልምን? የማይገባኝ ጥቅም ለማግኘት ጉቦ ሰጥችሄ አላውቅምን? ከስራ ቦታዬ በኔ ሃሳቦች የማይስማሙትን አልኮንንም? ሰራተኞች ሲሳሳቱ ችግራቸውን ከመረዳት ፋንታ አልፈርድባቸውም? ልጄ ውትድርና ገብቶ የማያምንበትን ክፉ ድርጊቶች እንዲያደርግ ይታዘዛል ያደርጋል። ልጄ ነው የሚጦረኝ እና እንደዚህ አይነቱን ጉዳይ ለሱ በማንሳት ላበሳጨው አልፈልግም እላለሁ። ታድያ እንደ የኢግዚአብሔር ልጅ ሃላፊነቴን አልካድኩምን?
እራሳችንን በደምብ ከመረመርን እነዚህ አይነቶቹ ሀጥያቶች እንዴት ከኛ ወደ ህብረተሰቡ፤ ከህብረተሰብ ወደ መንግስታችን እንደሚተላለፍ እንደሚያንጸባርቅ ልንገነዘብ እንችላለን። ክርስትያኖች የሁላችንም ኃጢአት የተገናኘው እንደሆነ እናምናለን። ለሌሎችንም ኃጢአት ሃላፊነት እንዳለብን እናምናለን። አባቶች ይህን ተጠንቅቀው ነው የሚያስተምሩን። ከላይ እንደምሳሌ የጠቀስኳቸው ኃጢአቶች እንዴት አሁን ካለው የምንግስት ስረዓት ባህሪ ጋር እንደሚገናኙ ግልጽ እንደሆነ ተስፋ አለኝ።
ክርስትያን በመሆኔ መጠን ለነዚህ ኃጢአቶች ንስሃ ገብቼ እየወደኩኝ እየተነሳሁኝ እያስተካከልኩኝ መኖር ነው የሚጥበቅብኝ። የፖለቲካ ኑሮዬም እንደዚህ ነው መሆን ያለበት። የምደግፈው የፖለቲካ አቋም፤ አመለካከት፤ ፓርቲ፤ ርዕዮተ ዓለም፤ ወዘተ ከክርስትያንነቴ ስር ነው መሆን ያለባቸው። እንደ ክርስትያን እስከኖርኩኝ ድረስ ፖለቲካው እራሱን ያስተካክላል።
ሆኖም ማንም ሰው አጥፊና ክፉ ነበር የሚያደርግ መንግስት ወይም ተቋምን መታገል የለበትም ማለት አይቻልም። እያንዳንዱ የራሱን ልብ ያውቃልና ልታገል ቢል በሱ ልፈርድ አልችልም፤ ግን ትግሉ ውጤታማ እንዲሆን በመጀመርያ የራሱን ልብና ገበና መፈተሽ አለበት። ሳይፈትሽ ሌላውን ለማስወገድ ብቻ ከታገለ ትግሉን አያሸንፍም። ወይም ይባስ ያሸንፍና ከታገለው የባሰ ሆኖ ይገኛል። ይህን እውነታ ሃይማኖታችን ያስተምረናል። እውነታም ስለሆነ በታሪክ በትደጋጋሚ ሲከሰት አይተናል! ስለዚህ በመጀመርያ ክርስትያን እንሁን፤ ሙሉ ክርስትያን እንሁን። ከሆንን ሌላው እራሱን ያስተካክላል።
Subscribe to:
Posts (Atom)