Showing posts with label elite absence. Show all posts
Showing posts with label elite absence. Show all posts

Wednesday, 2 November 2022

FUD

 Written February 2022


አንድ የፕሮፓጋንዳ ዘዴ Fear Uncertainty Doubt (FUD) ይባላል። የዚህ ዘዴ አላማ አንድ ህብረተሰብ በፍርሀት፤ በአለማረጋጋትና በጥርጣሬ መንፈስ እንዲሞላ ነው። የአንድ ህብረተሰብን ስነ ልቦና በዚህ መንፈስ ከተሞላ የገዛ ራሱን ሸባና አቅመ ቢስ ያደርጋል። ከዛ በቀላሉ ይገዛል።
በተለይ ከነጭና ቆይ ሽብር በሗላ በኢትዮጵያዊነት የሚያምነው ህብረተሰብ ስነ ልቦናው በፍርሀትና ጨለምተኝነት ተሞላ። ፖለቲካ ኮሬንቲ ነው ብሎ ከምንም አይነት መተባበርና መደራጀት ሸሸ። እንኳን በዘዴና በብልህነት በየዋሕነትም ለደህንነቱ መታገል አቃተው።
የዚህ ህብረተሰብ ጠላቶች ይህ ስነ ልቦናው ገብቷቸው ህብረተሰቡን በቀላሉ ለመግዛት FUD ፕሮፖጋንዳን ተጠቀሙ። ወደ ፍርሀት፤ አለመረጋጋትና ጥርጣሬ ያመዘነ ህዝብን ትንሽ ገፋ ካርግነው ወጥመድ ውስጥ ገብቶ ይቀራል ብለው አበቡ እንዳሉትም ሆነ።
የ FUD ዘዴ ቀልጣፋነት ዋናው ምክነያት የመቀጣጠል ባህሪው ነው። እንደ ቫይረስ ይሰራል። ይህ ማለት አንዴ ህብረተሰቡን ፍረሀት፤ አለሚጋጋትና ጥርጣሬን ካሳቀፍነው ህብረተሰቡ እራሱ እርስ በርሱ ፕሮፖጋንዳውን ያሰራጭል! የጠላት ስራ ይቀላል።
ባለፈው 30 ዓመት ዛሬም ይህ ነው በኢትዮጵያዊነት ጎራው ሲከሰት የታየው። ባለው በነባራዊው ሁኔታ ደስተኛ ያልሆኑት ንግግራቸው መልእክቶቻቸው አሉታዊ ናቸው። ከሌ እየጎዳን ነው፤ ከሀዲ ነው፤ እነሱ እየመጡብን ነው፤ ደህና ሰው የለም፤ አለቀልን ፤ ወዘተ። እነዚህ መልእክቶች የጠላትን የFUD ፕሮፓጋንዳ የሚያስፈጽሙ ናቸው። ህዝብን በቀላሉ እንዲገዛ የሚያደርጉ ናቸው።
ህብረተሰቡ ለራሱ ሰላም እንዲቆምና እንዲታገል የሚፈልጉ የFUD ተቃራኒ መልእክቶችን ነው ማስተላለፍ የለባቸው።
ቀጥታ ምሳሌ ልሰጣችሁ። ብልጽግና አማራንና ኢትዮጵያን አደጋ ላይ እየጣላት ነው ብለው የሚያምኑት ዛሬ ምንድነው የፕሮፖጋንዳ መልእክቶቻቸው ምንድ ነው መሆን ያለበት? ዛሬ ከሞላ ጎደል 100% መልእክቶቻቸው አሉታዊ ነወ፤ ባጭሩ "ብልጽግና የጠፋናል" ነው። የFUD መልእክት ነው ህዝቡ ተስፋ ቆርጦ ወደ ተግባር እንዳይሄድ ያደርገዋል። በተዋራኒው 100% መልእክቱ መሆን ያለበት ህብረት ፍጠር፤ ተደራጀ፤ እርስ በርስ ተዋወቅ፤ አንድ ሁን፤ ተዘጋጅ፤ ወዘተ። ይህ መልእክት የህዝቡን ስነ ልቦና ከተጽእኖ ተደራጊ ወደ ተግባረኛ ይቀይረዋል። ቤቱ ቁጭ ብሎ ከሚያዝን ወደ ራስ ማዳን ስራ እንዲገባ ይገፋፈዋል። ይህ ነው የሚፈለገው።
በግሌ መንግስት በጎብዝም ባይረባም በኢትዮጵያዊነት የሚያምነው ህብረተሰብ ወደ ስራ ካልገባና ካልተደራጀ ከባድ ጉዞ ነው የሚሆነው። በFUD የተጠመደ ህዝብ ለራሱ አደጋ ነው።

Saturday, 9 March 2019

የአዲስ አበባ ህዝብ ማለት...

በሩን ከፍቶ የሚያድር ሰው ዘራፊው ሲመጣበት እባክህ አትዝረፈኝ ብሎ የሚለምን።

ሳያርስ ሳይዘራ የክረመ ገበሬ አዝመራ ሳይኖረው እግዚአብሔርን የሚያማርር።

አትንቶ የማያውቅ ተማሪ ፈተናውን ሲወድቅ አስተማሪውን የሚወቅስ።

ወዘተ።

የአዲስ አበባ ህዝብ (ከነ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ) ለዓመታት በትንሿ ህወሓት የተገዛው የራሱን የቤት ስራ ስላልሰራ ነው። ይህ የቤት ስራ ተደራጅቶ ለራስ መብት መቆም ነው።

ካሁን ወድያ የአዲስ ህዝብ ካልተደራጀ ለሚደርስበት ጉድ ከራሱ በቀር ማንም ጥጠያቂ አይኖርም። የአምስት ሚሊዮን ህዝብ ከተማ መቶ ሚሊዮን ብር በጀት፤ አንድ ሚሊዮን አባል ያለው ድርጅት ማቋቋም ካልቻለ በቅኝ ግዛት መገዛት ይገባዋል አይቀርለትምም።

Friday, 22 February 2019

የጅልነት ፖለቲካ

አክራሪ የኦሮሞ ብሄርተኝነት በተለያየ መንገድ ፍላጎታቸውን በአዲስ አበባ ህዝብ ላይ መጫን እንደሚፈልጉ ገልጸዋል። አቋም ከመውሰድ እና ከመናገር አልፎ በተግባር ስራቸውን ሰርተዋል። የአዲስ አበባ «ወጣቶችን» በጅምላ አስረዋል። አዲስ አበባን እናደራጅ ያሉትን አስረው አስፈራርተዋል። ከለገጣፎ አፈናቅለዋል። ወዘተ። እንዲህ በማድረግ አክራሪው ቡድን አቅታጫውን በግልጽ አስቀምቷል። የማስፈራራት ዘመቻውን ቀጥሏል።

ለነገሩ ይህ (ይቅርታ አድርጉልኝ) የጅልነት ፖለቲካ አካሄድ ነው። የሚበጃቸው የነበረው የአዲስ አበባ ህዝብን ሳያስቀይሙ ሳይነሳሱ ቀስ ብለው ውስጥ ለውስት ስራቸውን መስራት ነበር። ግን የጡንቻ አካሄድ መርጠው የአዲስ አበባ ህዝብን ያናድዳሉ እና ተነስቶ እንዲደራጀና መብቱን እንዲያስከበር ያደርጉታል።

ይህ ነው የጅልነት ፖለቲካ። ግን ምና ያመጣሉ ነው ይህን የሚያደርጉት! የአዲስ አበባ ህዝብ እና ጠቅላላ የኢትዮጵያ ብሄርተኛ ጎራው ምን ያመጣል ነው። ስለዚህ ማን ነው ጅሉ። እኛ ነን።

Thursday, 1 November 2018

Ethiopia's Distorted Political Landscape

I believe that, today, the main hurdle facing Prime Minister Abiy Ahmed et al as they work on solving Ethiopia's various political problems is the imbalance between the ethnic nationalist and civic nationalist (Ethiopianist) elites. This imbalance has resulted in a distorted political landscape, a distortion which if left uncorrected, will continue to obstruct any possible progress.

What exactly is this distortion? Today, ethnic nationalist elite power and institutional power adequately reflects the level of support for ethnic nationalism among the masses. On the other hand, civic nationalist elite power and institutional power greatly under represents the level of support for civic nationalism among the masses. In simple terms, let us assume half the general population supports civic nationalism and the other half ethnic nationalism. The problem is that 80% of the political elite, in terms of political parties, power, organized influence, and institutional power, is composed of ethnic nationalists. The civic nationalist elite is running at 20%. That is, our political elite is overwhelmingly dominated by ethnic nationalists, while the general population is at worst evenly split between ethnic nationalism and civic nationalism. This political distortion is, in my opinion, the overarching problem in Ethiopian politics that continues to prevent any kind of reality-based, serious negotiations among our political elites.

While the ethnic nationalist elite hopes to use this disproportionate leverage that it has gained from over 27 years of domination to its advantage, the civic nationalist elite are too weak to respond constructively. The under represented civic nationalist masses absolutely refuse to give in to any kind of ethnic nationalist agenda. We have an impasse. Unless the 'elite distortion' is corrected, the impasse will continue and we will never be able to take solid steps towards a robust and long lasting political settlement.

Now, obviously, many would question my premise that there still is today in Ethiopian massive support for civic nationalism. Many would say that no, there is not much support for civic nationalism today in Ethiopia, and the weakness of its elite properly reflects this low support. Well, let me address this briefly. Since we do not have any polls in Ethiopia, we have to take various indicators as evidence when we make our arguments. Let us look at these indicators.

First, there is a good argument to be made that there are reasons for the weakness of the civic nationalist elite that have nothing to do with dwindling support for civic nationalism among the general population. Over the past fifty plus years, the civic nationalist elite has suffered from tremendous internal conflict - two endogenous revolutions and upheavals - the 1974 revolution and the Red Terror - and then one exogenous revolution, the 1991 revolution. The end effect of all of this was more or less the ousting of civic nationalist elites from Ethiopian political space.

Another external factor that weakened the elite was the rise of Marxism, which not only divided the Ethiopianist elite and infected it with a culture of self-mutilation, but also weakened the country with poor political and economic policies. This weakened not only the country as a whole, but also the elite, as it resulted in the masses becoming alienated from the leadership. And then add to this another factor - the fall of Marxism (Soviet Union), an event which led to the sudden and ungraceful collapse of the Dergue. And to all of this we can add another, underappreciated factor - a political culture of nearly devoid of conflict resolution. All of these factors contributed to a massive implosion of the civic nationalist elite, an implosion which had little to do with its constituency among the masses. The elite collapsed while its constituency remained more or less intact.

The subsequent 27 years of ethnic nationalist rule by the TPLF, with its sustained anti-civic nationalism propaganda and policies, can be said to have increased overall support for ethnic nationalism among the population. Again, we have no polls, but there is enough anecdotal evidence to make this argument. However, there is also evidence that this increase in ethnic nationalism is often over-estimated. Take, for example, what we can take away from the case of the 2005 elections. The civic nationalist Kinijit won an easy majority of the national vote in this election, and Kinijit together with the Hibret, a coalition of soft ethnic nationalists, won 70% of the total vote (before the rigging started). This result was quite unexpected at the time, and one reason why it was unexpected was that few thought that there remained so much support for civic nationalism. The results of the vote showed that even after 14 years (1991-2005) of TPLF propaganda against civic nationalism, civic nationalism was alive and strong.

Today, after 13 years after the 2005 election, there is more anecdotal evidence of the decline of civic nationalism support; for example, the increase in heretofore unheard of Amhara nationalism. But on the other hand, we have seen overwhelming support nation-wide for Prime Minister Abiy Ahmed and Oromia President Lemma Megersa, a large part of the support obviously stemming from their Ethiopianist rhetoric and positions. This outpouring of support for PM Abiy et al clearly shows that civic nationalism, among the masses at least, is alive and well in Ethiopia. So yes, all in all, I think it is safe to say that today, at least half of the Ethiopian population firmly support civic nationalism.

But how is this population represented among the political elite and in political and governmental institutions? The civic nationalist populace today has basically two elite representatives - Ginbot 7, and a part of the EPRDF, that represented by Abiy Ahmed, Team Lemma, et al. I argue that this representation is quite inadequate given the level of civic nationalist support among the masses.

Let us start with the EPRDF... The EPRDF was a full fledged ethnic nationalist coalition that is now being transformed from within towards civic nationalism. But transforming this decades old institution will deep rooted tentacles will take time. Ethnic nationalists are, obviously, resisting that transformation with full force. As a result, the EPRDF is yet to make a solid connection with the civic nationalist masses. Instead, it remains focused on this internal battle, the battle we are all familiar with, the battle that Abiy Ahmed and his team is currently engaged in. Now, to ensure that civic nationalism wins this battle, civic nationalists have to do two things. The first is to capture the EPRDF from within by changing minds, and the second is to capture it by, where possible joining the various EPRDF parties and basically outnumbering the ethnic nationalists and changing the power balance. As of yet, this process still at its beginning stages. So the EPRDF today cannot be said in anyway fully represent the civic nationalist population. There is a long way to go.

Ginbot 7, a brave and valiant party, basically the only civic nationalist party of any consequence, remains too small both in terms of membership and resources, to adequately represent the Ethiopianist masses. A clear illustration of this gap between the capacity of Ginbot 7 and the support for civic nationalism is the situation of Addis Ababa, where the vast majority of the city clearly supports civic nationalism, and yet there is not a single group, including Ginbot 7, which has harnessed this support into an organized and powerful political or civic force. Hence we have an Addis Ababa populace that, because it has no organized representation, feels powerless in the face of what it thinks is encirclement by ethnic nationalism. Easily over 80% of Addis Ababa's population of about five million are firm supporters of civic nationalism. How is it that such a large and resourceful population feels powerless? Because it is not organized - it is insufficiently represented among elites and institutions. Not because it is outnumbered, not because it is a minority, and not because it lacks in raw resources and capacity, but because it is unorganized, unrepresented, and incapable of mobilizing its resources. This example of Addis Ababa clearly illustrates the lack of capacity of Ginbot 7 has today.

Let us look, on the other hand, at the ethnic nationalist end of the scale. Clearly, the ethnic nationalist population has been well represented by its elites for the past 27 years. During this period, the ruling party has been ethnic nationalist, and all institutions, including the educational institutions, have been captured by ethnic nationalists in terms of numbers, propaganda, and policy. Even though today, the EPRDF is reforming towards civic nationalism, the institutional attachment to ethnic nationalism remains. Even today, ethnic nationalists in the party still hold significant power especially in Oromia and among the lower ranks. Given the size and nature of the EPRDF, it will take a long time for it to shed ethnic nationalism and then to connect with the civic nationalist population. Apart from the EPRDF, ethnic nationalist opposition parties, especially Oromo ones, are relatively well organized from top to bottom. In general, I don't think anyone would claim that the ethnic nationalist population lacks for elite representation in any way.

So there we have it, a relatively strong ethnic nationalist elite and a relatively weak civic nationalist elite. And at the same time, the division among the population at large between ethnic nationalism and civic nationalism is at most 50-50. A distorted political reality. Half the population is well represented but the other half is not.

How does this situation prevent Ethiopian politics from proceeding to a reasonable settlement? Well, given the distorted reality, elite negotiation between a strong ethnic nationalist elite and weak civic nationalist elite will result in the ethnic nationalists having the disproportionate upper hand and gaining disproportionate rewards. The result is a disgruntled and fearful civic nationalist populace whose wishes have been ignored. This populace may in the short term acquiesce, but in the long term it will either rebel or itself become ethnic nationalist, increasing the level of ethnicism in the country. In both cases the result will be catastrophic conflict.

So basically, either the civic nationalist elite organizes into a capable force or the country spirals into conflict and chaos. Yes, this is an existential issue.

Unfortunately, the task of empowering the civic nationalist elite is not an easy one. Civic nationalism cannot rely on ethnic fervor to mobilize itself as ethnic nationalists can. Instead, it will be tough slogging. Perhaps it is the knowledge that this work is tough and difficult that has led many civic nationalist elite members - including political parties and media - to simply avoid facing it, and rather spend their time raising the decibels against ethnic nationalists. Of course, avoiding the necessary tough work is no solution. What must be done must be done, as painful and hard as it must be.

From now on, the one and only priority of civic nationalists must be to strengthen the elite. Time and resources on 'opposition' activities, such as analysing, commentating on, and criticizing others' political activities and events should be minimized. Instead, all energy should be directed towards strengthening existing institutions such as Ginbot 7, creating additional political and civic institutions, mobilizing the civic nationalist population, and capturing the EPRDF.

A last word... A precondition to empowerment of the civic nationalist elite is a certain unity of thought and direction heretofore unseen among them. The culture of conflict mismanagement illustrated, for example, by the Kinijit conflict of 2005-2008, the various party conflicts of the last few years (Andinet, Medrek, etc.), the EDU internal conflicts during and after the Dergue, etc. must be ended!


Friday, 19 October 2018

Don't make enemies before you can fight!

ቆቅ ሞቷን ጠራች ይባላል።

የኢትዮጵያ ብሄርተኞች በቂ እንዳልተደራጀን የታወቀ ነገር ነው። በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ አባላት ያላቸው ድርጅቶች ሊኖርን ይገባል ግን የለንም። በርካታ ሚሊዮኖች ብዙሃን አለን ግን ልሂቃን፤ መሪ እና ድርጅት ላይ እጅግ ደካማ ነን።

በተዘዋዋሪ የጎሳ ድርጅቶች ያው የጎሳ በመሆናቸው ትብብር እና አንድነት ስላላቸው ጠንካራ ናቸው። ሁከት እና ችግር ስለሚያጎለብታቸው እየጠነከሩም እየሄዱ ነው።

በዚህ ሁኔታ የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ዋና ስራ መደራጀት እንደሆነ ግልጽ ነው። የህልውና ጉዳይ ነው። የዜግነት ፖለቲካችንን ካላራመድን እና ግዙፍ ድርጅቶች ካልፈጠርን እኛም ሀገራችንም እንጠፋለን። ጠ/ሚ አቢይ ቢፈልግም ይህን ሊያደርግልን አይችልም። እኛ የራሳችንን ድርሻ ካልሰራን እሱም አቅም ያጣል። ለነገሩ እስከ ዛሬም ሀገራችን ላሳለፈችው ችግር ዋና ምክንያት የኛ በሚገባው አለመደራጀት ነው።

በዚህ ሁኔታ፤ ደካማ ሆነን፤ ዋና ስራችን እራሳችንን ማጎልበት እና ማደራጀት በሆነበት ጊዜ ጠላቶች ማፍራት ጅልነት ነው። አሁን ሁሉንም የማቀፍ ጊዜ ነው። የጊዜ መግዥያ ጊዜ ነው። ጠ/ሚ አቢይ፤ የጎሳ ብሄርተኞች፤ ህወሓት ወዘተ ሁሉንም ተጠንቅቀን ይዘን ወዳጅ መስለን መገኘት አለብን። የመደራጀት ስራችንን መስራት ነው ያለብን። ብልህ ፖለቲካ ማለት ይህ ነው።

ለምሳሌ የአዲስ አበባ ሲቪክ ድርጅት ለማቋቋም ሲጀመር ስለ ከንቲባው አለማንሳት። ወይንም ማሞገስ። ጽሁፍ እና ፖስተሮች በአማርኛ ብቻ ሳይሆን በኦሮምኛም ማዘጋጀት። አዲስ አበባ ለአዲስ አበቤዎች አይነት መፈክር ትቶ በቀላሉ «ለአዲስ አበባ ነዋሪ ሁሉ መብት ማስከበር» ነው ተልዕኯችን ማለት ነው! ወዘተ። ሀሳቡ ግልጽ ይመስለኛል።

ግን ይህን ከማረግ ፋንታ እንደ ቆቛ እንጮሃለን! ምንም ሳይኖረን አፍ ብቻ እንሆናለን። ባለን ጊዜ አንዴ ከጎሳ ብሄርተኞች ጋር አሁን ደግሞ አንዳንዶቻችን ከጠ/ሚ አቢይ ጋር ግብ ግብ እንገባለን። ገና ለመታገል አቅም ሳይኖረን ጠላቶች እናፈራለን። ይህን ማቆም አለበን፤ የህልውና ጉዳይ ነው። የ50 ዓመት የፋራ ፖለቲካችንን ማቆም ካላቆምን ሌላ እድል የሚኖረን አይመስለኝም።

አካሄዳችን መሆን ያለበት መጀመርያ ኃይልን መሰብሰብ። ይህን ለማድረግ ባይጥመንም የሚያስፈልገውን ነገር ማድረግ። ከሁሉም ጋር አብሮ መስራት ያስፈልጋል። እራስን አለማጋለጥ ያስፈልጋል። ኃይልን ከሰበሰብን በኋላ ደፈር ያሉ አቋሞች መያዝ እና ስራዎች መስራት።

በመጨረሻ ማለት የምፈልገው... ምን አልባት በመጮህ፤ መተቸት እና በመውቀስ ህዝባችን እንዲማረር እና እንዲቆጣ አድርገን በቀላሉ ይደራጃል ብለን እናስብ ይሆናል? ለዚህ ይሆን ብዙዎቻችን ዋናው የመደራጀቱን ስራ ትተን 100% ጊዜአችንን በመተቸት እና መወንጀል የምናጠፋው?

ይህ ከሆነ በጣም የተሳሳተ አስተሳሰብ ነው። አካሄድ ውድቅ እንደሆነ የ27 ዓመት ማስረጃ አለን! ለ27 ዓመት ህወሓት እና የጎሳ ብሄርተኞች ሲረግጡን ያሁሉ ሚሊዮን ህዝብ ሆነን አንዳች ግዙፍ ድርጅት ማቋቋም አልቻልንም። የወሬ፤ ጩሀት እና ትችት ፖለቲካ አልሰራም።

ህወሓት ከስልጣን የወረደው እነ ኢሳት ህዝቡ ሀውሓትን እንዲጠላ ስላደረጉ አይደለም። ህዝቡ በለቱ ኑሮ አይቷቸው ጠልቷቸዋልና! አልፎ ተርፎኦ ይህ ጸረ-ህወሓት ዘመቻ ምንም አይነት ጠንካራ ድርጅት አልፈጠረም። ያሁሉ ዓመታት ጩሀት በኋላ የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ትንሿ ግንቦት 7ን ብቻ ነው ያፈራነው።

ስለዚህ የጩሀት ፖለቲካ አይሰራም። ህዝቡን በፕሮፓጋንዳ አማርሮ ማደራጀት እንደማይቻል አይተናል። ህዝቡ በእውን በኑሮው ተማርሯል። የፖለቲከኞች ስራ ይበልጥ ተማረሩልኝ ማለት ሳይሆን ማደራጀት እና ለምሬቱ ትክክለኛ መስመር ማብጀት ነው። የኛ የኢትዮጵያ ብሄርተኞች የፖለቲካ ልሂቃን ይህን ማድረግ አልቻልንም። እስቲ አሁን እንሞክር።

Disarmed! አለች ርዕዮት ዓለሙ

በዛሬ እለታዊ ፕሮግራም የርዕዮት ዓለም አስተያየትን (https://www.youtube.com/watch?v=b1OuvNmwxeY) በተመለከተ...

ነጥቧ ከሞላ ጎደል እንዲህ ነው፤ እነ «ቲም ለማ» ከመጀመርያዉኑ በጭፍን አምነን መከተል («መደገፍ») አልነበረብንም። ለ«ዴሞክራሲ» መታገል መቀጠል ነበረብን እና እነ «ቲም ለማ» እውነትም ዴሞክራቶች ቢሆኑ መሃል መንገድ እንገናኛለን ነው። ዛሬ እነ ጠ/ሚ አብይ አድሎ እያሳዩ እየሆነ የፈራሁት ሁኔታ እየተከሰተ ነው ግን አሁን እኛ ለዴሞክራሲ የምንታገለው ቡድን እራሳችንን "disarm" አድርገናል። በተወሰነ ደረጃ "its' too late" ነው የምትለው።

ምን መሳርያ ኖሮን ነው "disarm" ያረግነው ነው ጥያቄው! እኛ ኢትዮጵያ ብሄርተኞች ከሁሉም ፖለቲካ ኃይሎች የመጨረሻ ደካማ ነበርን ዓመት በፊት ዛሬም እንዲሁ። ምንም "disarm" አላረግንም። ነው ግንቦት 7 ሀገር መግባት አልነበረበትም ወይንም ጥጥቁን መፍታት አልነበረበትም ነው? ዓመት በፊት በኦሮሚያ የነበረው ሁኔታ ይታወቃል። በኦህዴድ ያለው ሁኔታ ይታወቃል። «ጠባቦች» በርካታ ነበሩ አሁንም ናቸው። እንደ አብይ በነሱ ላይም ከነሱ ጋርም ነው የመንግስት ግልበጣ ያደረጉት። እኛ የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ኢሚንት ነው ያደረግነው።

ታድያ ዛሬ ጠ/ሚ አቢይ ፈልገውም ባይፈልጉም ኦሮሞ ብሄርተኞቹን ወድያው መቆጣጠር ባይችሉ ምን ይገርማል። የኢትዮጵያ ብሄርተኛው ቡድን ለ50 ዓመት መደራጀት ያልቻለው ዛሬም ስላልቻለ ነው ይህ የሚከሰተው። የአዲስ አበባ ህዝብ ገና ድሮ ቢደራጅ ኖር (ዋጋውን ከፍሎ) ይህ ሁሉ አይሆንም ነበር። ዛሬም ባለፉት ስድስት ወራት መደራጀት ይችል ነበር። አሁንም ይችላል። ላለመቻሉ እነ ጠ/ሚ አቢይን መውቀስ ተገቢ አይደለም። በፍፁም ተገቢ አይደለም። እንደልማዳችን የራሳችንን ችግር ሌላ ላይ እየለጠፍን ነው።

እኛ መጀመርያ ተደራጅተን ታክቲካል አላያንስ ከነ ጠ/ሚ አቢይ ጋር መፍጠር ነው። አሁን ላለውን ችግር እሱ ላይ ከመለጠፍ ፋንታ ስራችንን ሰርተን ብልህ ፖለቲከኞች ሆነን እራሳችንን አጎልብትን መገኘት ነው። ሀውሓት ያደረገው፤ ኦሮሞ ብሄርተኞች ያደረጉትን እኛ ሊያቅተን አይገባም።

ይቅርታ አድርጉልኝ ግን የኛ የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ፖለቲካ በመደራጀት ብቻ ሳይሆን በስልትም እጅግ ደካማ ይመስለኛል። የህዝብ/ብዙሃን ቁጥር አለን ግን ድርጅት የለንም። ስለዚህም አቅመ-ቢስ ነን። ልሰዚህ ይህ ጊዜ የማጎልበት ነው እንጂ የጠላት መፍጠር አይደለም!! እነ ጠ/ሚ አቢይን ጓደኛ አድርጎ፤ የጎሳ ብሄርተኞችን ዝም ብሎ፤ ወሬ ሳናበዛ ለመደራጀት እና ለመጎልበት እራሳችንን ጊዜ መስጠት አለብን። ይህ ነው ብቸኛ አማራጭ።

Wednesday, 17 October 2018

ኢትዮጵያን የሚገላት የአንድነት ኃይሉ ነው (ክፍል 3)

በደርግ ዘመን ብዙ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ስራ ከሀገር ውጭ (በዲያስፖራ) ነበር የሚደረገው ሀገር ውስጥ በነፃነት መስራት ስለማይቻል።

በዚህ ጊዜ ሻዕብያ እና ህወሓት ከዲያስፖራ በርካታ ገንዘብ እና ሌላ ድጋር እየሰበሰቡ ግዙፍ ተቋማት ሆነው ኢትዮጵያን አንቀጠቀጡ።

የ«ኢትዮጵያዊነት» ኃይል ግን «ዴሞክራት» (ኢዲዩ) እና «ማርክሲስት» (ኢህአፓ፤ መኢሶን፤ ደርግ ወዘተ) ሆኖ ተከፋፍሎ ቆየ። ኤዲዩ እርስ በርስ ተከፋፍሎ እና ተጣልቶ በፍጥነት እራሱን ከፖለቲካ ዓለም አባረረ! ማርክሲስቶቹ እርስ በርስ ተፋጁ፤ ሀገሪቷን አሰቃዩ እና ፈትፍተው ለጎሳ ብሄርተኞቹ አጎረሱ።

እኛ ኢትዮጵያዊ ብሄርተኞች አንድ አላማ ኖሮን መተማመን፤ መስማማት፤ አብሮ መስራት፤ መተባበር እና መደራጀት አለመቻል በሽታችን አሁንም አንቆ ይዞናል።

ኢትዮጵያን የሚገላት የአንድነት ኃይሉ ነው (ክፍል 1)

ባለፈው ኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት የኤርትራ ዲያስፖራ እንደልማዳቸው እየተሯሯጡ ለሀገራቸው ገንዘብ እያዋጡ ነበር። ምን ያህል አዋጡ? ልምሳሌ ያህል፤ በአንድ ቀን ከአንድ ከተማ ሲአትል (ዋሺንግተን ስቴት) አንድ ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር አዋጥተዋል! ከዋሺንግተን ዲሲ አይነቱ ብዙ ኤርትራዊ ያለበት ከተማ ምን ያህል እንደተዋጣ ባላውቅም መገመት ይቻላል።

ተወዳጁ «ኢትዮጵያዊነትን» የወከለው ቅንጅት ለሰላም እና ዴሞክራሲ ፓርቲ መሪዎቹ ከተፈቱ በኋላ ሰሜን አሜሪካ መጥተው ለወራት ቆዩ። ከመላው ሰሜን አሜሪካ የሚኖር ኢትዮጵያዊያን ከአንድ ሚሊዮን ዶላር በታች ሰብስበው (እና እርስ በርስ ተጣልተው) ተመለሱ!

የአንድነት ኃይሉ እርስ በርስ አለመስማማት እና አለመደራጀት ኢትዮጵያን ይገላል።

Monday, 26 March 2018

አማራጭ የፖለቲካ ልሂቃን ቡድን አለ?

በ2017/5አ.አ የተሳፈ ጽሁፍን አማርኛ ትርጉም

English version: https://asfawdarguemeshal.blogspot.ca/2017/05/alternative-political-elite.html

በ1983 ደርግ ፈርሶ ሻዕብያ ህወሓትና ኦነግ ወደ ስልጣን ሲገቡ መዐቱን ፈርተን ነበር። ምክንያቱም ሻዕብያ ህወሓትና ኦነግን እንደ ጎሳ ብሔርተኞች ሺፍቶች አገረን ለማፍረስ ኢትዮጵያን ለመገነጣጠል የሚመኙ አድርገን ስለቆጠርናቸው።

ዛሬ ከ26 ዓመት በኋላ ኢትዮጵያ ከነ በርካታ ችግሮቿ አሁንም አለች! ኤርትራ ብትገኝጠልም ጸንፈኛ የጎሳ አስተዳደር ቢጫንባትም ኢትዮጵያ ተርፋለች። ዋናው የተረፈችበት ምክንያት ብዙሃኗ ድሮም ዛሬም ባብዛኛው የአገር ብሔርተኛ አገርን ከ«ጎሳ» የሚያስቀድም ስለሆነ ነው። ይህ የህዝባችን ባሕሪ የህወሓትን ጸንፈኛ የጎሳ አቋምን ሊቋቋምና መልሶ ሊገፋው አብቅቶታል። እንደ የድሮ የቱርክ መሪ ከማል አታቱክር ህወሓት የአገር ህዝብን ወደ የማያምንበት አስተሳሰብ በግድ ሊጎትተው ፈለገ ግን ሙሉ ለሙሉ አልተሳካም። ህዝቡ የጎሳ ብሔርተኝነትን ህወሓት እንዳለመው ያህል አልተቀበለውም። በህዝቡ መካከል ኢትዮጵያዊነት አሁንም ጠንክራ ትገኛለች!

በእውነቱ የኢትዮጵያ ህዝብ ህወሓትን አብርዶታል ማለት ይቻላል። ይህን ለመረዳት እስቲ ወደ የኢህአዴግ የመጀመርያ 10 ዓመት ግዛት ወደ ኋላ ሄደን እንመልከት። በዛን ዘመን በተለይ ከኢርትራ ጦርነቱ በፊት «ጠባብ የጎሳ ብሔርተኛ» የሚል አባባል አልነበረም። «ነፍጠኛ» «ትምክህተኛ» በቻ ነበር ህወሓት የሚዘፍነው። ህወሓት ሁሉንም «ጎሳዬ ከኢትዮጵያዊነቴ ይበልጣል» እንዲል ያበረታታ ነበር። «መጀምርያ ኦሮሞ ነኝ ሁለተኛ ኢትዮጵያዊ» ወይም «መጀመርያ ትግሬ ነኝ ሁለተኛ ኢትዮጵያዊ» ማለት የተለመደ ነበር። «ኢትዮጵያዊነት» የሚጠቃ የሚሾፍበት ነበር። አሁን ግን እንደዚህ አይነት ቴአትር ቀንሷል። «ጠባብ» የሚለው ቃል ወደ ፖለኢትካ ቋንቋችን ገባ። ኢህአዴግን ችራሽ ኢትዮጵያዊ እኔና እኔ ብቻ ነኝ ማለት ጀመረ! ህወሓት ድሮ የሚሰብከውን ጸንፈኛ የጎሳ ብሔርተኝነትን ዛሬ እንደ ማነቆ ነው የሚያየው።

ለዚህ ለውጥ የኢትዮጵያ ህዝብ ሊመሰገን ይገባል። የህዝባችን ጠንካራ አገር ፍቅርና የአገር ብሔርተኝነት ነው አገሪቷን ከከባድ አደጋ ጠብቆ በህይወት ይሚያኖራት። አስገራሚ ነገር ግን ይህ የህዝባችን ድል አለ ልሂቃን ጎራ በብዙሀኑ ኃይል በቻ መደረጉ ነው። ከላይ እንደጠቀስኩት በ1983 የፖለቲካ ልሂቃን ሲባል ሻዕብያ ህወሓትና ኦነግ ብቻ ነበሩ ልሂቃንም የወታደር ኃይልም ከነሱ ነበር። ሌላው ወገን የኢትዮጵያ ብሔርተኛ  ወይም «አገር ወዳድ» ጎራ ኃይልም ልሂቃንም አልነበረውም። ይህ ልሂቃን ከአገር ፖለቲካ ጠፍቶ ነበር።

የጠፋው ምክንያት ይህ ልሂቃን ጎራ የረዥም ዓመት የራስ ማጥፋት ዘመቻ አካሄዶ ስለነበር ነው። ከ1950 አካባቢ ጀምሮ የኃይለ ሥላሴ ተማሪዎችና ልሂቃን በእርስ በርስ መተላለቅ በራስ ማጥፋት ምኞት መለከፍ ተጥቅቶ የራሱን ማጥፋት ስራ ብ1983 አብዮቱ አጥናቀቀ። እራሱን አንዴ አድሃሪ አንዴ ፍዩዳል አንዴ ኢህአፓ አንዴ ምኤሶን አንዴ ኢዲዩ አንዴ ደርግ ወዘተ እያለ እርስ በርስ ተፋጅቶ እራሱን ገደለ።

ለዚህም ነው ሽዐብያ ህወሓትና ኦነግ በ1983 በስልጣን ጉዳይ መደራደር ሲጀምሩ የኢትዮጵያ ብሔርተኛ ወቂል የፖለቲካ ወይም የጦር ኃይል ያልነበረው። ለኢትዮጵያ የሚቆምላት ልሂቃን አልነበረም። ልሂቃኑ ይህ ስራን ለብዙሓኑ ተውወው ግን ብዙሃኑ ስራውን በአቅሙ ሰርቷል።

ዛሬም የኢትዮጵያ ብሄርተኛ ልሂቃን ጎራ ከሞላ ጎደል የለም። ይህ ሊደንቀን አይገባም። የፖለቲካ ልሂቃን ባንዴ አይነሳም፤ የረዝም ዓመትና የትውልድ ውጤት ነው። የኢትዮጵያ ብሄርተኝነት ልሂቃን ጎራ በ1983 የራሱን ማጥፋት ዘመቻ አጠናቅቆ ከዝያ ወዲህ ኢህአዴግ እንዳይነሳ ብቻ ነው ያደረገው። ስለዚህ ይህ ልሂቃን ዛሬ በሽተኛ የቀጨጨ ከወላጆቹ ከአባቶቹ ተለይቶ ምንም ውርስ ግንኙነት ዬሌለው ህጻን ይመስላል።

ለዚህ የልሂቃኑ ችግር ምክንያት ይኢህአዴግ ጭቆና ብቻ ነው? በፍጹም! ቢሆን ኖሮ ቢያንስ በውጭ አገር ኢህአዴግ በማይደርስበት ቦታ ይህ ልሂቃን ጠንክሮ ይገኝ ነበር። ግን የለም። በተጨማሪ የቅንጅት የምርጫ 1997 ቀውስ የተፈጠረው በኢትዮጵያ ብሄርተኛ ልሂቃኑ መሆኑን እናውቃለን። ልሂቃኑ ባለመብሰሉ ምክንያት ያስከተለው የእርስ በርስ ቅራኔ ነው ቅንጅትን ያፈረሰው። ዛሬም አገር ውስጥም ውጭም የቅንጅት ርዥራዞችና ተከታዮቻቸው እየተፋጅን ነው። እነዚህ መረጃዎች ለኢትዮጵያ ብሄርተኝነት ልሂቃኑ ድክመት በቂ መረጃ ናቸው።

ስለዚህ የኢህአዴግ ጭቆና ነው የኢትዮጵያ ብሄርተኛ ልሂቃንን ያደከመው ማለት አይቻልም። ኢህአዴግም ቢጠፋ ይህ ልሂቃን ጠንክሮ ይገኛል ቃልን እራሳችንን ማታለል ነው። የልሂቃኑ ውድቀት ረዝም ዓመት የፈጀ ውስብስብ ታሪክ ነው። በዚህ ረገድ ይህ ልሂቃንን ከሞት ለማስነሳት እንደዚሁ ረዝም ጊዜ ሊፈጅ ይችላል። አንድ ልሂቃን ጎራ ባንዴ መጎልበት አይቻልም። ግን እስከዛ ብዙሃኑ ልቆ ሄድዋልና መሪ ይፈልጋል።

ስለዚህ ወዴት ነው ማምራት የምንችለው? የጎሳ ብሄርተኝነት እንዲቀንስ፤ ጭቆና ኢፍትሓዊነት፤ የስነ መግባር እጦትና ሙስና በአገራችን እንዳይኖር፤ ፖለቲካና ሌሎች ጉዳዮችን በሰላም የምንወያይበት መድረክ የምንፈልግ ምን እናድርግ? አገራችን ህዝቦቿ በምትወደው በምታከብረው መንግስት እንድትገዛ የምንመኝ ምን እናድርግ? አገር ወዳድ መንግስት የምንፈልግ ምን እናድረግ?

በይፋ ንቅናቄዎች ድርጅቶች ፓርቲዎች ማቋቋም እንደማይሆን ግልጽ ነው! እስር ጽቃይ ሞትም ሊያደርስ ይችላል። በ50 ዓመት እራስ ማጥፋት ዘመቻ ምክንያት የደከመ የተቃዋሚው ልሂቃን እንደዚህ አይነቱን ጭቆና ሊቋቋመው አይችልም። ያለፉት 26 ዓመት ታሪክ ይህን አሳይቶናል። ከዚህ የተለየ የርቀቀ አካሄድ ያስፈልጋል።

ይህ አካሄድ ያለው የፖለቲካ ሥርዓት ማለትም ኢህአዴግ ውስጥ ገብቶ ውስጥ ሆኖ መታገል ነው። ዛሬ ኢህአዴግ ብቸኛ አቅም ያለው የፖለቲካ መዋቅር ስለሆነ ይህን መዋቅርን ተቆጣጥሮት የለውጥ አጋር ማድረግ ነው ስራችን የሚሆነው።

«አይሆንም» ይላሉ ተስፋ ቆራጮቹ! ህወሓት ይህን መቼም አይፈቅደም ይላሉ በዛው አፋቸው ህወሓት የአገራችን 8% ብቻ ነው የሚወክለው ይላሉ! ግን 8% በጣም ትንሽ ስለሆነ 92% የሆነው ህዝብ ትንሽ ብቃት ቢኖረውም ሁኔታውን ለመቀየር በቂ ነው። እንደ የሩስያ መሪ ቭላዲሚር ፑቲን ከነበረው ሥርዐት ውስጥ ሆነው ማንነታቸውን ደብቀው ሙሉ ስልጣን እስከሚይዙ ፕሬዚደንት ሆኖ ሩሲያን 180 ዲግሬ የቀየራት ኢትዮጵያ ውስጥም እንደዚህ ማድረ ይቻላል። መቼም እንደ እባብ ልባሞች እንደ ርግብም የዋሆች መሆን ያስፈልጋል! በመጀመርያ ካለው የፖለቲካ አዝማምያ ጋር አብሮ መሄድ ያስፈልጋል። ቀስ በቀስ ራስን ባለማጋለጥ የፖለቲካ ተከታይነትና ኃይል ማከማቸት ያስፈልጋል። በስልጣን ደረጃ ከፍ ባለ ቁጥር ባለው የስልጣን መጠን መጠቀም ፍላጎትን ማስፈጸም ይችላል። በዚሁ ረገድ ህሊና ያለው ሰው የፓርቲውን ፖለቲካ እየተከተለ ሰው ላይ ጉዳት ሳይፈጽም ኢፍትሃዊ ድርጊቶች ሳያደርግ በብልጠት ስራውን መስራት ይችላል። የፖለቲካ ተጎጂዎችንም ሊረዳ ይችላል።

ይህ አይነቱ ስራ ታላቅ የፖለቲካ ብስለትና ሙያ ይጠይቃል ከባድ ስራ ስለሆነ። ግን ለጊዜው በኢትዮጵያ የፖለቲካ ሁኔታ ብቸናው መንገድ ነው። አለበለዛ ቅጭ ብሎ ከእግዚአብሔር መብረቅ መጠበቅ ወይም ህዝባዊ አመጽ መጠበቅ ይሆናል። መቆጣጠር የማይቻል ለአገር ይበልጥ አስጊ የሆነ ችግርን መጠበቅ ይሆናል።

ስለዚህ በኔ አመለካከት የኢትዮጵያን ፖለቲካ ወደ ጥሩ መንገድ ለመምራት ፍላጎት ያላቸው የኢትዮጵያ ብሄርተኛ የሆኑ ግለሰቦች በኢህአዴግ ቀመጠቀም ብዙ አማራጭ የላቸውም። አማራጭ ሊሆን የሚገባው የኢትዮጵያ ብሄርተና ልሂቃን ድርጅት ከ50 ዓመት የራስ ማጥፋት ዘመቻው ገና አልዳነም። ይህ አይነት ድርጅት ወይም ንቅናቄ አጠንክሮ ለማቁቋም እስካሁን አልቻልነውም የረዝም ዓመት ስራ ነው የሚሆነው። ሌሎች አማራጮች እንደ መንግስት ላይ የዓለም አቀፍ ተጽእኖ ማስነሳት ወይም የተቃዋሚ ፓርቲ ማቋቋም እስካሁን አልሰሩምና ውጤታማ አልሆኑም። ስለዚህ ወደ መሳካት የሚችለው ስራ እንግባ፤ ኢህአዴግ ዙርያውን ሰርጎ ገብተን እንቆጣጠረውና በዛ መንገድ ለውጥ እናምጣ።