Showing posts with label disempowerment. Show all posts
Showing posts with label disempowerment. Show all posts

Wednesday, 17 October 2018

ኢትዮጵያን የሚገላት የአንድነት ኃይሉ ነው (ክፍል 3)

በደርግ ዘመን ብዙ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ስራ ከሀገር ውጭ (በዲያስፖራ) ነበር የሚደረገው ሀገር ውስጥ በነፃነት መስራት ስለማይቻል።

በዚህ ጊዜ ሻዕብያ እና ህወሓት ከዲያስፖራ በርካታ ገንዘብ እና ሌላ ድጋር እየሰበሰቡ ግዙፍ ተቋማት ሆነው ኢትዮጵያን አንቀጠቀጡ።

የ«ኢትዮጵያዊነት» ኃይል ግን «ዴሞክራት» (ኢዲዩ) እና «ማርክሲስት» (ኢህአፓ፤ መኢሶን፤ ደርግ ወዘተ) ሆኖ ተከፋፍሎ ቆየ። ኤዲዩ እርስ በርስ ተከፋፍሎ እና ተጣልቶ በፍጥነት እራሱን ከፖለቲካ ዓለም አባረረ! ማርክሲስቶቹ እርስ በርስ ተፋጁ፤ ሀገሪቷን አሰቃዩ እና ፈትፍተው ለጎሳ ብሄርተኞቹ አጎረሱ።

እኛ ኢትዮጵያዊ ብሄርተኞች አንድ አላማ ኖሮን መተማመን፤ መስማማት፤ አብሮ መስራት፤ መተባበር እና መደራጀት አለመቻል በሽታችን አሁንም አንቆ ይዞናል።

Thursday, 11 October 2018

መልዕክት ለኢሳቶች…

አቤቱታ፤ ማማረር፤ ማልቀስ፤ complaining ህዝብን ተስፋ እንዲቆርት ያደርጋል። ይህ ከኢሳት ተዕልኮ የሚጻረር ነው።

እንደ አንድ ተራ ዜጋ ምክሬ እንዲህ ነው፤ ስለ ችግሮች ለ10 ደቂቃ ካወራችሁ ስለ መፍትሄ እና አማራጭ መንገዶች ለ20 ደቂቃ ተወያዩ። አዋጪው መንገድ ይህ ይመስለኛል።