Written February 2022
የሰላም ክፍሌ ይትባረክ ብሎግ፤ ስለ ሀገራችን ኢትዮጵያ ያለኝን ትናንሽ ሀሳቦች በትህትና አቀርባለሁ። ለስሕተቶቼም በቅድሚያ ይቅርታ እጠይቃለሁ
Wednesday, 2 November 2022
FUD
Thursday, 16 December 2021
የሃላፊነት ፖለቲካ
የታወቀው የመካከለኛ ምስራቅ ታሪክ ምሁር በርናርድ ልዊስ የአረብ ፖለቲካ ባህል ድክመትን ለመተቸት እንዲህ ብሎ ነበር፤
“When people realize things are going wrong, there are two questions they can ask......One is, ‘What did we do wrong?’ and the other is, ‘Who did this to us?’ The latter leads to conspiracy theories and paranoia. The first question leads to another line of thinking: ‘How do we put it right?’”
ትርጉም፤ «ህዝብ ነገሮች እየተበላሹ እንደሆነ ሲገነዘብ ሁለት አይነት ጥያቄዎችን መጠየቅ ይችላሉ፤ አንዱ «ምን ተሳስተን ነው?» ነው፤ ሌላው ጥያቄ «ማን ነው እንደዚህ ያደረገን ነው?» የመጨረሻው አይነት ጥያቄ ወደ ሴራ፤ ፍረሃትና ጥርጣሬ ይመራል። የመጀመርያው ጥያቄ ግን «እንዴት ነው ነገሮችን የምናስተካከለው» ወደሚለው ይመራል።
የዚህ አባባል ትርጉም ባጭሩ እንዲህ ነው፤ ችግርህን ሙሉበሙሉ የጠላቴ ጥፋት ነው ካልክ ለጠላት ያጋለጡህን የራስህን ድክመቶች አታምንም አታርምም። ጠላትን በቀጥታ በማጥፋት ላይ ብቻ ታተኩራለህ፤ ካቃተህ ተስፋ ትቆርጣለህ።
ምሳሌ፤ ህወሓት ስልጣን ከያዘ ጀምሮ ተቃዋሚዎች መደራጀት ሳይችሉ፤ ገንዘብና አቅም መሰብሰብ ሳይችሉ፤ ምንም አይነት የተደራጀ የህዝብ ድጋፍ መሰብሰብ ሳይችሉ እነዚህ መሰረታዊ የህልውና ችግራቸውን ከማረም ይልቅ ያላቸውን ጊዜና አቅም ህወሓትን በመኮነን ብቻ አባከኑ። በዚህ ምክንያት ተቃዋሚዎቹ ህወሓትን ሊጎዱት አልቻልም። መጨረሻ ላይ ህወሓት የፈረሰው በራሱ ያጠመደው የጎሳ ብሄረተኝነት አደጋ ነው።
ዛሬም የኢትዮጵያዊነት የፖለቲካ ጎራ ተመሳሳይ ስህተት ላይ ይመስለኛል። ችግራችን ሁሉ የህወሓት ጥፋት ነው እያለ የራሱን ችግር እንኳን ለመፍታት ለማመንም ዝግጁ አይመስለኝም። ለምንድነው ህወሓት እንደዚህ ጠንክሮ የሚቀናቀነን? ለምንድነው መጀመሪያውኑ ህወሓት ሊገዛን የቻለው? ህወሓት ከየት ነው የመጣው? እነዚህ ጥያቄዎች ጥይቀን በትክክል ብንመልስ የራሳችንን ድክመቶች አይተን አርመን ህወሓትን በተሻለ ደረጃ መግጠም እንችላለን። ግን አላደረግነውም። በራሳችን ላይ ግምገማ አላደረግንም። ስህተቶቻችንን አላመንም። አላረምንም። በዚህ ምክንያት አላስፈላጊ ዋጋ እየከፈልን ነው።
መሆን የነበረበት እራሳችንን በዚህ መንገድ መገምገም ነበር፤ 1) ማርክሲስት ሆነን እርስ በርስ በመጣላታችንና ሀገሪቷን በማድከማችን እራሳችን ነን ህወሓትን የፈጠርነው ወይንም እንዲፈጠር ሜዳውን ያዘጋጀነው፤ 2) ሀውሓት ለረጅም ዓመታት የገዛን ምክንያት እኛ ቁጥራችን እጅግ አብላጫ ቢሆንም አብሮ መስራትና መደራጀት ስላቻልን ነው፤ 3) ዛሬም የህወሓትን ጦርነት በአጭሩ መጨረስ ያልቻልንበት ምክንያት አንድ ሆነን ተማምነን ተናበን መስራት ስላልቻልን ነው።
እራሳችንን በዚህ መንገድ ከገመገምን የችግሩ መፍትሄን አገኘን ማለት ነው። የፈረንጅ ጸረ ኢትዮጵያ የሆነ እንደ ማርክሲዝም አይነት ፖለቲካዊ አስተሳሰብ ጎጂ እንደሆነ ተረድተን ከዛ አይነት አስተሳሰቦች እራሳችንን እናርቃለን። መተባበርና አንድ መሆን የግድ እንደሆነ ተረድተን ጥርጣሬ፤ መጠላለፍ፤ ምቀኝነት፤ ትእቢት ወዘተን አስወግደን በአንድነት እንሰራለን። እርስ በርስ ያሉንን ትናንሽ ልዩነቶች እንቅፋት እንዳይሆኑን ለትክክለኛው ጊዜ ና መድረክ ትተናቸው በአንድነት እንሰራለን። ለህወሓት ጥቃት ያጋለጡንን መሰረታዊ ችግሮቻችንን አርመን እንገኛለን። ይህንን ካደረግን ጠላትን በቀላሉ እናስወግዳለን።
Wednesday, 5 September 2018
ልማት ሀገርን አይገነባም!
ለማስታወስ ያህል የተወሰነ ዓመት በፊት ህዝብን የምርጫ 1997 ችግርን ለማስረሳት፤ «ጠባብ» የጎሳ ብሄርተኝነትን ለመዋጋት፤ መንግስትን ሊጥል የሚችል መሃበረሰባዊ ክፍፍልን ለማስወገድ ኢህአዴግ «ልማታዊ መንግስት» ብሎ አወጀ። ኦሮሞ፤ አማራ፤ ትግሬ፤ ሲዳማ ወዘተ ብሄር ብሄረሰቦች አንድ መሆን ባይችሉም በ«ልማት» ዙርያ አንድነት ይፈጥራሉ ወይንም ግጭት ይቀንሳሉ ተብሎ ነው «ልማት» የታወጀው (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2016/10/ethnic-federalism-kills-meles.html)። የዚህ የልማት ዘመቻ ደግሞ ታላቁ መሪ መለስ ዜናዊ ነው ተብሎ የሳቸው ምስሎች ከነ ልማት ምስሎች ጋር በማርክሲስት አይነት ስዕሎች በየቦታው ተለጠፉ።
ልማቱ መጣ ኤኮኖሚው በፍጥነት አደገ። ግን ህዝቡ ይበልጥ ተከፋፈለ። ግጭቶች እየጨመሩ እየጠነከሩ ሄደ። ሰላም እና ፍቅር እየጠፋ ሄደ። የግብረ ገብ እጦቱ በአስፈሪ መልክ በዛ አገሩን አጠለቀለቀ (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/08/blog-post_31.html)። «ልማት» ወደ «ገንዘብ» ተተርጉሞ ለገንዘብ ብለን እናታችንን የምንሸጥ ስባዊነት-ቢስ ማህበረሰብ ሆንን። ይበልጥ ተከፋፈልን። «ልማት» የሚለው መፈከር አልሰራም።
ግን አሁንም ስለ «ልማት» እንሰማለን። «ለምን አንድ ሆነን ተፋቅረን ሁላችንም ወደ ልማት አንሄድም?» ይባላል። «ሀገራችንን በጋራ እናሳድጋት» ሲባል እንሰማለን። «አንድ ከሆነን ሀገራችን እንደ ሌሎች ሀገራት ትበለጽጋለች!» ይባላል።
አዎን ልማት እና እድገት አይከፋም። ግን ልማት ሀገር እና ህዝብ አያደርግም ወደፊትም ሊያደርግ አይችልም። ሀገር እና ህዝብ የሚያደርገን «ፍቅር» እና «ሰላም»፤ «እውነተኛ ዝምድና እና ትሥስር»፤ «መደጋገፍ» እና «መረዳዳት»፤ «አባቶችንና ተውፊትን በጋራ ማክበር» ወዘተ። እነዚህ ጊዜያዊ ሳይሆኑ ዘላቂያዊ ነገሮች ናቸው። ልክ እንደ ሃብት ቤተሰብን እንደማይፈጥር እንደማይገነባ ሀገርንም አይፈጥርም አይገነባም።
ይህን ስለተረዱ ነው ጠ/ሚ አብይ አህመድን ታላቅ የሚያረጋቸው። የሳቸው ትኩረት በጊዜያዊ አላፊ ትናንሽ ነገሮች ሳይሆን በከፍ ያሉት (higher) ነገሮች ነው። ህዝባችን ከልማት በላይ ደስታ እንዲኖረው ነው የምፈልገው ብለዋል። ይህ ደግሞ ለኢትዮጵያው ትውፊታዊ አመለካከት ነው። ኢትዮጵያዊ ከገንዘብ፤ ምቾት፤ ሃባት ወዘተ ይልቅ ፍቅር፤ ሰላም፤ ፍትህ ወዘተን ያስቀድማል በሃይማኖትን እና ትውፊቱ ምክንያት። ለዚህም ነው የጠ/ሚ አብይ መልዕክት ምዕራቢያዊያንን በሚያስገርም ሁኔታ ህዝባችንን ያስደሰተው።
ስለዚህ የኛ መሪዎች እና ፖለቲከኞች እንዲሁም እኛ ብዙሃን «ልማት» የሚለውን ጽንሰ ሃሳብ ላሁን ብንተወው እና ትክክለኛ ቦታው ብንሰጠው ጥሩ ይመስለኛል። ፍቅር እና ሰላማችንን እናዳብር። ክፍፍሎቻችንን በግልጽ እና በትህትና እንወያይ። ይቅርታ እንባባል እርስ በርሳችን እንቆርቆር። ሀገርን እንገንባ። እዚህ ላይ እናተኩር። ከዛ በኋላ ልማት እንደ ሁለተኛ ምርት (byproduct) ይመጣል። ባይፈጥንም ፍቅራችን ያኖረናል።
Friday, 13 July 2018
The Great Obang!
Well, what a delight it is that Obang has now found a leader, Dr Abiy Ahmed, even more naive than him! So naive that he's made peace, love, and reconciliation work.
Congratulations, Obang!
But, as you say, it's time to get down to work. There are many possible sources of division and instability in Ethiopia, particularly ethnic nationalism. We Ethiopian nationalists have to work overtime to remove the disease of division from ourselves so that we can confront ethnic nationalism from a position of strength, but in a peaceful, positive, constructive, empathetic, and just way.
Obang's latest interview on ESAT: https://www.youtube.com/watch?v=UJP05Mzp6f4