Saturday 9 March 2019

የአዲስ አበባ ህዝብ ማለት...

በሩን ከፍቶ የሚያድር ሰው ዘራፊው ሲመጣበት እባክህ አትዝረፈኝ ብሎ የሚለምን።

ሳያርስ ሳይዘራ የክረመ ገበሬ አዝመራ ሳይኖረው እግዚአብሔርን የሚያማርር።

አትንቶ የማያውቅ ተማሪ ፈተናውን ሲወድቅ አስተማሪውን የሚወቅስ።

ወዘተ።

የአዲስ አበባ ህዝብ (ከነ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ) ለዓመታት በትንሿ ህወሓት የተገዛው የራሱን የቤት ስራ ስላልሰራ ነው። ይህ የቤት ስራ ተደራጅቶ ለራስ መብት መቆም ነው።

ካሁን ወድያ የአዲስ ህዝብ ካልተደራጀ ለሚደርስበት ጉድ ከራሱ በቀር ማንም ጥጠያቂ አይኖርም። የአምስት ሚሊዮን ህዝብ ከተማ መቶ ሚሊዮን ብር በጀት፤ አንድ ሚሊዮን አባል ያለው ድርጅት ማቋቋም ካልቻለ በቅኝ ግዛት መገዛት ይገባዋል አይቀርለትምም።

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!