Showing posts with label alliances. Show all posts
Showing posts with label alliances. Show all posts

Friday, 19 October 2018

የወሬ ፖለቲካ

እኛ ኢትዮጵያ ብሄርተኞች ለ27 ዓመት ወያኔን ከመውቀስ ሌላ ስራ ባለመስራታችን የወያኔን ለሩብ ክፍለ ዘመን እንዲገዛ አደረግን። በቂ ጸረ-ወያኔ ፕሮፓጋንዳ ካሰራጨን ህዝቡ በአመጽ ይነሳል ብለን ገምተን ይሆናል ግን አልሆነም። በመጨረሻ አመጹን ያስነሳው ህዝቡ በእውን የትግሬ አድሎ በዝቶበት ነው። የትግሬ አድሎ አለ ብሎ በነ ኢሳት ስለተነገረ ሳይሆን ህዝቡ በለት ኑሮው ስላየው ነው (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2016/10/ethnic-federalism-kills-meles.html)።

ስለዚህ የወሬ ፖለቲካ እንደማይሰራ የ27 ዓመት ማስረጃ አለን። እኛ ኢትዮጵያ ብሄርተኞች 100% ጊዜአችንን ስለ ወያኔ በማልቀስ ከማዋል ፋንታ 50%ኡን ህዝብ እና ልሂቃንን በማደራጀት ብናውለው የት ደርሰን ነበር።

አሁንም አንዳንድ ጓዶቻችን የወሬ ዘመቻ በጎሳ ብሄርተኞች እና አሁን በ ጠ/ሚ አቢይ ማካሄድ ጠቃሚ ይመስላቸዋል። የድሮውን ስህተት መድገም። ለ27 ዓመት ያልሰርዋን መቀጠል። ምን ማለት ነው የማይሰራን ነገር መደጋገም?

ምን አልባት ውስጣችን ማደራጀት እና ሌሎች የእውነት የፖለቲካ ስራዎች ከባድ እንደሆኑ ስለምናውቅ ወሬ ላይ በማተኮር ማምለጥ እንፈልግ ይሆን። ወይንም ሻዕብያ እና ህወሓት ግዙፍ በህዝባቸው ጽናት ግዙፍ ድርጅቶች ሆነው ሲገኙ እኛ ኢትዮጵያ ብሄርተኞች የነሱን 1% የሚያክል ድርጅት መመስራት ስላቃተን አፍረን ይህንን ላለማየት ይሆን ወደ ወሬ ፖለቲካ የምንሸሸው። የዝቅተኛ ስሜት አድሮብን ይሆን 6% ድጋፍ ያለው ወያኔ ለ27 ዓመት ሲገዛን አንድ ጠንካራ ድርጅት መፍጠር ባለመቻላችን?

ምክንያቱ ምንም ቢሆን የወረ ፖለቲካ አይሰራም እና ካሁኑኑ አቅማችንን ከዛ ወደ ከባድ ስራው ወደ መደራጀት ማሸጋሸግ አለብን። ይህ ማለት ካሁን ወድያ ወሬ ሳይሆን ስራ መስራት። መሳደብ ሳይሆን ብልጥ ሆኖ ትብብሮችን መፍጠር ለጊዜውም ቢሆን እስከንደራጅ። ድልዲዮችን ከማቃጠል መጠቀም። እንደ ጠ/ሚ አቢይ አይነቱን ከማራቅ ማቀፍ እና መጠቀም። ይህ ነው ፖለቲካ። እንጂ ዝም ብሎ ማውራት መገዛት ማለት ነው።

Don't make enemies before you can fight!

ቆቅ ሞቷን ጠራች ይባላል።

የኢትዮጵያ ብሄርተኞች በቂ እንዳልተደራጀን የታወቀ ነገር ነው። በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ አባላት ያላቸው ድርጅቶች ሊኖርን ይገባል ግን የለንም። በርካታ ሚሊዮኖች ብዙሃን አለን ግን ልሂቃን፤ መሪ እና ድርጅት ላይ እጅግ ደካማ ነን።

በተዘዋዋሪ የጎሳ ድርጅቶች ያው የጎሳ በመሆናቸው ትብብር እና አንድነት ስላላቸው ጠንካራ ናቸው። ሁከት እና ችግር ስለሚያጎለብታቸው እየጠነከሩም እየሄዱ ነው።

በዚህ ሁኔታ የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ዋና ስራ መደራጀት እንደሆነ ግልጽ ነው። የህልውና ጉዳይ ነው። የዜግነት ፖለቲካችንን ካላራመድን እና ግዙፍ ድርጅቶች ካልፈጠርን እኛም ሀገራችንም እንጠፋለን። ጠ/ሚ አቢይ ቢፈልግም ይህን ሊያደርግልን አይችልም። እኛ የራሳችንን ድርሻ ካልሰራን እሱም አቅም ያጣል። ለነገሩ እስከ ዛሬም ሀገራችን ላሳለፈችው ችግር ዋና ምክንያት የኛ በሚገባው አለመደራጀት ነው።

በዚህ ሁኔታ፤ ደካማ ሆነን፤ ዋና ስራችን እራሳችንን ማጎልበት እና ማደራጀት በሆነበት ጊዜ ጠላቶች ማፍራት ጅልነት ነው። አሁን ሁሉንም የማቀፍ ጊዜ ነው። የጊዜ መግዥያ ጊዜ ነው። ጠ/ሚ አቢይ፤ የጎሳ ብሄርተኞች፤ ህወሓት ወዘተ ሁሉንም ተጠንቅቀን ይዘን ወዳጅ መስለን መገኘት አለብን። የመደራጀት ስራችንን መስራት ነው ያለብን። ብልህ ፖለቲካ ማለት ይህ ነው።

ለምሳሌ የአዲስ አበባ ሲቪክ ድርጅት ለማቋቋም ሲጀመር ስለ ከንቲባው አለማንሳት። ወይንም ማሞገስ። ጽሁፍ እና ፖስተሮች በአማርኛ ብቻ ሳይሆን በኦሮምኛም ማዘጋጀት። አዲስ አበባ ለአዲስ አበቤዎች አይነት መፈክር ትቶ በቀላሉ «ለአዲስ አበባ ነዋሪ ሁሉ መብት ማስከበር» ነው ተልዕኯችን ማለት ነው! ወዘተ። ሀሳቡ ግልጽ ይመስለኛል።

ግን ይህን ከማረግ ፋንታ እንደ ቆቛ እንጮሃለን! ምንም ሳይኖረን አፍ ብቻ እንሆናለን። ባለን ጊዜ አንዴ ከጎሳ ብሄርተኞች ጋር አሁን ደግሞ አንዳንዶቻችን ከጠ/ሚ አቢይ ጋር ግብ ግብ እንገባለን። ገና ለመታገል አቅም ሳይኖረን ጠላቶች እናፈራለን። ይህን ማቆም አለበን፤ የህልውና ጉዳይ ነው። የ50 ዓመት የፋራ ፖለቲካችንን ማቆም ካላቆምን ሌላ እድል የሚኖረን አይመስለኝም።

አካሄዳችን መሆን ያለበት መጀመርያ ኃይልን መሰብሰብ። ይህን ለማድረግ ባይጥመንም የሚያስፈልገውን ነገር ማድረግ። ከሁሉም ጋር አብሮ መስራት ያስፈልጋል። እራስን አለማጋለጥ ያስፈልጋል። ኃይልን ከሰበሰብን በኋላ ደፈር ያሉ አቋሞች መያዝ እና ስራዎች መስራት።

በመጨረሻ ማለት የምፈልገው... ምን አልባት በመጮህ፤ መተቸት እና በመውቀስ ህዝባችን እንዲማረር እና እንዲቆጣ አድርገን በቀላሉ ይደራጃል ብለን እናስብ ይሆናል? ለዚህ ይሆን ብዙዎቻችን ዋናው የመደራጀቱን ስራ ትተን 100% ጊዜአችንን በመተቸት እና መወንጀል የምናጠፋው?

ይህ ከሆነ በጣም የተሳሳተ አስተሳሰብ ነው። አካሄድ ውድቅ እንደሆነ የ27 ዓመት ማስረጃ አለን! ለ27 ዓመት ህወሓት እና የጎሳ ብሄርተኞች ሲረግጡን ያሁሉ ሚሊዮን ህዝብ ሆነን አንዳች ግዙፍ ድርጅት ማቋቋም አልቻልንም። የወሬ፤ ጩሀት እና ትችት ፖለቲካ አልሰራም።

ህወሓት ከስልጣን የወረደው እነ ኢሳት ህዝቡ ሀውሓትን እንዲጠላ ስላደረጉ አይደለም። ህዝቡ በለቱ ኑሮ አይቷቸው ጠልቷቸዋልና! አልፎ ተርፎኦ ይህ ጸረ-ህወሓት ዘመቻ ምንም አይነት ጠንካራ ድርጅት አልፈጠረም። ያሁሉ ዓመታት ጩሀት በኋላ የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ትንሿ ግንቦት 7ን ብቻ ነው ያፈራነው።

ስለዚህ የጩሀት ፖለቲካ አይሰራም። ህዝቡን በፕሮፓጋንዳ አማርሮ ማደራጀት እንደማይቻል አይተናል። ህዝቡ በእውን በኑሮው ተማርሯል። የፖለቲከኞች ስራ ይበልጥ ተማረሩልኝ ማለት ሳይሆን ማደራጀት እና ለምሬቱ ትክክለኛ መስመር ማብጀት ነው። የኛ የኢትዮጵያ ብሄርተኞች የፖለቲካ ልሂቃን ይህን ማድረግ አልቻልንም። እስቲ አሁን እንሞክር።

Disarmed! አለች ርዕዮት ዓለሙ

በዛሬ እለታዊ ፕሮግራም የርዕዮት ዓለም አስተያየትን (https://www.youtube.com/watch?v=b1OuvNmwxeY) በተመለከተ...

ነጥቧ ከሞላ ጎደል እንዲህ ነው፤ እነ «ቲም ለማ» ከመጀመርያዉኑ በጭፍን አምነን መከተል («መደገፍ») አልነበረብንም። ለ«ዴሞክራሲ» መታገል መቀጠል ነበረብን እና እነ «ቲም ለማ» እውነትም ዴሞክራቶች ቢሆኑ መሃል መንገድ እንገናኛለን ነው። ዛሬ እነ ጠ/ሚ አብይ አድሎ እያሳዩ እየሆነ የፈራሁት ሁኔታ እየተከሰተ ነው ግን አሁን እኛ ለዴሞክራሲ የምንታገለው ቡድን እራሳችንን "disarm" አድርገናል። በተወሰነ ደረጃ "its' too late" ነው የምትለው።

ምን መሳርያ ኖሮን ነው "disarm" ያረግነው ነው ጥያቄው! እኛ ኢትዮጵያ ብሄርተኞች ከሁሉም ፖለቲካ ኃይሎች የመጨረሻ ደካማ ነበርን ዓመት በፊት ዛሬም እንዲሁ። ምንም "disarm" አላረግንም። ነው ግንቦት 7 ሀገር መግባት አልነበረበትም ወይንም ጥጥቁን መፍታት አልነበረበትም ነው? ዓመት በፊት በኦሮሚያ የነበረው ሁኔታ ይታወቃል። በኦህዴድ ያለው ሁኔታ ይታወቃል። «ጠባቦች» በርካታ ነበሩ አሁንም ናቸው። እንደ አብይ በነሱ ላይም ከነሱ ጋርም ነው የመንግስት ግልበጣ ያደረጉት። እኛ የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ኢሚንት ነው ያደረግነው።

ታድያ ዛሬ ጠ/ሚ አቢይ ፈልገውም ባይፈልጉም ኦሮሞ ብሄርተኞቹን ወድያው መቆጣጠር ባይችሉ ምን ይገርማል። የኢትዮጵያ ብሄርተኛው ቡድን ለ50 ዓመት መደራጀት ያልቻለው ዛሬም ስላልቻለ ነው ይህ የሚከሰተው። የአዲስ አበባ ህዝብ ገና ድሮ ቢደራጅ ኖር (ዋጋውን ከፍሎ) ይህ ሁሉ አይሆንም ነበር። ዛሬም ባለፉት ስድስት ወራት መደራጀት ይችል ነበር። አሁንም ይችላል። ላለመቻሉ እነ ጠ/ሚ አቢይን መውቀስ ተገቢ አይደለም። በፍፁም ተገቢ አይደለም። እንደልማዳችን የራሳችንን ችግር ሌላ ላይ እየለጠፍን ነው።

እኛ መጀመርያ ተደራጅተን ታክቲካል አላያንስ ከነ ጠ/ሚ አቢይ ጋር መፍጠር ነው። አሁን ላለውን ችግር እሱ ላይ ከመለጠፍ ፋንታ ስራችንን ሰርተን ብልህ ፖለቲከኞች ሆነን እራሳችንን አጎልብትን መገኘት ነው። ሀውሓት ያደረገው፤ ኦሮሞ ብሄርተኞች ያደረጉትን እኛ ሊያቅተን አይገባም።

ይቅርታ አድርጉልኝ ግን የኛ የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ፖለቲካ በመደራጀት ብቻ ሳይሆን በስልትም እጅግ ደካማ ይመስለኛል። የህዝብ/ብዙሃን ቁጥር አለን ግን ድርጅት የለንም። ስለዚህም አቅመ-ቢስ ነን። ልሰዚህ ይህ ጊዜ የማጎልበት ነው እንጂ የጠላት መፍጠር አይደለም!! እነ ጠ/ሚ አቢይን ጓደኛ አድርጎ፤ የጎሳ ብሄርተኞችን ዝም ብሎ፤ ወሬ ሳናበዛ ለመደራጀት እና ለመጎልበት እራሳችንን ጊዜ መስጠት አለብን። ይህ ነው ብቸኛ አማራጭ።