Friday 19 October 2018

Disarmed! አለች ርዕዮት ዓለሙ

በዛሬ እለታዊ ፕሮግራም የርዕዮት ዓለም አስተያየትን (https://www.youtube.com/watch?v=b1OuvNmwxeY) በተመለከተ...

ነጥቧ ከሞላ ጎደል እንዲህ ነው፤ እነ «ቲም ለማ» ከመጀመርያዉኑ በጭፍን አምነን መከተል («መደገፍ») አልነበረብንም። ለ«ዴሞክራሲ» መታገል መቀጠል ነበረብን እና እነ «ቲም ለማ» እውነትም ዴሞክራቶች ቢሆኑ መሃል መንገድ እንገናኛለን ነው። ዛሬ እነ ጠ/ሚ አብይ አድሎ እያሳዩ እየሆነ የፈራሁት ሁኔታ እየተከሰተ ነው ግን አሁን እኛ ለዴሞክራሲ የምንታገለው ቡድን እራሳችንን "disarm" አድርገናል። በተወሰነ ደረጃ "its' too late" ነው የምትለው።

ምን መሳርያ ኖሮን ነው "disarm" ያረግነው ነው ጥያቄው! እኛ ኢትዮጵያ ብሄርተኞች ከሁሉም ፖለቲካ ኃይሎች የመጨረሻ ደካማ ነበርን ዓመት በፊት ዛሬም እንዲሁ። ምንም "disarm" አላረግንም። ነው ግንቦት 7 ሀገር መግባት አልነበረበትም ወይንም ጥጥቁን መፍታት አልነበረበትም ነው? ዓመት በፊት በኦሮሚያ የነበረው ሁኔታ ይታወቃል። በኦህዴድ ያለው ሁኔታ ይታወቃል። «ጠባቦች» በርካታ ነበሩ አሁንም ናቸው። እንደ አብይ በነሱ ላይም ከነሱ ጋርም ነው የመንግስት ግልበጣ ያደረጉት። እኛ የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ኢሚንት ነው ያደረግነው።

ታድያ ዛሬ ጠ/ሚ አቢይ ፈልገውም ባይፈልጉም ኦሮሞ ብሄርተኞቹን ወድያው መቆጣጠር ባይችሉ ምን ይገርማል። የኢትዮጵያ ብሄርተኛው ቡድን ለ50 ዓመት መደራጀት ያልቻለው ዛሬም ስላልቻለ ነው ይህ የሚከሰተው። የአዲስ አበባ ህዝብ ገና ድሮ ቢደራጅ ኖር (ዋጋውን ከፍሎ) ይህ ሁሉ አይሆንም ነበር። ዛሬም ባለፉት ስድስት ወራት መደራጀት ይችል ነበር። አሁንም ይችላል። ላለመቻሉ እነ ጠ/ሚ አቢይን መውቀስ ተገቢ አይደለም። በፍፁም ተገቢ አይደለም። እንደልማዳችን የራሳችንን ችግር ሌላ ላይ እየለጠፍን ነው።

እኛ መጀመርያ ተደራጅተን ታክቲካል አላያንስ ከነ ጠ/ሚ አቢይ ጋር መፍጠር ነው። አሁን ላለውን ችግር እሱ ላይ ከመለጠፍ ፋንታ ስራችንን ሰርተን ብልህ ፖለቲከኞች ሆነን እራሳችንን አጎልብትን መገኘት ነው። ሀውሓት ያደረገው፤ ኦሮሞ ብሄርተኞች ያደረጉትን እኛ ሊያቅተን አይገባም።

ይቅርታ አድርጉልኝ ግን የኛ የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ፖለቲካ በመደራጀት ብቻ ሳይሆን በስልትም እጅግ ደካማ ይመስለኛል። የህዝብ/ብዙሃን ቁጥር አለን ግን ድርጅት የለንም። ስለዚህም አቅመ-ቢስ ነን። ልሰዚህ ይህ ጊዜ የማጎልበት ነው እንጂ የጠላት መፍጠር አይደለም!! እነ ጠ/ሚ አቢይን ጓደኛ አድርጎ፤ የጎሳ ብሄርተኞችን ዝም ብሎ፤ ወሬ ሳናበዛ ለመደራጀት እና ለመጎልበት እራሳችንን ጊዜ መስጠት አለብን። ይህ ነው ብቸኛ አማራጭ።

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!