በዚህ ዘመን የቃላቶች ትርጉም ተተንቅቀን ነጣጥለን ማየት አለብን።
እስቲ በመጀመርያ «መቻቻል» ምን ማለት እንደሆነ እንመርምር። ሰው የሚወድውን ነገር «ቻለው» ይባላል? አይባልም! የማይወደውን ግን በተለያዩ ምክንያቶች ስለነገሩ ምንም ማድረግ የማይችለውን ወይም ማድረግ የማይፈልገውን ነገር ነው «ቻለው» የሚባለው።
ለምሳሌ… ሙስሊም ጎረቤቴ በየጊዜው ድምጽ የበዛው የጸሎት ዝግጅት ያካሄዳል ከበቱ። ጩኸቱን አልወደውም ግን ለሰላም ብዬ ዝም እላለሁ። ይህ የመቻቻል አንድ ምሳሌ ነው።
እዚ ጋር አንድ ነገርን ልብ እንበል። ጎረቤቴን ዝም ያልኩት ስለምወደው ወይም ጥሩ ልሁንለት ብዬ አይደለም። «ነግ በኔን» አስቤ ነው። ለራሴ ጥቅም ብዬ ነው። እኔም ዝግጅቶችህን ተው ብዬ አላስቸግረውም እሱም እኔ እንደዚሁ አይነት ፕሮግራም ባዘጋጅ ዝም ይለኛል። አልፎ ተርፎ ጸብ ስለሌለን ግንኙነታችን ሰላማዊ ስለሆነ ወደ ፊት በተለያዩ የሚጠቁሙን ጉዳዮች መተባበር መረዳዳት ቀላል ሊሆን ይችላል።
ስለዚህ «መቻቻል» የአብሮ መኖር ስልት ነው። የጥሩነት ወይም በጎ መግባር ውጤት አይደለም የመዋደድ የፍቅርም ውጤት አይደለም።
መቻቻል እንዲህ ከሆነ ለኛ ኦርቶዶክስ ክርስትያኖች ምን ማለት ነው? መቻቻል አለብን ወይ? የሌላ ሃይማኖት ተከታዮችን «መቻል» አለብን ወይ? «የሃይማኖት መቻቻልን» መተግበር አለብን ወይ? በፍፁም! በመጀመርያ እንደ ክርስትናችን «መውደድ» ነው ያለብን። አምላካችን እንዳለን እሱ እንደሚወደን ያህል ባለንጀራችንን መውደድ አለብን። የኛ የክርስትያኖች ተዕልኮ «ፍቅር» ነው እንጂ «መቻቻል» አይደለም! ማንም ሰው ከልምድና ምቾት አንጻር መቻቻል ይችላል፤ ግን ክርስትያኖች መውደድ ነው ያለብን።
ወደ ቅድሙ ምሳሌአችን ከተመለሰን የሙስሊም ጎረቤቴን ስለ ጸሎት ዝግጅቶቹ የማላስቸግረው ምክንያት «መቻቻል» ሳይሆን «ፍቅር» ነው መሆን ያለበት። ስለ ዝግጅቱ ካላማረርኩኝ አለማማረሬ ከፍቅር የመነጨ መሆን አለበት እንጂ ለራሴ ጥቅም ብዬ መሆን የለበትም። እሱም ይሉኝታ ኖሮት ዝም ይለንኛል ብዬ ከሱ ጠብቄ ሳይሆን ምንም ሳልጠብቅ ምሆን አለበት። ስለዚህ ክርስትያኖች መቻቻልን መተግበር አለባቸው ማለት ትርጉም የለውም። ከመቻቻል በላይ ሰማይ ጠቀሱን ፍቅር መተግበር ነው ያለን።
እንግዲህ አንዳንዶቻችሁ «አምላካችሁ ውደዱ ቢላችሁም አትሰሙትም» ትሉኝ ይሆናል። «እናንተ ኦርቶዶክስ ክርስትያኖች ድሮም አሁንም ፍቅርን አታውቁም።» አልክድም፤ እውነት ነው፤ እኔ ኦርቶዶክስ ክርስትያን ብሆንም ኃጢአተኛ ነኝ ፍቅር ይጎለኛል። ፍቅር የሆነውን ተልዕኮኤን ሁል ጊዜ እየሳትኩኝ ነው የምኖረው። ይህ ኃጢአተኝነቴ ግን የሚስተካከለው ወይንም በትክክሉ ቋንቋ የሚታከመው መቻቻልን መተግበር በመሞከር አይደለም። ፍቅርን በመተግበር ነው። ካልቻልኩኝ ከወደቅኩኝ ተመልሼ መሞከር መነሳት ነው። ይህ ነው የክርስትና ኑሮ። እንጂ መውደድ አልችልም ብዬ ተስፋ ቆርቼ እስቲ መቻቻልን ልሞርክ ማለት ውድቅ ሀሳብ ነው።
ስለዚህ ፕሮቴስታንት ወንድሜ፤ ሙስሊም እህቴ፤ ሴኩላሪስት ወንድሜ፤ ካስቀየምኩህ ካስቸገርኩህ ከጎዳሁህ እኔን ኃጢአተኛውን ይቅር በለኝ። መሻሻል እሞክራለሁ። ልችልህ ሳይሆን በእግዚአብሔር እርዳታ ልወድህ እሞክራለሁ።
የሰላም ክፍሌ ይትባረክ ብሎግ፤ ስለ ሀገራችን ኢትዮጵያ ያለኝን ትናንሽ ሀሳቦች በትህትና አቀርባለሁ። ለስሕተቶቼም በቅድሚያ ይቅርታ እጠይቃለሁ
Showing posts with label ኦርቶዶክስ ክርስቲያን. Show all posts
Showing posts with label ኦርቶዶክስ ክርስቲያን. Show all posts
Tuesday, 3 April 2018
Wednesday, 21 March 2018
«ሴኩላሪዝም»
ትንሽ አመታት በፊት አንድ የመንግስት ስራተኛ የሆነ ዘመዴ የኦርቶዶክስ መዝሙር ከመስሪያቤት ኮምፕዩተሩ ላይ ማዳመጥ ክልክል እንደተደረገ ነገረኝ። ለምን ብዬ ስጠይቀው ክርስትያኑም ሙስሊሙም የሚፈልገውን መዝሙር፤ ስብከት፤ ትምሕርት እያዳመጠ እና ኮምፕዩተሩ ላይ ሥዕል እየለጠፈ የሰራተኞች እርስ በርስ ግጭት ሊፈጥር ይችላል ተብሎ ተከለከለ አለኝ። የሚገርመው ነገር ግን 1) ከመስሪያቤቱ እንደዚህ አይነት ግጭቶች አልነበሩም እና 2) ክልከላው በተራ ትዛዝ ሳይሆን ከከፍ ያለ የአስተዳደር ደረጃ በመመርያ ምልክ የተላለፈ ነበር። የመመርያው ርዕስ ደግሞ «ሴኩላሪዝም» ነበር።
ይህን ታሪክ ስሰማ እጅግ አዘንኩኝ። መቼ ነው መንግስቶቻችን፤ ምሁሮቻችን እና ልሂቆቻችን የምዕራብ ዓለም ርዕዮት ዓለምና ፍልስፍና ይዘው አገራችን ላይ መጫን የሚያቆሙት? ካለፉት የ100 ዓመታት ታሪካችን አይማሩምን?
እስቲ «ሴኩላሪዝም» ባጭሩ ምን እንደሆነ እንመልከት። «ሴኩላሪዝም በዓለማችን እግዚአብሔር የለም/አይሳተፍም ብሎ ማሰብ ነው»። ሴኩላሪዝም እግዚህብሔር ሊኖር ላይኖርም ይችላል ግን ከዓለማችን ከሕይወታችን ከለት ኑሮአችንም አይሳተፍም የሚለው አመለካከት ነው። እግዚአብሔር ካለ እዛው ከዙፋኑ ወይንም ገነቱ ተቀምጦ ይመለከተናል። በሃይማኖት እና በእግዚአብሔር በግል ምርጫችን ልናምንባቸው የምንችል የእምነት ሥርዓቶች ናቸው። በሀሳብ ደረጃ ነው የምናምንባቸው ካላሰኘን ደግሞ ከሀሳባችን እናስወግዳቸዋለን!
ይህ አስተሳሰብ በተለያየ መንገድ ወደ ክርስትያን የሆነውን አስተሳሰብ ገብቷል። «ዓለማዊ» እና «መንፋሳዊ» የምንላቸው ቃላት በተሳሳተ መንገድ እንጠቀማለን። ዓለማዊ ስንል ስራችን፤ ትምሕርታችን፤ ገበያችን፤ ንግዳችን ወዘተ ነው። እግዚአብሔር እነዚ ነገሮች ውስጥ እንዳለ አናምንም። ስለዚህም ነው በነዚህ የህይወት ዘርፎቻችን ኢ-ክርስትያናዊ ነገሮች እያደረግን እያለን አማኞች ነን የምንለው። እሁድ እሁድ ግን ቤተ ክርስትያን ሄደን ወደ መንፈሳዊስ ዓለም እንሸጋገራለን። እዛ ጨዋ ነን፤ ጥሩ ስነ መግባር አለን፤ ጭንቀቶቻችንን አስተንፍሰን ወደ ዓለማችን እንመለሳለን።
ይህ ግን የውሸት ክርስትና ነው። በእምነታችን እግዚአብሔር በሁሉም ቦታ በሁሉም ነገር አለ። «እኔ የቅርብ አምላክ ነኝ እንጂ የሩቅ አምላክ አይደለሁም። ሰው በስውር ቢሸሸግ፥ እኔ አላየውምን? ሰማይንና ምድርንስ የሞላሁ እኔ አይደለሁምን? ይላል እግዚአብሔር።» ኤር 23:23-24።
ስለዚህ ትምሕርት ቤት ብሄድ፤ መስሪያ ቦታ ብሄድ፤ እርሻዬ ላይ ብሆን፤ ትራንስፖርት ላይ ብሆን፤ መጠጥ ቤት ብሄድ፤ በሁሉም ቦታ እግዚአብሔር አለ። ሕይወታችንን እግዚአብሔር ያለበትና የሌለበት ብለን ልንከፋፍለው አንችልም። በሁሉም ቦታ በሁሉ ደቂቃ ከኛ ጋር ነውና።
ይህ የሚያሳየን የሰው ልጅ ክርስትያንም ሴኩላሪስትም አብሮ ሊሆን አይችልም። ብዙዎቻችን ወደዚህ ስህተት ብንገባም ሊሆን የማይችል ነገር ነው። ለክርስትያኖች እግዚአብሔር ልኬት የለውምና። በተጨማሪ ሴኩላሪዝም እግዚአብሔርን ከለት ኑሮአችን ማጥፋት ስለሚፈልግ የክርስትና ተቃራኒ ብቻ ሳይሆን ጠላት እንደሆነ ግልጽ ነው።
«እናንተ ኦርቶዶክሶች፤ ሙስሊሞች፤ ፕሮቴስታንቶች አብሮ መኖር አትችሉም። ስለዚህም (እግዚአብሔራን ተክቼ!) ከላያችሁ ሆኜ አስተዳድራችኋለሁ» ይላል ሴኩላሪዝም / ሴኩላሪስቱ። «እኔ ነኝ ስልጡኑ፤ ከማንም ጋር የማልጋጨው፤ ከሁሉም ጋር የምግባባው፤ ሁሉንም የማከብረው» ይላል። እውነቱ ግን ሴኩላሪስቱ እንደዚህ ሲል ሁሉንም በሰላም ለመጠበቅ ሳይሆን አላማው ይህን አስመስሎ «እግዚአብሔር የለም» የሚባለውን ሃይማኖትን ለማስፋፋት ነው። እግዚአብሔር ከአዕምሮአችን ብቻ ነው ያለው እንጂ ከስራ ቦታችን፤ ገበያ ቦታችን፤ መንገዶቻችን፤ ሚዲያዎቻችን፤ ከለት ኑሮአችን የለም ብለን ካመንን ቀጥሎ እግዚአብሔር የትም የለም ማለት የሚቀጥለው ቀላል እርምጃ ነውና!
በተጨማሪ እግዚአብሔር ከለት ኑሮአችን ከሌለ የማህበረሰብ የአገራችን ድንጋጌዎች ከየት ሊመጡ ነው? ከሴኩላሪዝም ርዕዮት ዓለም ከ«እግዚአብሔር የለም» ሃይማኖት ሊመጡ ነው! አያችሁ ሴኩላሪዝም እራሱን ገለልተኛ አድርጎ እንዴት «እግዚአብሔር የለም» ሃይማኖትን ሰተት ብሎ እንደሚያሰፍን።
ኢትዮጵያ የሃይማኖት አገር ናት። ታሪካችን ትውፊታችን ከዚህ የተያያዘ ነው። ማንነታችን ይህ ነው። ሴኩላሪዝም ደግሞ የህን አፍርሶ «እግዚአብሔር የለም» ሃይማኖትን ነው ማስፈን የሚፈልገው። ይህ ሂደት እንዴት እንደሚሰራ ለማወቅ የምዕራብ ዓለሙን ያለፈውን 400 መቶ ዓመት ታሪክ መመልከት ነው። ስለዚህ ሴኩላሪዝም ኢ-ኢትይጵያዊ እንደሆነ ተረድተን ወደ አገራችን ሰተት ብሎ እንዳይገባ መጠንቀቅ አለብን። በተለይ ደግሞ ወደ ልባችን ሰተት ብሎ እንዳይገባ መጠንቀቅ አለብን።
ይህን ታሪክ ስሰማ እጅግ አዘንኩኝ። መቼ ነው መንግስቶቻችን፤ ምሁሮቻችን እና ልሂቆቻችን የምዕራብ ዓለም ርዕዮት ዓለምና ፍልስፍና ይዘው አገራችን ላይ መጫን የሚያቆሙት? ካለፉት የ100 ዓመታት ታሪካችን አይማሩምን?
እስቲ «ሴኩላሪዝም» ባጭሩ ምን እንደሆነ እንመልከት። «ሴኩላሪዝም በዓለማችን እግዚአብሔር የለም/አይሳተፍም ብሎ ማሰብ ነው»። ሴኩላሪዝም እግዚህብሔር ሊኖር ላይኖርም ይችላል ግን ከዓለማችን ከሕይወታችን ከለት ኑሮአችንም አይሳተፍም የሚለው አመለካከት ነው። እግዚአብሔር ካለ እዛው ከዙፋኑ ወይንም ገነቱ ተቀምጦ ይመለከተናል። በሃይማኖት እና በእግዚአብሔር በግል ምርጫችን ልናምንባቸው የምንችል የእምነት ሥርዓቶች ናቸው። በሀሳብ ደረጃ ነው የምናምንባቸው ካላሰኘን ደግሞ ከሀሳባችን እናስወግዳቸዋለን!
ይህ አስተሳሰብ በተለያየ መንገድ ወደ ክርስትያን የሆነውን አስተሳሰብ ገብቷል። «ዓለማዊ» እና «መንፋሳዊ» የምንላቸው ቃላት በተሳሳተ መንገድ እንጠቀማለን። ዓለማዊ ስንል ስራችን፤ ትምሕርታችን፤ ገበያችን፤ ንግዳችን ወዘተ ነው። እግዚአብሔር እነዚ ነገሮች ውስጥ እንዳለ አናምንም። ስለዚህም ነው በነዚህ የህይወት ዘርፎቻችን ኢ-ክርስትያናዊ ነገሮች እያደረግን እያለን አማኞች ነን የምንለው። እሁድ እሁድ ግን ቤተ ክርስትያን ሄደን ወደ መንፈሳዊስ ዓለም እንሸጋገራለን። እዛ ጨዋ ነን፤ ጥሩ ስነ መግባር አለን፤ ጭንቀቶቻችንን አስተንፍሰን ወደ ዓለማችን እንመለሳለን።
ይህ ግን የውሸት ክርስትና ነው። በእምነታችን እግዚአብሔር በሁሉም ቦታ በሁሉም ነገር አለ። «እኔ የቅርብ አምላክ ነኝ እንጂ የሩቅ አምላክ አይደለሁም። ሰው በስውር ቢሸሸግ፥ እኔ አላየውምን? ሰማይንና ምድርንስ የሞላሁ እኔ አይደለሁምን? ይላል እግዚአብሔር።» ኤር 23:23-24።
ስለዚህ ትምሕርት ቤት ብሄድ፤ መስሪያ ቦታ ብሄድ፤ እርሻዬ ላይ ብሆን፤ ትራንስፖርት ላይ ብሆን፤ መጠጥ ቤት ብሄድ፤ በሁሉም ቦታ እግዚአብሔር አለ። ሕይወታችንን እግዚአብሔር ያለበትና የሌለበት ብለን ልንከፋፍለው አንችልም። በሁሉም ቦታ በሁሉ ደቂቃ ከኛ ጋር ነውና።
ይህ የሚያሳየን የሰው ልጅ ክርስትያንም ሴኩላሪስትም አብሮ ሊሆን አይችልም። ብዙዎቻችን ወደዚህ ስህተት ብንገባም ሊሆን የማይችል ነገር ነው። ለክርስትያኖች እግዚአብሔር ልኬት የለውምና። በተጨማሪ ሴኩላሪዝም እግዚአብሔርን ከለት ኑሮአችን ማጥፋት ስለሚፈልግ የክርስትና ተቃራኒ ብቻ ሳይሆን ጠላት እንደሆነ ግልጽ ነው።
«እናንተ ኦርቶዶክሶች፤ ሙስሊሞች፤ ፕሮቴስታንቶች አብሮ መኖር አትችሉም። ስለዚህም (እግዚአብሔራን ተክቼ!) ከላያችሁ ሆኜ አስተዳድራችኋለሁ» ይላል ሴኩላሪዝም / ሴኩላሪስቱ። «እኔ ነኝ ስልጡኑ፤ ከማንም ጋር የማልጋጨው፤ ከሁሉም ጋር የምግባባው፤ ሁሉንም የማከብረው» ይላል። እውነቱ ግን ሴኩላሪስቱ እንደዚህ ሲል ሁሉንም በሰላም ለመጠበቅ ሳይሆን አላማው ይህን አስመስሎ «እግዚአብሔር የለም» የሚባለውን ሃይማኖትን ለማስፋፋት ነው። እግዚአብሔር ከአዕምሮአችን ብቻ ነው ያለው እንጂ ከስራ ቦታችን፤ ገበያ ቦታችን፤ መንገዶቻችን፤ ሚዲያዎቻችን፤ ከለት ኑሮአችን የለም ብለን ካመንን ቀጥሎ እግዚአብሔር የትም የለም ማለት የሚቀጥለው ቀላል እርምጃ ነውና!
በተጨማሪ እግዚአብሔር ከለት ኑሮአችን ከሌለ የማህበረሰብ የአገራችን ድንጋጌዎች ከየት ሊመጡ ነው? ከሴኩላሪዝም ርዕዮት ዓለም ከ«እግዚአብሔር የለም» ሃይማኖት ሊመጡ ነው! አያችሁ ሴኩላሪዝም እራሱን ገለልተኛ አድርጎ እንዴት «እግዚአብሔር የለም» ሃይማኖትን ሰተት ብሎ እንደሚያሰፍን።
ኢትዮጵያ የሃይማኖት አገር ናት። ታሪካችን ትውፊታችን ከዚህ የተያያዘ ነው። ማንነታችን ይህ ነው። ሴኩላሪዝም ደግሞ የህን አፍርሶ «እግዚአብሔር የለም» ሃይማኖትን ነው ማስፈን የሚፈልገው። ይህ ሂደት እንዴት እንደሚሰራ ለማወቅ የምዕራብ ዓለሙን ያለፈውን 400 መቶ ዓመት ታሪክ መመልከት ነው። ስለዚህ ሴኩላሪዝም ኢ-ኢትይጵያዊ እንደሆነ ተረድተን ወደ አገራችን ሰተት ብሎ እንዳይገባ መጠንቀቅ አለብን። በተለይ ደግሞ ወደ ልባችን ሰተት ብሎ እንዳይገባ መጠንቀቅ አለብን።
Friday, 16 March 2018
ስለ ትህትና
እግዚአብሔር ክፉ መናፍስትን የማስወጣት ጸጋ የሰጣቸው አንድ ባሕታዊ ነበሩ። በአንድ ወቅት ጋኔኖቹን የሚያስፈራቸውና ከሰዎች እንዲለቁ የሚያደርጋቸው ምን እንደሆነ ለመረዳት ፈልገው ጠየቁ።
«ጾም ይሆን?» ብለው አንዱን ጠየቁት።
«እኛ መቼም አንበላም አንጠጣምም» ብሎ ክፉ መንፈሱ መለሰላቸው።
«የለሊት ሙሉ ጸሎት ይሆን?»
«እኛ አንተኛ።»
«ዓለምን ትቶ መመንን?»
«ይህ እንደ ትልቅ ነገር ይቆጠራል። ግን እኛ አብዛኛው ጊዜአችንን በየ በርሃው እየዞርን ነው የምናጠፋው።»
«ታድያ ምንድነው ይዞ ሊቆጣጠራችሁ የሚችለው፤ እባካችሁ ንገሩኝ» ብለው ታላቁ አባት ደግመው ጠየቁ።
ክፉ መንፈሱ በተአምራዊ ኃይል ጥያቄውን እንዲመልስ ተገደደ፤ «ትህትና ነው። ይህን መቼም ልናሸንፍ አንችልምና።»
«ጾም ይሆን?» ብለው አንዱን ጠየቁት።
«እኛ መቼም አንበላም አንጠጣምም» ብሎ ክፉ መንፈሱ መለሰላቸው።
«የለሊት ሙሉ ጸሎት ይሆን?»
«እኛ አንተኛ።»
«ዓለምን ትቶ መመንን?»
«ይህ እንደ ትልቅ ነገር ይቆጠራል። ግን እኛ አብዛኛው ጊዜአችንን በየ በርሃው እየዞርን ነው የምናጠፋው።»
«ታድያ ምንድነው ይዞ ሊቆጣጠራችሁ የሚችለው፤ እባካችሁ ንገሩኝ» ብለው ታላቁ አባት ደግመው ጠየቁ።
ክፉ መንፈሱ በተአምራዊ ኃይል ጥያቄውን እንዲመልስ ተገደደ፤ «ትህትና ነው። ይህን መቼም ልናሸንፍ አንችልምና።»
ቤተክርስቲያን የፈውስ ቦታ ናት
«ወደ ቤተክርስቲያን ግባ እና ከኃጢአትህ ታጠብ። ቤተክርስቲያን የፈውስ ቦታ እንጂ የዳኛ ፍርድ ቤት አይደለችም እና። ወደ ቤተክርስቲያን በመግባትህ አትፈር። ኃጢአት ሰርተህ ንሰሐ ባለመግባትህ ግን እፈር።»
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
Friday, 2 March 2018
የምዕራባዊያን አገራት አምልኮ
የአባቴ ትውልድ የምዕራባዊያን አገሮችን የሚተቹባቸው በርካታ ጉዳዮች ነበሩ። ዘረኛ ናቸው። ታላቂቷ ምዕራባዊ አገር አሜሪካ አሁንም በጥቁር ዜጎቿ ታላቅ ግፍ እያደረሰችባቸው ነው። ዓለምን በቅኝ ግዛት አሰቃይተዋል። ቅኝ ግዛታቸውን እየተውዉ ቢሆንም አሁንም በ«አዲሱ ቅኝ ግዛት» መርህ ዘንድ ጥቅማቸውን የማያስከብሩ መንግስታትን በመፈንቀለ መንግስትና የተለያዩ ዘዴዎች ያፈርሳሉ።
የአሁኑ ትውልድ ደግሞ የምዕራባዊያን አገሮችን እንደ ጣዖት የሚያመልክ ይመስላል። ነፃነት ከነሱ ጎራ ነው የሚገኘው። ተራማጅነት ከነሱ ነው። ሀብት ከነሱ። ዴሞክራሲ ከነሱ። ቴክኖሎጂ ከነሱ። ስነ መግባር ከነሱ። ወዘተ።
በኔ ኢይታ ይህ አምልኮ ለአገራችን ለያንዳንዳችንም አደገኛ ነው። ለምን ብትሉኝ ይህ አመለካከት ከባህላችን፤ ትውፊታችን፤ ማንነታችን ነጥቆ እንደ ስሩ የተነቀለ አትክልት ነው የሚያደርገን።
ስለዚህም ቢዚህ ርእስ ዙርያ የተወሰኑ ጽሁፎች ለማዘጋጀት አቅጅያለሁ። የኢትዮጵያዊነት፤ የሰውነት፤ የማንነት ጉዳይ የተሳሰረበት ርእስ ነው። የምዕራባዊው ፕሮፓጋንዳ እጅግ ከባድ ነው። በመሰረታዊ አስተሳሰባችንን፤ አስተያየታችንን፤ አስተነፋፈሳችንንም ታላቅ ሚና ተጫውቷል። መሰራታዊ ሃሳቦቻችንና ቋንቋችንም ቀይሯል መቀየሩንም አናውቀውም! ይህ ሁሉ በደምብ ልናየው ይገባል።
ጽሁፎቼን ስጽፍ በተለምዶ በመጀመርያ እንደ ክርስቲያን በማቀው ክርስቲያናዊ አመለካከት ነው የምጽፋቸው። እምነቴ በሁሉ ነገር ኢግዚአብሔር አለ ብሎ ሰለሚያስተምር እንቋን የማንነት ጉዳይ ምንም ነገር ከዚህ መነጽር ውጭ ማየት አይቻልም።
ለጽሁፎቼ እንደ መግብያና ሀሳብ ማንሸራሸርያ እስቲ እነዚህን ቃላቶችን እናስባቸው፤
ዘመናዊነት (modernity)
መሻሻል ወይም እድገት (progress)
ዴሞክራሲ (democracy)
ነፃነት (freedom)
ሰው (Man)
ፍትህ (justice)
ልማት (development)
አገር (nation)
ጎሳ (tribe - in the neutral sense)
ተፈጥሮ (nature)
ፍቅር (love)
ስልጣኔ (civilization)
ሴኩላሪዝም (secularism)
የአሁኑ ትውልድ ደግሞ የምዕራባዊያን አገሮችን እንደ ጣዖት የሚያመልክ ይመስላል። ነፃነት ከነሱ ጎራ ነው የሚገኘው። ተራማጅነት ከነሱ ነው። ሀብት ከነሱ። ዴሞክራሲ ከነሱ። ቴክኖሎጂ ከነሱ። ስነ መግባር ከነሱ። ወዘተ።
በኔ ኢይታ ይህ አምልኮ ለአገራችን ለያንዳንዳችንም አደገኛ ነው። ለምን ብትሉኝ ይህ አመለካከት ከባህላችን፤ ትውፊታችን፤ ማንነታችን ነጥቆ እንደ ስሩ የተነቀለ አትክልት ነው የሚያደርገን።
ስለዚህም ቢዚህ ርእስ ዙርያ የተወሰኑ ጽሁፎች ለማዘጋጀት አቅጅያለሁ። የኢትዮጵያዊነት፤ የሰውነት፤ የማንነት ጉዳይ የተሳሰረበት ርእስ ነው። የምዕራባዊው ፕሮፓጋንዳ እጅግ ከባድ ነው። በመሰረታዊ አስተሳሰባችንን፤ አስተያየታችንን፤ አስተነፋፈሳችንንም ታላቅ ሚና ተጫውቷል። መሰራታዊ ሃሳቦቻችንና ቋንቋችንም ቀይሯል መቀየሩንም አናውቀውም! ይህ ሁሉ በደምብ ልናየው ይገባል።
ጽሁፎቼን ስጽፍ በተለምዶ በመጀመርያ እንደ ክርስቲያን በማቀው ክርስቲያናዊ አመለካከት ነው የምጽፋቸው። እምነቴ በሁሉ ነገር ኢግዚአብሔር አለ ብሎ ሰለሚያስተምር እንቋን የማንነት ጉዳይ ምንም ነገር ከዚህ መነጽር ውጭ ማየት አይቻልም።
ለጽሁፎቼ እንደ መግብያና ሀሳብ ማንሸራሸርያ እስቲ እነዚህን ቃላቶችን እናስባቸው፤
ዘመናዊነት (modernity)
መሻሻል ወይም እድገት (progress)
ዴሞክራሲ (democracy)
ነፃነት (freedom)
ሰው (Man)
ፍትህ (justice)
ልማት (development)
አገር (nation)
ጎሳ (tribe - in the neutral sense)
ተፈጥሮ (nature)
ፍቅር (love)
ስልጣኔ (civilization)
ሴኩላሪዝም (secularism)
Thursday, 1 February 2018
ትህትና
አባ ቲኾን በጻፉት መጸሃፍ "Everyday Saints" አባ ቲኾን አንድ ታላቅና ጀግና መኖክሲት፤ በሶቪዬት መንግስት ደጋግመው የታሰሩ የሆኑ፤ ስለ ገዳም ኑሮ ሲጠይቋቸው እኚህ መኖክሲት እንደዚህ አልዋቸው፤ «ዋናውና መጀመርያው ነገር ይህ ነው፤ ማንንም ላይ አትፍረድ»
አለመፍረድ ማለት አለመኮነን ነው። ይህ መፍረድ ድርጊትን ወይም አቋምን ጥሩ ነው ወይ መትፎ ነው ማለት አይደለም። እንደዚህ አይነት ፍርድ ተገቢም አስፈላጊም ነው። አትፍረዱ ማለት አትኮንኑ፤ ሰውን ከድርጊቱ ጋር አታቆራኙ። ሰውየው እራሱ መጥፎ ነው፤ ሃጥያተኛ ነው፤ እኔ ከሱ እሻላለሁ፤ እሱ ወደ ገሃንም ይገባል አይነቱ ነው አትበሉ አታስቡ የምንባለው። ስለዚህ ለክርስቲያን በድርጊት መፍረድ ተገቢ ነው ግን በሰው ማንነት መፍረድ ትክክል አይደለም።
በሰው መፍረድ ኢክርስቲያናዊ የሆነው አንዱ ምክነያት መፍረድ ወደ ተዕቢት ስለሚመራ ነው። ተዕቢት ደግሞ የመጀመርያውና ዋናው እግዚአብሔርን ያጣንበት ምክንያት ነው። አዳምና ሄዋን በትዕቢታቸው ምክንያት መልአክት ለመሆን አስበው ነው እጸ በለሱን የበሉትና። ስለዝህ እንደ ክርስቲያን ከትእቢት ርቀን ወደ ተቃራኒው ትህትና ነው መጠጋት ያለብን።
አዎን ትህትና አንድ ክርስቲያን ከሚፈልገው ዋና ጥሩ ባህርይ ነው። «ትህትናና ፍርሃ እግዚአብሔር ከሁሉ መልክአ ምግባር በላይ ናቸው» ትብሏል። ትህትና የሰው ልጅን ዋና ተልኮ፤ ማለት ወደ እግዚአብሔር መቅረብ፤ ለማሟላት ግድ ነው። እራሱን እንዲገመግም፤ ከፈተናና ሴጣን እንዲርቅ፤ ሌሎችን ላይ ከመጠቆም እራሱን ላይ መጠቆም። እነዚህ በሙሉ ትህትና ይጠይቃሉ።
እንደዚህ ሆኖ ማንም ሰው፤ በተለይ መሪ፤ ትህትናን ሲያንጸባርቅ ደስ ይለኛል። እራሱን ወይም ወገኑን የማያሞገስ፤ እራሱን አጥፊና ሃላፊ የሚያደርግ፤ እራሱን ጥልቆ የሚገመግም፤ ሌሎችን በፍርድ ሳይሆን በመቆርቆር አይን የሚያይ ሰው ደስ ይለኛል። ይህ ባህሪዎች ለራሱም ለዙርያው ላሉትም እጅግ ይበጃል።
እኔ አቶ ለማ መገርሳን አላውቋቸውም ግን ያዳማጥኳቸው ንግግሮቻቸው በትህትና የተሞሉ በመሆናቸው ተደስጭያለው። በዚህ ረድፍ ለሁላችንም ታላቅ ምሳሌ መሆናቸው ነው ከሁሉም በላይ ያስደሰተኝ።
ከአቶ ለማ ሌሎችን በሰሞኑ አይቻለሁ። ብአዴን በደብረ ብርሃን የጠራው የምሁራን ስብሰባ ላይ አንድ ወጣት ምህሩን በጥህትና እጅግ እጅግ አስደሰተኝ። እኛ ምሁራን ባንኖር ገበሬው (ብዙሃኑ) በሰላም አብሮ ይኖር ነበርና እኛ ነን ችግሩ። ለችግሩ መፍትሄ እናገኝለታለን ከማለት መጀመርያ እራሳችንን እንፈትሽ ብሎ ታላቅና አስደናቂ ንግግር አቀረበ። እንደዚህ አይነቱ የምላስ ሳይሆን የመንፈስ ጀግና ነው ሁላችንም የሚያስፈልገን።
ሁላችንም በሌላ ላይ ከመጠቆም፤ ችግርሮቻችንን ብሌላ ከማሳበበ፤ መፍትሄም ከሌሎች ነው የሚመጣው ብለን ከምናሰብ፤ እራሳችንን ወድቅ (disempower) ከማድረግ፤ ውስጣችንን መርምረን ሌሎች ላይ ሳንፈርድ ብንራመድ ለሁላችንም መልካም እንሆን ነበር።
እግዚአብሔር ትህትና ይስጠን። ከትዕቢት ፈተና ያርቀን። የእርስበርስ ሰላም እንድሽ ይርዳን።
አለመፍረድ ማለት አለመኮነን ነው። ይህ መፍረድ ድርጊትን ወይም አቋምን ጥሩ ነው ወይ መትፎ ነው ማለት አይደለም። እንደዚህ አይነት ፍርድ ተገቢም አስፈላጊም ነው። አትፍረዱ ማለት አትኮንኑ፤ ሰውን ከድርጊቱ ጋር አታቆራኙ። ሰውየው እራሱ መጥፎ ነው፤ ሃጥያተኛ ነው፤ እኔ ከሱ እሻላለሁ፤ እሱ ወደ ገሃንም ይገባል አይነቱ ነው አትበሉ አታስቡ የምንባለው። ስለዚህ ለክርስቲያን በድርጊት መፍረድ ተገቢ ነው ግን በሰው ማንነት መፍረድ ትክክል አይደለም።
በሰው መፍረድ ኢክርስቲያናዊ የሆነው አንዱ ምክነያት መፍረድ ወደ ተዕቢት ስለሚመራ ነው። ተዕቢት ደግሞ የመጀመርያውና ዋናው እግዚአብሔርን ያጣንበት ምክንያት ነው። አዳምና ሄዋን በትዕቢታቸው ምክንያት መልአክት ለመሆን አስበው ነው እጸ በለሱን የበሉትና። ስለዝህ እንደ ክርስቲያን ከትእቢት ርቀን ወደ ተቃራኒው ትህትና ነው መጠጋት ያለብን።
አዎን ትህትና አንድ ክርስቲያን ከሚፈልገው ዋና ጥሩ ባህርይ ነው። «ትህትናና ፍርሃ እግዚአብሔር ከሁሉ መልክአ ምግባር በላይ ናቸው» ትብሏል። ትህትና የሰው ልጅን ዋና ተልኮ፤ ማለት ወደ እግዚአብሔር መቅረብ፤ ለማሟላት ግድ ነው። እራሱን እንዲገመግም፤ ከፈተናና ሴጣን እንዲርቅ፤ ሌሎችን ላይ ከመጠቆም እራሱን ላይ መጠቆም። እነዚህ በሙሉ ትህትና ይጠይቃሉ።
እንደዚህ ሆኖ ማንም ሰው፤ በተለይ መሪ፤ ትህትናን ሲያንጸባርቅ ደስ ይለኛል። እራሱን ወይም ወገኑን የማያሞገስ፤ እራሱን አጥፊና ሃላፊ የሚያደርግ፤ እራሱን ጥልቆ የሚገመግም፤ ሌሎችን በፍርድ ሳይሆን በመቆርቆር አይን የሚያይ ሰው ደስ ይለኛል። ይህ ባህሪዎች ለራሱም ለዙርያው ላሉትም እጅግ ይበጃል።
እኔ አቶ ለማ መገርሳን አላውቋቸውም ግን ያዳማጥኳቸው ንግግሮቻቸው በትህትና የተሞሉ በመሆናቸው ተደስጭያለው። በዚህ ረድፍ ለሁላችንም ታላቅ ምሳሌ መሆናቸው ነው ከሁሉም በላይ ያስደሰተኝ።
ከአቶ ለማ ሌሎችን በሰሞኑ አይቻለሁ። ብአዴን በደብረ ብርሃን የጠራው የምሁራን ስብሰባ ላይ አንድ ወጣት ምህሩን በጥህትና እጅግ እጅግ አስደሰተኝ። እኛ ምሁራን ባንኖር ገበሬው (ብዙሃኑ) በሰላም አብሮ ይኖር ነበርና እኛ ነን ችግሩ። ለችግሩ መፍትሄ እናገኝለታለን ከማለት መጀመርያ እራሳችንን እንፈትሽ ብሎ ታላቅና አስደናቂ ንግግር አቀረበ። እንደዚህ አይነቱ የምላስ ሳይሆን የመንፈስ ጀግና ነው ሁላችንም የሚያስፈልገን።
ሁላችንም በሌላ ላይ ከመጠቆም፤ ችግርሮቻችንን ብሌላ ከማሳበበ፤ መፍትሄም ከሌሎች ነው የሚመጣው ብለን ከምናሰብ፤ እራሳችንን ወድቅ (disempower) ከማድረግ፤ ውስጣችንን መርምረን ሌሎች ላይ ሳንፈርድ ብንራመድ ለሁላችንም መልካም እንሆን ነበር።
እግዚአብሔር ትህትና ይስጠን። ከትዕቢት ፈተና ያርቀን። የእርስበርስ ሰላም እንድሽ ይርዳን።
Thursday, 13 October 2016
ኦርቶዶክስ ክርስትናና ፖለቲካ
2009/2/3
ዓ.ም.
(2016/10/13)
«እግዚአብሔር በሁልም ስፍራ አለ በሁሉም ነገርም ይገኛል» (God is everywhere present and in all things) አንድ የኦርቶዶክስ ሃይማኖት መሰረታዊ እምነት ነው። ይህ አባባል እግዚአብሔር የፈተራት ዓለም በሁለት በ«አለማዊ» እና በ«ሃይማኖታዊ» ስፍሮች እንዳልተከፈለች ይገልጻል። ወደ ቤተሰባችን፤ ስራችን፤ ንግዳችን፤ ዘፈናችን፤ መዝኒያናችን፤ ስፖርታችን፤ ትምህርትቤታችን፤ እርሻችን፤ ፖለቲካችንም ስንሄድ እግዚአብሔርንና እምነታችንን ትትን መሄድ አይቻላም! እግዚአብሔር በነዚ ስፍሮች ሁሉ አለና። ግድብ የለውም። ስለዚህ ፖለቲካና ክርስትና የተለያዩና የማይገናኙ ናቸው ማለት አይቻልም።
ስለዚህ ክርስትያኖች በፖለቲካ ልንሳተፍ እንችላለን። የማህበራዊ ኑሮ ፖለቲካን ስለሚይካትት ብንፈልግም ባንፈልጉም በተወሰነ ደረጃ ቢሆንም ፖለቲካ ውስጥ ተሳትፈናል። ሁለት ምሳሌዎች ልስጣችሁ፤ ቀረጥ መክፈል ማለት ገንዘብ ለመንግስት መስጠት ነው። የዚህን ገንዘብን አጥቃቀም የሚወስኑት ፖለቲከኞች ናቸው። በገንዘባችን ለሚያደርጉት ግን ተጠሪ ነን ግንዘባችን ነውና። በቀበሌ ወይም በማንኛውም የምንግስት መሥሪያቤት ስንገለገል ፖለቲከኞች የዘረጉትን የአስተዳድራዊ ዘዴ መቀበል ማለት ነው። ብለት ኑሮአችን ፖለቲካ አይጠፋም። ፖለቲካ አንዱ የህይወታችን ዘርፍ ነው።
ታድያ የአንድ ክርስትያን ፖለቲካዊ ኑሮ እንዴት መሆን አለበት? ይህን ለመመለስ በመጀመርያ አንዳንድ መሰረታዊ የሆኑ የክርስትና እምነቶች እንመልከት። ከላይ እግዚአብሔር ከሁሉም አለ የሚለውን አባባል ጠቅሽያለሁ። ቀጥሎ «በዐይነህ ውስጥ ያለውን ግንድ ሳትመለከት፤ በወንድምህ ዐይን ያለውን ጉድፍ ለምን ታያለህ» የሚለውን እስቲ እንመልከት። ባለንጀራችሁን እንደራሳችሁ ውደዱ ይበልጥ ደግሞ እኔ እንደምወዳችሁ ያህል ውደዱት ብሎ ክርስቶስ አዞናል። ይህን አባባልንም እንመልከት።
ሌላ አባባል፤ ቅዱስ ባስሊዮስ እንደዚህ አሉ፤ « የባለንጀራህ ሀጥያት ብቻ ከሆነ የሚታይህ ያንን ብቻ ከማየት ይልቅ በፊትም አሁንም የሚያደርገውን ጥሩ ነገሮች እንዳሉ ተገንዘብ። መፍረድን ትተህ ይህን ለማድረግ ስትሞክር ጭራሽ እርሱ ካንተ የተሻለ እንደሆነ ትረዳለህ።» ይህ አባባል ሁለት መሰረታዊ እምነቶታችንን ይገልጻል፤ እግዚአብሔር የፈጠረው ሁሉም ሰው ትንሽም ቢሆን ጥሩነት ስላለው በሌላ ሰው መፍረድ ተገቢ አይደለም።
ክርስቶስ «እኔ በልቤ የዋህና ትሑት ነኝ» ብሎ እኛም እንደሱ እንድንሆን አዞናል። ትሕትና የቀደመውና ዋናው ሀጥያታችን «ትዕቢት» ተቃራኒና መድሀኒት ስለሆነ የሃይማኖት አባቶች የምያተኩሩበት መልካ መግባር ነው። አባ ይስሐቅ ዘሶሪያ እንዲህ ብለዋል፤ «ጨው ለምግብ እንደሚሆን ትህትና ለሁሉ መልካ መግባር ይሆናል።»
የክርስትያን ፖለቲካ ኑሮ ከላይ በጠቀስኳቸው አባባሎች የሚያስተምሩን መልካ መግባሮች ነው መካተትና መመራት አለበት፤ 1) እግዚአብሔር ከሁሉም አለ፤ 2) የሌላውን ሀጥያት ከማየት ፋንታ የራሳችንን ሀጥያት አይተን ንስሃ እንጋባ እናርማቸውም፤ 3) ባለንጀራችንን ክርስቶስ እንደሚወደን እንውደድ፤ 4) በሰው አንፍረድ፤ ትሑት እንሁን ከትዕቢትና ትምክህት እንራቅ።
በዛሬው የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሁኔታ አንድ ክርስትያን እነዚህን እምነቶች ተከትሎ ምን ሊያደርግ ይገባዋል? አትፍረዱ፤ ትሑት ሁኑ፤ የራሳችሁን ሀጥያት ተመልከቱ፤ አብዛኞቻችን በፖለቲካ ዙርያ የሌላው ሰው፤ ወገን፤ ጎሳ፤ ፓርቲ ጥፋት ብቻ ነው የሚታየን። የኢህአዴግ፤ የህወሓት፤ የኦነግ፤ የሻእቢያ፤ የኢዴፓ፤ የደርግ፤ የኢሀፓ፤ የኃይለ ስላሴ፤ የዘንድሮ ተቃዋሚ፤ የዲያስፖራ፤ ወዘተ። አንድ ክርስትያን እራሱን ሳይመረምር የራሱን ጥፋቶች ተረድቶ ንስሀ ሳይገባ የማንንም፤ የኢህአዴግንም፤ ጥፋትና ስህተትን ላይ ማተኮር የለበትም።
ግን ምን የፖለቲካ ሀጥያት አለብኝ ብለን የምንጠይቅ ብዙ ነን። ከበርካታ ሰዎች ከገደለው ካሰቃየው ኢህአዴግ፤ ደርግ፤ ወዘተ ምኔ ሊወዳደር ይችላል። እስቲ ይህን ጥያቄ በምሳሌዎች ለመመለስ ልሞክር።
ጎረቤቴ ለ«ኢንቬስተር» ተብሎ መሬቱን ሲነጠቅ ረዳሁትን? ትንሽም ነገር አደረግኩለት?የምፍረአቸውን የሰፈሬን ዱሪዬዎችን ለመርዳትና ጥሩ መስመር ለማስያዝ ያረግኩት ነገር አለ? ወይም የራሳቸው ጉዳይ ብዬ ዞር ብዬም አላያቸውም። ችግር እስኪያመጡ። በፖለቲካ ዙሪያ «ኦሮሞ» ሲባል በልቤ ፍርሃትና ጥርጣሬ አይሰፍንም? ነው በንጹ ልቦና ጉዳዩን እመለከታለሁ? «እነሱ ከሚገዙን ወያኔ ይግዛን» ብዬ አስቤ አላቅምን? ግን አንድ ቀንም «ከነሱ» ጋር ቁጭ ብዬ ተወያይቼ አላቅም። ከጎረቤቶቼ ጋር ድሮ ተጣልቼ አሁንም አልተቀየምኳቸውም? በዚህ ጥላቻ ምክነያት እንኳን ለፖለቲካ ለውጥ ለምንም ነገር ከነሱ ጋር መተባበር አልችልም አይደ? ከባልደረባዬ ምሁር በትንሽ አስተሳሰብ ልዩነት ምክነያት ጠላቶች አልሆንም? እንኳን አብረን ለመስራት መተያየትም አንፈልግም አይደለምን? ስራተኞቼን እንደ ሰው ቆጥሬ አላውቅም እሁድ ቤተክርስትያን ለመሄድም እድል አልሰጣቸውም! ዘላለማዊ ቂም አልፈጠርኩባቸውም? ኢህአዴግ ይህንን ቂም ተጠቅሞ እነዚህን ሰራተኞቼን እኔን ለመግዳት ወይም የኔን አቋም ለማዳከም መጠቀም አይችልምን? የማይገባኝ ጥቅም ለማግኘት ጉቦ ሰጥችሄ አላውቅምን? ከስራ ቦታዬ በኔ ሃሳቦች የማይስማሙትን አልኮንንም? ሰራተኞች ሲሳሳቱ ችግራቸውን ከመረዳት ፋንታ አልፈርድባቸውም? ልጄ ውትድርና ገብቶ የማያምንበትን ክፉ ድርጊቶች እንዲያደርግ ይታዘዛል ያደርጋል። ልጄ ነው የሚጦረኝ እና እንደዚህ አይነቱን ጉዳይ ለሱ በማንሳት ላበሳጨው አልፈልግም እላለሁ። ታድያ እንደ የኢግዚአብሔር ልጅ ሃላፊነቴን አልካድኩምን?
እራሳችንን በደምብ ከመረመርን እነዚህ አይነቶቹ ሀጥያቶች እንዴት ከኛ ወደ ህብረተሰቡ፤ ከህብረተሰብ ወደ መንግስታችን እንደሚተላለፍ እንደሚያንጸባርቅ ልንገነዘብ እንችላለን። ክርስትያኖች የሁላችንም ኃጢአት የተገናኘው እንደሆነ እናምናለን። ለሌሎችንም ኃጢአት ሃላፊነት እንዳለብን እናምናለን። አባቶች ይህን ተጠንቅቀው ነው የሚያስተምሩን። ከላይ እንደምሳሌ የጠቀስኳቸው ኃጢአቶች እንዴት አሁን ካለው የምንግስት ስረዓት ባህሪ ጋር እንደሚገናኙ ግልጽ እንደሆነ ተስፋ አለኝ።
ክርስትያን በመሆኔ መጠን ለነዚህ ኃጢአቶች ንስሃ ገብቼ እየወደኩኝ እየተነሳሁኝ እያስተካከልኩኝ መኖር ነው የሚጥበቅብኝ። የፖለቲካ ኑሮዬም እንደዚህ ነው መሆን ያለበት። የምደግፈው የፖለቲካ አቋም፤ አመለካከት፤ ፓርቲ፤ ርዕዮተ ዓለም፤ ወዘተ ከክርስትያንነቴ ስር ነው መሆን ያለባቸው። እንደ ክርስትያን እስከኖርኩኝ ድረስ ፖለቲካው እራሱን ያስተካክላል።
ሆኖም ማንም ሰው አጥፊና ክፉ ነበር የሚያደርግ መንግስት ወይም ተቋምን መታገል የለበትም ማለት አይቻልም። እያንዳንዱ የራሱን ልብ ያውቃልና ልታገል ቢል በሱ ልፈርድ አልችልም፤ ግን ትግሉ ውጤታማ እንዲሆን በመጀመርያ የራሱን ልብና ገበና መፈተሽ አለበት። ሳይፈትሽ ሌላውን ለማስወገድ ብቻ ከታገለ ትግሉን አያሸንፍም። ወይም ይባስ ያሸንፍና ከታገለው የባሰ ሆኖ ይገኛል። ይህን እውነታ ሃይማኖታችን ያስተምረናል። እውነታም ስለሆነ በታሪክ በትደጋጋሚ ሲከሰት አይተናል! ስለዚህ በመጀመርያ ክርስትያን እንሁን፤ ሙሉ ክርስትያን እንሁን። ከሆንን ሌላው እራሱን ያስተካክላል።
Subscribe to:
Posts (Atom)