Friday 16 March 2018

ስለ ትህትና

እግዚአብሔር ክፉ መናፍስትን የማስወጣት ጸጋ የሰጣቸው አንድ ባሕታዊ ነበሩ። በአንድ ወቅት ጋኔኖቹን የሚያስፈራቸውና ከሰዎች እንዲለቁ የሚያደርጋቸው ምን እንደሆነ ለመረዳት ፈልገው ጠየቁ።

«ጾም ይሆን?» ብለው አንዱን ጠየቁት።

«እኛ መቼም አንበላም አንጠጣምም» ብሎ ክፉ መንፈሱ መለሰላቸው።

«የለሊት ሙሉ ጸሎት ይሆን?»

«እኛ አንተኛ።»

«ዓለምን ትቶ መመንን?»

«ይህ እንደ ትልቅ ነገር ይቆጠራል። ግን እኛ አብዛኛው ጊዜአችንን በየ በርሃው እየዞርን ነው የምናጠፋው።»

«ታድያ ምንድነው ይዞ ሊቆጣጠራችሁ የሚችለው፤ እባካችሁ ንገሩኝ» ብለው ታላቁ አባት ደግመው ጠየቁ።

ክፉ መንፈሱ በተአምራዊ ኃይል ጥያቄውን እንዲመልስ ተገደደ፤ «ትህትና ነው። ይህን መቼም ልናሸንፍ አንችልምና።»

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!