Sunday 11 December 2016

ተሃድሶ

ስለ «ተሃድሶ ኦርቶዶክስ» የሚባለውን ንቅናቄ አንዳንድ ሃሳቦች ለማቅረብ እወደለሁ። በመጀመርያ ትሃድሶ በትክክል ምን እንደሆነ አይታወቅም። በጾም ጊዜ አሳ መብላት አግባብ ነው የሚሉ ተሃድሶ ተብለው ሊሰየሙ ይችላሉ። እንደ ፒያኖ ወይም ኦርጋን አይነት የሙዚቃ መሳርያ ከቤተ ክርስቲያን ውስጥ መተቀም ይቻላል የሚሉም እንደዚሁ ተሃድሶ ተብለው ይሰየማሉ። ከቤተ ክርስቲያን ውስጥ ጫማ ማድረግ ክልክል አይደለም የሚሉትም እንደዚሁ። በድንግል ማርያም አማላጅነት አምነው ግን በስብከታቸው ስለሷ ብዙ የማይናገሩ ተሃድሶ ይባላሉ። ቅድስት ድንግል ማርያምን እንደ ክርስቶስ የሚያመልኩ አሉና ይህ መሆን የለበትም የሚሉም ሳይገባ ተሃድሶ ይባላሉ። የጋራ ጾም አያስፈልጉም የሚሉም ተሃድሶ ይባላሉ። በቅዱሳን አማላጅነት አናምንም የሚሉም ተሃድሶ ይባላሉ። ወዘተ። «ተሃድሶ» የሚባለው ስያሜ በተለያዩ አግባብ ያላቸውም የሌላቸውም ምክንያቶች እንጠቀማለን።

ከዚህ ጽሁፍ ግን ተሃድሶ ስል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን እምነትንም ስርዓትንም መቀየር - በትንሹም በትልቁም - የሚፈልግ አቋምን ነው። ጫማ ከቤተ ክርስቲያን እናድረግ እስከ የቅዱሳን አማላጅነት የለም የሚሉት። እነዚህ እጅግ የተለያዩ አቋሞች እንደሆኑ እራዳለሁ! ጫማ አለማድረግ የ«ትንሽ» ስረዓት ጉዳይ ነው - የእምነት ጉዳይ ቢሆን ኖሮ ከግብጽ በተ ክርስቲያን ጋር እንለያይ ነበር። ትንሽ ስረዓት ቢሆንም ምክነያት አለው - ይህን ስርዓት ለመቀየር የሚጓጓው መንፈስ በቅዱሳን አማላጅነት አላምንም ከሚለው መንፈስ በተወሰነ ደረጃ ግንኙነት አለው። ላስረዳ...

የኦርቶዶክስ ክርስቲያን እምነት በሶስት መስፈርቶች ሊፈተሽ ይችላል። እምነቱ ከጥንት ጅምሮ ያለ ነው፤ እምነቱ በሁሉም ቦታ ይገኝ ነበር፤ እምነቱ በሁሉም ይታመን ነበር። እነዚህ መስፈርቶች ከክርስቶስ ቀጥሎ ከሃዋሪያቶቹ የወረስነውን እምነት አለማጠፍም አለ«ማደስ»ም ከመንፈቅ ትቆጥበን እምነታችንን እንደተሰጠን ይዘን እንድንጠብቅ የሚገልጹ ናቸው።

የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሃሳብ እንደዚህ ነው። አዲስ ነገርን - ትንሽም ትልቅም - በቀላሉ አታስተናግድም። ቅዱስ አታናሲዮስ መጽሃፍ ቅዱስ የትኞቹን መጸሃፍት እንደሚያካትት ሲናገሩ አዲስ ነገር ነበር። መጸሃፍ ቅዱስ እነዚህ መጸሃፍቶች ናቸው ተብሎ ተሰይሞ አያውቅም ነበር። ታድያ ይህ አዲስ ነገር ነበር ወይ? በፍጹም፤ ቅዱስ አታናሲዮስ የነበረ ሁሉም በሁሉም ቦታ ከመጀመርያ የሚያምኑበትን ነው ያረጋገጡት። ሌሎች መጸሃፍቶችን የተተውበት ምክንያትም የቤተ ክርስቲያን እረኞች ህዝቡ እነዚህን መጸሃፍት በተሳሳተ መልኩ እያነበበ ወደ ኑፋቄ ሲገባ አይተው ነው።

የቤተ ክርስቲያን ስረዓትም በተመሳሳይ ቢጠበቅም ትንሽ ላላ ይላል። ስረዓትን «ታናሽ»ና «ታላቅ» ብለን መከፋፈል ይቻላል ግን ይህ ቅፍፍል ወጥ አይደለም - ታናሽና ታላቅ ዳሮች ሆነው ከመካከል ብዙ አሉ። ታናሽ ስረዓቶች ለምሳሌ ጫማ አለማድረግ፤ ታቦት፤ ወዘተ ከኛ ጋር አንድ ከሆነችው የግብጽ ቤተ ክርስቲያን የሉም። እነሱም የራሳቸው እኛ የሌለን ስርዓቶች አሏቸው። ሆኖም ስረዓትም በቀላሉ አይቀየረም። እንደ እምነት ያህል ባይሆንም ከእምነቱ ጋር እጅግ የተያያዘ ስለሆነ መቀየሩ እጅግ አስፈላጊ መሆን አለበት።

ለምሳሌ የቅዳሴአችን ዜማ የተጻፈው በ6ኛው ክፍለ ዘመን በቅዱስ ያሬድ ነው። ከዛ በፊት የነበረው ዜማ የተለየ ነበር ወይም ዜማ አልነበረም። የቅዳሴ ዜማ የስረዓት ለውጥ በቅዱስ ያሬድ ጊዜ ተካሄደ። ይህ የሚያሳየው ስርዓት መቀየር እንደሚቻል ነው። ግን ከዛ በኋላ እስካሁን ለ15 ክፍለ ዘመን አልተቀየረም። ይህ ደግሞ የሚያሳየው ስረዓት መቀየር ቢቻልም (እንደ ስረዓቱ አይነት) እጅግ በጣም ጥቂት ጊዜ ነው የሚቀየረው። የኦርቶዶክስ አስተሳሰብ ለውጥ ስለማይወድና ጥንቱን ስለሚያስቀድም።

ስረዓት ይቀየር ሲባል ለምን ብለን እራሳችንን መጠየቅ አለብን። ኦርቶዶክሳዊ ለውጥ የሚከላከለው አንዱ ታላቅ ምክነያት አብዛኛው ጊዜ ለውጥ የሚፈለገው ለማይሆን ምክነያት ስለሆነ ነው። እንደዚህ አይነት ምክነያቶች ምሳሌዎች እንደ የመንፈቅ አስተሳሰብ፤ ፖለቲካ ወይም የስልጣን ሹኩቻ፤ ፍርሃት አይነቱ ናቸው።

በዛሬው ዘመን - «ዘመናዊነት» ግዥ ርዕዮተ ዓለም በሆነበት ዘመን - የስረዓት ለውጥ (የእምነትም ለውጥ) የሚገፋፋው ከዘመኑ ጋር አብሮ ለመሄድ ነው። ቅዱስ ያሬድን ያነሳሳቸው ጾም ጸሎትና የዳዊት መዝሙርን በመድገም እግዚአብሔርን ይበልጥ ለማመስገን ፈልገው ነው። በዛሬው ዘመን ግን ብንወድም ባንወድም ብናውቀውም ባናውቀም ከዘመኑ ጋር አብሮ የመሄድ ሃሳብ ተጽእኖ ያሳድርብናል ሳናውቀውም ይገፋፋናል። በዚህ ምክነያት ከበፊት ዘመናት - ከቅዱስ ያሬድም - ይበልት ጥንቃቄ ማድረግ አለብን። ምንም አይነት ስርዓትን እንኳን ለመቀየር በጥያቄ ምልክት ውስጥም ማድረግ የለብንም።

ብለላው ቋንቋ እላይ የጠቀኩትን የቤተ ክርስቲያናችንን አስተሳሰብን መርሳት የለብንም - ለውጥን በታቻለው ምከላከልንና መፈተሽን።

ይህ ብዬ ወደ ተሃድሶ እንመለስ። በቤተ ክርስቲያናችን ስንት የሚሰራ ስራ እያለ ለምንድነው ማደስ የሚታሰበው። ንስሃ ገብተናልን? እግዚአብሔርን በሙሉ ልባችን እንድወደዋለን? ያለንን በሙሉ እንሰጠዋለን? በሰው ላይ አንፈርድምን? ገና እንድወድቃለን እንነሳለን መውደቃችን እጅግ ቢበዛም። እረኞቻችን ታድያ ድሮም እንደነበራቸው ዛሬም እንድንነሳና ለክርስቶስ ለመቅረብ ያለንን ፍላጎት ለማዳበር ብዙ ስራ አላቸው። ይህ ሁሉ ስራ እያለ ስለማደስ ማሰብ ምን አስፈለገ?

እንዳልኩት የዘመኑ ርዕዮተ አለም በፍጹም ሳናውቀው ከባድ ተእጽኖ ያደርግብናል። ካቶሊኩንና ፕሮቴስታንቱን እያየን ሳናውቀው በአፋችን እንደተሳሳቱ እየተናገርንም በልባችን አንዳንድ ነገሮቻቸው በነበር ብለን እንመኛለን። ስነ ስረዓት፤ ንጽህና፤ ፍልስፍና፤ ሃብት፤ ብልጠት፤ ስነ መግባር ወዘተ። ቤተ ክርስቲያናችን ትታደስ ስንልም እንደነዚህ ትንሽ ትሁን ማለታችን ነው። ምንጩ ይህ ነው አደጋውም ይህ ነው።

ታድያ እንደዚህ ስንል ሌላው አብዛኞቻችን በተለይ ካህናቶቻችን በተለይ እናድስ የሚሉት የማናውቀው ነገር ምህ ያህል ካቶሊኩና ፕሮቴስታንቱ - በተለይ ፕሮቴስታንቱ - ችግር ውስጥ እንዳለ ነው። «ፔንጤ» የምንላቸው በትክክሉ «ኤቫንጄሊካል» የሚባሉት ለምሳሌ ባለፉት 50 ዓመታት ኢትዮጵያ ውስጥ ቢያድጉም ባሁኑ ጊዜ በምንጫቸው ሃገር አሜሪካ እየመነመኑና ታላቅ አደጋ ላይ ናቸው። መሰረታው እምነታቸው የግል ስለሆነ - ቤተ ክርስቲያን ሳይሆን ግለ ሰብ ነው ሃይማኖቱን ብቻውን ከመንፈስ ቅዱስ ጋር እይሚያውቀው ብለው ስለተነሱ - አሁን እስከ 30,000 አይነት ክፍፍሎች አላቸው። ስንቶቻችን ነን ይህን የምናውቀው። የቆዩት ፕሮቴስታንቶች (በኢንግሊዘኛ «ሜይንላይን» ይባላሉ) እንደ አንግሊካን ደግሞ ከሁሉም ክርስቲያን ከሚባሉት የመነመኑና ምእመናን ያጡ ናቸው። ይህን ስንቶቻችን ነው የምናውቀው? አሜሪካን ሀገር ትልቁ የክርስቲያን ፍልሰት ከፕሮቴስታንት ወደ ኦርቶዶክስ እንደሆነ ስንቶቻችን ነን የምናውቀው? ባንዳን የኦርቶዶክስ ሃገረ ስክበቶች አብዛኛ ካህናት ከፕሮቴስታንትነት ውደ ኦርቶዶክስ የተቀየሩ እንደሆነ ስንቶቻችን እናውቃለን? ኦርቶዶክእነሱ ወደ ኦርቶዶክስ ይመጣሉ እኛ ደግሞ ወደነሱ መሄ እንፈልጋለን!

ክሃገራችን ውጭ ብንመለከት ይበጀናል። ውጭ ሃገር ያለነው - በተለይ ካህናት - ስራችን ብለን ዙርያችን እንመልከት። የክርስትና ድርጅቶች አካሄድን እንመልከት። ዛሬ ከምንጩ አሜሪካ እየጠፋ ያለው ፕሮቴስታንት ሃይማኖት ነገ ኢትዮጵያ በዚሁኑ ምክነያት እንደሚጠፋ እንወቅ። ባለፉት ዓመታት በሃገራችን የተከናወነው የኦርቶዶክስ ወደ ጴንጤ ፍልስትን ብቻ አንይ። ሃገራችን ውስጥ እራሱ እነዚህ ድጅጅቶች እንዴት ቀንበቀን እየተፈረካከሱ እንደሆነና እየተባዙ እንደሆነ እንይ።

ምን አልባት ዞር ዞር ብለን ይህን ሁሉ ካየን የፕሮቴስታንት አደጋም የዘመኑ ፈተናንም ልንረዳው እንችላለን። ይህን ተረዳነው ማለት ደግሞ እንታደስ የሚለው ስሜት ይቀንስልናል። አስተያየታችንን ያስተካክላል ሚዛናዊም ያደርጋል።

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!