Sunday 24 March 2019

የመጠላለፍ ፖለቲካ ቁጥር 1,999,999

መቼስ እኛ ጎሰኝነትን እንጠላለን ህገ መንግስቱ ይቀየር የምንለው የመጠላለፍ ፖለቲካ ባለሙያዎች ነን። ህወሓት የሀገራችን 6%ም የማይሆን ድጋግ ይዞ ለ27 ዓመት ሲገዛን እንኳን መታገል መደራጀትም አቅቶን ቆየን። በተለይ አማራ ክልል ውስጥ የህወሓት ሰዎች አንድ ለመቶ ሺ ሆነው እንደፈለጉት ሲጫወቱብን ማንም ሳናደርግ ቆየን። በዲያስፖራ ያለነውም ከሳንቲሞች በቀር ማዋጣት አልቻልንም ምንም ቁም ነገር ያለው ድርጅትም አልነበረንም። ለማስታወ ያህል የነ ሻቢያ እና ህወሓት ዲያስፖራዎች በዓመት በአስርት ሚሊዮን ዶላር ነበር ለአቋማቸው የሚያዋጡት።

ዛሬም አክራሪ ጎሰኛው ህልውናችንን አደጋ ላይ እያደረገ እኛ እርስ በርስ እንጠላለፋለን። አሁንም የአማራ ብሄርተኞች እና «አንድነት ኃይል» ወዘተ ፉክክር አልበረደም። አቋማችን አንድ ሆኖ፤ «ህገ መንግስቱ ይቀየር» «ጎሰኝነት ይቅር»፤ እንኳን መተባበር በሰላም አብረን መኖር አልቻልንም። ስለ isolated attack አይደለም የማወራው። በየ አይነቱ ሰው አለ። እንደዚህ አይነት ነገሮች ይከሰታሉ። አብን አደረገው አይባልም። ሆኖም እንደዚህ አይነት ድርጊቶች pattern ሆኖዋል። በሁለቱም ወገን ያለው የአለመተባበርን መንፈስ የሚያንጸባርቅ መንፈስ።

አንዱ መፍትሄ ቀላል ነው፤ እንዲህ አይነት ክስተት ሲፈጠር ሁሉም ወገኖች በይፋ ጮክ ብለው ማውገዝ አለባቸው። ይህ ፖለቲካ 101 ይመስለኛል። ደጋፊዎችህ መስመር እንዳይስቱ፤ ሌሎች ባንተ እንዲተማመኑ የሚደረግ ነገር ነው። የጸብ መንፈስን በህብረት መንፈስ መተካት ነው። ማውገዝ ድርጊቱን እኔ ነኝ ያደረግኩት ብሎ ማመን አይደለም፤ ይህ የታወቀ ነገር መሆኑ ሁላችንም እንደምንረዳ ተስፋ አለኝ። ደግሞ ስለተወገዘ ደጋፊ አጣለhu የሚል እንደሌላ ተስፋ አለኝ። አብንን ማንም outflank የሚያደርግ ድርጅት የለም። ማለት አብን ያወገዘው የትም መሄጃ የለውም። ስለዚህ አብን እንደዚህ አይነት ድርጊቶችን ቶሎ ብሎ ማውገዝ አይጎዳውም እጅግ ይጠቅመዋል።

የአንድነት ኃይል ደጋፊዎችም እነ አብንን እንተው። ማለት ከተቸን ወንድማዊ ምክር በያዘ መልኩ ነው እንጂ መበሻሸቁ ያብቃ። አሁን ቁልፍ ጊዜ ነው፤ እንደ ጥንት አባቶቻችን የሰለጠነ እና የሰከነ ፖለቲካ አሁን ግድ ነው። የዓመታት ህጻንነታችን ለውቅቱ አይበጅም።


No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!