Saturday 9 March 2019

የአዲስ አበባ ህዝብ መደራጀት ምን ይመስላል?

ይዽርጅጥ ጽም፤ «የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ድርጅት»

ተእልኮ፤ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች መብት እና ጥቅም ለማስከበር የሚሰራ ድርጅት።

መሰረታዊ አቋሞች፤ ፩) አዲስ አበባ በአዲስ አበባ ነዋሪዎች ነው መገዛት ያለበት ፪) አዲስ አበባ ከጎረቤት ኦሮሚያ ክልል በተገቢው መልካም እና ገንቢ ግንኙነት ሊኖረው ይገባል ፫) የአዲስ አበባ ህዝብ መብቶች መከበር አለበት ፬) መካከለኛው እና ለዘብተኛው መንገድ መቅደም አለበት፤ ጸንፈኝነት ለአዲስ አበባ ህዝብ ጎጂ ነው።

የአደረጃጀት ሂደት፤ ፩) 100 የአዲስ አበባ ባለሃብቶች ሰብስቦ ከያንዳንዱ 10 ሚሊዮን ሰብስቦ መሰረት ማድረግ ፪) ሰፊ የንቃት እና የአባል መለምለም ሂደት አካሄዶ አንድ ሚሊዮን አባላት ማግኘት ፫) አዲስ አበባን በአንድ ለአምስት አሰራር ሁሉንም የህብረተሰብ እና ኤኮኖሚ ክፍል መቆጣጠር።

ስልቶች፤ ፩) አንድነት፤ የሃሳብ ልዩነቶች በአግባቡ ተንሸራሽረው መፍትሄ ይገኛሉ። ድርጅቱ ጸብ፤ ቂም፤ ሹክሹክታ ወዘተ ይጸየፋል ፪) ግልጽነት፤ ሚስጥርነት ድክመትን ያመጣል። የድርጅቱ ስራ በሙሉ የግልጽነትን ፈተና መቋቋም አለበት፤ ሚስጥር ከወጣ የሚጎዳ ድርጅት መሆን የለበትም ፫) ተሳታፊነት፤ ድርጅቱ አባላት እንዲሳተፉ መጣር አለበት አባሉ የድርጅቱ ባለበትነት እንዲሰማው።

የሰለጠነ እና የሰከነ ፖለቲካ መንፈስ፤ ለቅዋሜ የሚይመች አቋም፤ ድርጅቱ ኢ-ስሜታዊ ሆኖ የሚወስደው አቋም እና የሚያንጸባርቀው ሃሳብ ማንኛውንም ፈተና የሚቋቋሙ መሆን አለበት። ምሳሌዎች፤

፩) ልዩ ጥቅም ጉዳይ፤ «እንዴት ለኦሮሞ/ኦሮሚያ ልዩ ጥቅም ይኑር ትላላችሁ» ከማለት ምንድነው ልዩ ጥቅም ብሎ ወደ ውይይት መግባት። የኦሮሚያ ልዩ ዞን ነዋሪዎች የአዲስ አበባ አገልግሎትን ማግኘት ይችላሉ፤ የኦሮሚያ ነጋዴዎች በአዲስ አበባ እንደ ነዋሪ መነገድ ይችላሉ፤ ወዘተ አይነቱ ልዩ ጥቅም እንደ ማንኛውም ሜትሮፖሊታን ከተማ ተገቢ ነው። እስቲ ሌላ ምን ልዩ ጥቅም አለ ብሎ መወያየት ነው የድርጅቱ መንገስ።

፪) ኦሮሙማ በአዲስ አበባ፤ ከቋንቋ በላይ ኦሮሙማ የለም። ስለሆንም አዲስ አበባ በኦሮሚያ ልዩ ዞኖች በመከበቧ ኦሮምኛ የከተማዋ ሁለተኛ ቋንቋ ብትሆን መልካም ነው። በኦሮሚያ ልዩ ዞኖች አማርኛ እንደሚሰራው በአዲስ አበባ ኦሮምኛ ሊሰራ ይገባል።

፫) «የአዲስ አበባ ባልቤት ኦሮሚያ ነው»፤ ይህ አባባል ኢ-ዴሞችራሲያዊ ነው። የማንኛውም ቦታ ባለቤት ነዋሪው ነው። አዲስ አበባም ይሁን ልዩ ዞኖቹ ነዋሪዎቻቸው ናቸው የፖለቲካ ባለቤቶቹ። አለበለዛ ወደ አምባገነነት ገባን ማለት ነው።

፬) ተፈናቃዮች፤ የኦሮሞ ገበሬም ሌሎች የአዲስ አበባ እና ዙርያ ተፈናቃዮች በሙሉ ጉዳያቸው ይታይ። ማን ተፈናቀለ ምን ያህል ካሳ ተሰጠው ማን ካድሬ/መሪ በምዝበራ ተጠቀመ። ከምርመራው በኋላ እርምቶች ይደረጉ። አልፎ ተርፎ መሬት የግል ይሁን የሚለውን አቋም ድርጅቱ ያራምድ። መሬት የግል ቢሆን ኖሮ መፈናቀል የሚባል አጸያፊ ነገር አይኖርም ነበር። አልፎ ተርፎ አዲስ አበባ ዙርያ ያለው ኦሮሞ እና ሌሎች ገበሬዎች እጅግ ሃብታም ይሆኑ ነበር መሬ ታቸውን በመሸጥ። መንግስት 100,000 ብር ካሳ የሚሰጠው ግለሰብ የገበያ ዋጋውን አንድ ሚሊዮን ብር ሊሰጠው ይችላል።

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!