Showing posts with label ህሊና. Show all posts
Showing posts with label ህሊና. Show all posts

Monday, 10 September 2018

«ብዛት ቀጥሎ ጥራት» መመሪያ ያመጣው የችልተኝነት እና ስነ መግባር እጦት

ለረዥም ዓመታት የኢህአዴግ መንግስት «ብዛት ቀጥሎ ጥራት» የሚለውን መፈክር ለመንግስት አገልግሎት በሙሉ ይጠቀም ነበር። በትምሕርት፤ ጤና፤ መሠረተ ልማት፤ ቴሌኮም፤ ውሃ፤ መብራት ወዘተ የመንግስት ቱክረት ለብዙሃኑ አገልግሎት በሰፊው ማቅረብ ነበር። እንደሚታወቀው «ብዛት» እና «ጥራት» ተፎካካሪ ናቸው፤ ብዛትን ለመጨመር ጥራትን መቀነስ ያስገድዳል ጥራትን ለመጨመር ብዛትን መቀነስ ያስገድዳል። የኢህአዴግ መንግስት ያደላው ወደ ብዛት፤ ወጪ መቀነስ አና ጥራት በመከነስ። ውጤቱ ብዛት እና አነስተኛ ጥራት ነው።

መንግስት ይህን የብዛት እና ጥራት ሚዛን ምን ይምሰል እና ወደ የትኛው እናዳላ ብሎ ሲገመግም ለግምገማው ብዙ ግብአቶች (መስፈርቶች) ታይተዋል ብዬ እገምታለሁ። ለምሳሌ 1) ህዝቡ ምንድነው የሚጎድለው፤ 2) ህዝቡ የተወሰነ አገልግሎት ነው ወይንም ዜሮ አገልግሎት ነው የሚያገኘው፤ 3) የሌሎች ሀገሮች ልምድ ምንድነው፤ 4) አቅማችን ምንድነው የሚፈቅደው፤ ዛሬውኑ ጥራት ማቅረብ እንችላለን ወይንስ አንችልም፤ 4) ለፖለቲካ የሚያዋጣን ምንድነው፤ 5) በጀታችን ምንድነው የሚፈቅደው፤ ወዘተ። እነዚህ የተለመዱ "textbook" ጥያቄዎች ናቸው።

ግን እንደሚመስለኝ አንዱ ያልተካተተ መስፈርት «ባህል» ነው። ባህል ስል ብዛት ላይ ስናተኩር እና ጥራት ለጊዜውም ቢሆን አያስፈልግም ስንል፤ ይህን ስንሰብክ እና እንደ ፖሊሲ ስናራምድ ምን አይነት የስራ እና ሌላ ባህል ነው ስራተኛው እና መላ ህዝቡ ላይ እያዳበርን ያለነው የሚለው ጥያቄ ነው። በስነ መግባር እና ግብረ ገብ በኩል ምን አይነት የባህል ጫናዎች ነው ይህ ፖሊሲ የሚያመጣው? ይህ ጉዳይ ምናልባትም ዋናው ቢሆንም የታየ አይመስለኝም።

እኔ እንደሚገባኝ ጥራትን ትቶ ብዛት ላይ ማተኮር ባለሞያዎቻችን ላይ የ«ችልተኝነት» ባህል እና ባህሪ እንዲያድርባቸው አድርጓል። በስራቸው ከመኩራት እና ለሞያቸው ክብር እንዳይኖራቸው አድርጓል። የስነ መግባር እጦትንም አስፋፍቷል። እነዚህ ጉዳቶች በሰው ስነ ልቦና እና አቅም (human capital) ዙርያ ስለሆኑ ከብዛት ለሚገኘው ቁሳዊ ጥቅም ይልቅ ጉዳቱ እጅግ ከባድ ነው።

እስቲ ይህ «ችልተኝነት» እና ስነ መግባር እጦት» እንዴት እንደሚከሰት ምሳሌ ላቅርብ። አንድ ሐኪም ብዙ ቀዶ ጥገና ለማድረግ አቋራጭ  መንገዶች (short cut) ይጠቀማል። አንድ አንድ አስፈላጊ የሆኑ ጥንቃቄዎችንም አያደርግም። ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ይህ ልምድ እና ባህል ይሆናል በሐኪሙ ዘንድ ብቻ ሳይሆን በሐኪም ቤቱ እና ባልደረቦቹ። ችልተኝነት ባህል ይሆንበታል። ለሐኪም ቤቱም የችልተኝነት እና የግድየለሽነት ባህል እንዲሰፍን ያደርጋል።  ከዛ በኋላ አንድ ቀን ይህ ሐኪም ወደ ጥራት ያለው አሰራር ተቀየር ቢባል መቀየር ያስቸግረዋል። ልምድ እና ባህል ለመቀየር ረዥም ጊዜ ይፈጃል።

አልፎ ተርፎ ይህ የችልተኝነት እና በፍጥነት አለ ጥንቃቄ መስራት ባህሪ ሐኪሙ ተካሚውን እንደ ሰው ሳይሆን እንደ ቁጥር እንዲመለከት ያደርገዋል። 100 ሰው ከማክም ዛሬ 150 ነው የማክመው ብሎ እራሱን ቢያዝናናም ውስጡ የሚያደርገው ነገር ትክክል አለመሆኑ ስለሚያውቅ ታካሚውን እንደ ሰው አለማየት ይሞክራል ("objectify" ያደርጋቸዋል)። ህሊናችን 100 ሰው ክምንጠቅም አንድ ሰው ባንገድል እንደሚሻል ስለሚነግረን ("do no harm" እንደሚባለው) ማለት ነው። ሐኪሙ ቀዶ ጥገና ላይ ተገቢው ጥንቃቄ ባለማድረግ  ሰዎች ይጎዳሉ ወይንም ይሞታሉ። ሐኪሙ ይህ ጸጸት ህሊናውን ያስቸግረዋል።

«ብዛት ቀጥሎ ጥራት» የሚል ፖሊሲ ሲነደፍ ይህ ሁሉ መታሰብ ነበረበት። ግን አልታየም። ዛሬ የጠ/ሚ አብይ መንግስት ይህን መፈክር ትተነዋል እና ወደ ጥራት እንሄዳልን ብሏል። ጥሩ ውሳኔ ይመስለኛል። ይህ የፕሊሲ ለውጥ የሰው አቅምን (human capital) ከጊዚያዊ የቁስ ጥቅምን አብልጦ ያያል እና ትክክለኛ እና አዋጪ ነው። በዋናነት ሰውን ከራሱ ጋር ከህሊናው ጋር የሚያጣላ መርህውን ያስቆማል። ቀጥሎ ሰራተኛም አዛዥም በስራው እንዲኮራ እና የ«ሙያ ስነ መግባር» እንዲኖረው ያደርጋል። የአገልግሎት ተጠቃሚ ጉዳትን እንዲቀንስ ያደርጋል። ሙያተኛው በስራው እና በሙያው ሲኮራ፤ ህሊናው ንፁ ሲሆን፤ ለተስተናጋጁ ሲቆረቆር ወዘተ ስራው ጥሩ ይሆናል፤ እየተሻሻለ ይሄዳል እና ለኤኮኖሚው ዘለቀታ ያለው መሻሻል ያደርጋል።

ግን የተበላሸ ባህልን መቀየር እጅግ ከባድ ነው። ቁሳቁስ መስራት እና መገንባት ቀላል ነው። ግን የሰው ልጅን መጠገን እና ማጎልበት ከማድ ነው። በዚህ ምክንያት ወደ ፊት ፖሊሲዎች ሲዋከሩ በሰው አቅም እና ስነ ልቦና ያላቸው ጫናዎች በጥንቃቄ መታየት የሚኖሩባቸው ይመስለኛል።

Friday, 6 April 2018

የህዝብ ብዛት

የኢትዮጵያ ህዝብ ቁጥር በዝቷል በተለያዩ መንገዶች የህዝብ ቁጥር እድገትን መቀነስ አለብን ሲባል እጅግ አዝናለሁ። በተለይ የኛ ምሁራን ልሂቃን እንደዚህ ሲሉ ስለ ሀገራችን ህልውና እሰጋለሁ። ሀገራችን ብዙ የፖለቲካ የኤኮኖሚ የመሐበረሰብ ችግሮች አሉትና ከነዚህ ሁሉ የሰው ቁትር መብዛት «ችግር» ከተባለም ትንሹ ነው። የሰው ቁጥር አለ አግባብ ጨምሯል ከተባለም ምክንያቱ የእርግዝና መከላከያ እጦት ሳይሆን ሌሎች የኤኮኖሚና የፖለቲካ ችግሮች ናቸው።

እስቲ አንዳንድ እውነታዎች እንመልከት፤

1. በገጠር ሴቶች በአማካይ ስድስት ልጆች ይወልዳሉ። በአዲስ አበባ በአማካይ ሁለት ልጆች ይወልዳሉ። ላለፉት 43 ዓመት የመንግስታችን የመሬት ፖሊሲ ህዝባችን ከገጥር እንዳይወጣ አድርጓል። ምክንያቱም አንድ ገበሬ ገጠርን ትቶ ወደ ከተማ መምጣት ከፈለገ መሬቱን መሸጥ ስለማይችል ከሞላ ጎደል ባዶ እጁን ወደ ከተመ መምጣት ስለሚሆንበት አያደርገውም። በዚህ ምክንያት 43 ዓመት በፊት የህዝባችን 85% የገጠር ነዋሪ ነበር አሁንም ወደ 80% የገጠር ነዋሪ ነው። የመሬት ፖሊሲው ባይኖር ይህ ቁጥር ዛሬ ምናልባት 60% ይሆን ነበር። እንደዚህ ቢሆን ኖር 80% ፋንታ 60% ነበር ስድስ ልግ የሚወልድው 20% ፋንታ 40% ሁለት ልግ ይወልዳል። በዚህ ምክንያት የጠቅላላ የህዝብ ቁጥር እድገት ይቀንስ ነበር።

2. ሀብት ምቾት ድሎት ከትመት (urbanization) በጠቅላላ ብልጽግና (development) በጨመረ ቁጥር የቤተሰብ መጠን ይቀንሳል። ይህ ንድፈ ሐሳብ (theory) ሳይሆን ያለፈው የ100 አመት የዓለም ታሪክ የመሰከረው እውነታ ነው። በሀገርም በህብረተሰብም ደረጃ ይህ እውነታ ይታያል። ሀብታም ሀገሮች ብዙ አይወልዱም ከነሱም የሚወልዱት ካልበለጸጉ ሀገሮች የመጡ መጤዎች ናቸው። ማንኛውም ሀገር አማካይ ሀብቱ በጨመረ ቁጥር የቤተሰብ መጠኑ ይቀንሳል። ስለዚህ በኢትዮጵያም «ብልጽግና» በጨመረ ቁጥር የሚወለደው ቁጥር ይቀንሳል። ስለዚህ አሁን እንቀንሰው ብሎ መርሯሯጥ አያስፈልግም።

3. የህዝብ ብዛት ሀብት ነው። የምዕራብ ሀገሮች ፍልሰትን (immigration) የሚጋብዙት ምክንያት የሰው እጥረት ስላላቸው ኤኮኖሚያቸው እየተጎዳ ስለሆነ ነው። የአዲስ አበባ ኤኮኖሚ የሚንርበት አንዱ ምክንያት ከገጠር ወደ ከተማ ያለው ፍልሰት ነው። የሰው ኃይልና የሸማች (consumer) ቁጥር በመጨመረ ቁጥር የኤኮኖሚ እንቅሳሴ ይጨምራል። በውጭ ግንኙነት አንጻርም ብዙ ህዝብ ያለው ሀገር በዓለም ላይ ያለው ኃይልና ሚና ይጨምራል። የኢትዮጵያ የዝብን ቁጥር በአባይ ግድብ ላይ ያለው ሚና ትንሽ አይደለም። ስለዚህ የህዝብ ብዛት እንደ እንቅፋት ብቻ መታየት የለበተም።

4. ኢትዮጵያ ገና ብዙ የህዝብ ቁጥር ማስተናገድ የምትችል ሀገር ናት። ካላት ለም መሬትና ሌሎች የተፈጥሮ ምንጮች አንጻር ምናልባት እስከ 200 ሚሊዮን ትችላለች። ጃፓን የኢትዮጵያ አራት እጥፍ ሰው በካሬ ኪሎሜትር አላት። ስለዚህ ኢትዮጵያ ትጨናነቃለች ብለን ልንሰጋ አይገባም።

ከዚህ አልፎ ተርፎ እንደ ኦርቶዶክስ ክርትያን የህዝብ ቁጥርን «መቆጣጠር» የሚባለው ነገር ያሳስበኛል። በተለይ የወሊድ መቆጣጠርን ማስፋፋት ያሳስበኛል። እንደዚህ አይነት ጉዳይ ውስጥ መግባት ትዕቢትን ነው የሚጋበዘው። እራሳችንን እንደ አምላክ እንድናይ ይፈትነናል። ከእግዚአብሔር የሰጠንን የተፈጥሮ ተልእኮ እንድንወጣ ይፈትነናል። ለዚህም ነው የሃይማኖት አባቶቻችን በሙሉ የቃወሙታ። ይህን መጠቀም ከሰው ተልእኮና ማንነት ይጋጫል ማጣት ነው ይላሉ። እርግጥ ካህናት በእረኝነት ሚናቸው በአንዳንድ አጋጣሚዎች የሃይማኖት ልጆቻቸውን እንዲጠቀሙ ሊፈቅዱ ይችላሉ ግን በጠቅላላ ከተቻለ አይመከርም። የስጋ ግንኙነትና መውለድ በተፈጥሮ የተገናኙ ናቸው ማለያየት ለሰው ልጅ ጎጂ ነውና።

ይህን እያወቅን የህዝብ ቁጥር እድገት እንዲቀንስ ተግባራዊ ስራዎች እናካሄድ ማለት ይከብደኛል። በተለይ በወሊድ መቆጣጠርያን በመጠቀም እንቀንስ ማለት ይከብደኛል። ለተጠቃሚው መንፈስ ጎጂ ነው ብዬ የማምነው ነገርን ማስፋፋት ህሊናዬ አይፈቅድልኝም። ሰዎች በገዛ ፍቃዳቸው ቢጠቀሙ ልፈርድባቸው አይገባም አልችልም «መብታቸው» ነው። ግን እንደ መንግስት መርህ ይህን ማስተዋወቅና ማስፋፋት ጎጂ ነው ብዬ ነው የማምነው። የቤተሰብ መጠንን ይቀንሳል ግን የመንፈሳዊ ጉዳቱ በምዕራቡ ዓለም የምናየው ኢትዮጵያ ውስጥ ማየት አልፈልግም። አዎ ዛሬ በሀገራችን በደምብ ተስፋፍቷል ግን መንግስት ከዚህ ጉዳይ እራሱን ቢያወጣ እወዳለሁ።

አልፎ ተርፎ ከላይ እንደጠቀስኩት በኔ እምነት የህዝብ ቁጥራችን አሳሳቢ ጉዳይም አይደለም። ክትመት ብልጽግና በጨመሩ ቁጥር የህዝብ ቁጥር እድገት ይቀንሳል። ቻይና ለ40 አመት ህዝቧ እንዳይወልዱ አድርጋ አሁን የህዝብ ቁጥራችን አንሶ አሳስቦናል ትላለች! እንማር!

ሀገራችን ገና «አልሞላችም»። ስለዚህ ትኩረታችንን ወደ ሌሎች የኤኮኖሚ የፖለቲካ የመሐበረሰብ ጉዳዮች ይሁን። እነዚህን ጉዳዮች በማሸነፍ የህዝብ ብዛት ጉዳያችንም በራሱ ይስተካከላል።

Friday, 17 November 2017

ከማነኛዉ ወገን ነህ? ቄሱ!

(from Father Arseny: Priest, Prisoner, Spiritual Father)

በመጀመሪያ ወደ እስር ቤት ስትገባ ቀናትን ትቆጥራለህ፣ ከዚያም ሳምንታትን፣ ከሁለትዓመታት በኋላ በሚመጣዉ ጊዜ የምታደርገው ሞትን መጠበቅ ብቻ ነው፡፡ አድካሚ የጉልበት ሥራ፣መራራ ረሐብ፣ እርስ በእርስ መናቆር፣ መደባደብ፣ ብርዱና ከቤተ-ሰብ መለየቱ ያደድቡህናየማይቀረውን ሞት ብቻ እንድታስብ ትሆናለህ፡፡ ስለዚህ አብዛኛዎቹ እስረኞች በስነ-ምግባር ረገድደካሞች የሚሆኑት፡፡

ለብዙዎቻችን የፖለቲካና ለሁሉም የወንጀለኛ እስረኞች ስሜታችን እንደ ሁኔታዉ ግራና ቀኝየሚዋልል ነበር፣ የአለቃው ቁጥጥር፣ የሚሠረቅ ዳቦ፣ እርስ በእርስ መናቆር፣ በተለይ በእስር ቤቱለተመደቡ እስረኞች የተመደበው እጅግ ከባድ የጉልበት ሥራ፣ ልዩዉ የቅጣት ክፍል፣ በረዶየሚሆኑ ጣቶች ወይም በጎረቤት የእስር ቤቱ ክፍሎች ውስጥ የሚሞቱት እስረኞች ስሜትንለመቀያየር ምክንያቶች ነበሩ፡፡ ሐሳብህ ሁሉ ተራና በእነዚህ ላይ ብቻ የሚያተኩሩ ይሆናሉ፡፡ እጅግበጣም የአያሌዎቹ እስረኞች ሕልም እስከሚጠግቡ በልተው ለሁለት ወይም ለሦስት ሰዓታት ያህልመተኛት ወይም ግማሽ ሊትር ቮድካ አግኝተው ሁሉንም ጨልጠው እንደገና ሌላ ተጨማሪ ምግብቢሰለቅጡ በወደዱ ነበር፣ ይሁን እንጂ እነዚህ ሁሉ ባዶ ምኞቶች ብቻ ነበሩ፡፡

እጅግ በጣም ትቂት የፖለቲካ እስረኞች በተቻላቸው መጠን ርኅሩኅ ሆነው ለመቆየት ሞከሩ፣ራሳቸውንም ከሌላዉ በመለየት፣ እርስ በእርስ በመደጋገፍና ራሳቸውን ወደ ተራ የወንጀለኛ እስረኞችዝቅ ላለማድረግ እየጣሩ ነበር፡፡ በተቻላቸው መጠን የእስር ቤቱ ደንብ በሚፈቅደው መሠረትራሳቸውን በማያዋርድ ሁኔታ ይኖራሉ፡፡ እነዚህ ሰዎች ከእስር ቤቱ የበረንዳ ማዕዘን ላይ ቆመውቃለ-ተናብቦ/ሌክቸር ያደርጋሉ፣ ግጥም ወይም አጭር ሳይንስ-ነክ ጽሑፍ ያነባሉ፣ አልፎ አልፎምየትም ባገኙት ብጣሽ ወረቀት ሳይቀር ማስታዎሻ ይጽፋሉ፡፡ በሆነ ርእሰ-ጉዳይ ላይ ሞቅ ያለ ክርክርይነሣል፣ ይሁን እንጂ እጅግ በጣም የሚጦፈው ፖለቲካን አስመልክቶ የሚደረገው ክርክር ነበር፡፡አልፎ አልፎ የወንጀል እስረኞችም ሳይቀር በክርክሩ ይቀላቀሉ ነበር፤ ፖለቲከኞች በፖለቲካ ረገድብዙም ፍላጎት አይታይባቸውም፣ ይሁን እንጂ አልፎ አልፎ ፍላጎቱ ነበራቸው፡፡ ሰዎች በስሜትየሚቃወሟቸውን በጥላቻ ይከራከሯቸው ነበር፡፡ አባ አርሴኒ በዚህ ክርከር ፈጽመው አይሳተፉም፡፡ነገር ግን ከዕለታት አንድ ቀን ያለፍላጎታቸው ተጎትተው ገቡ፡፡

ምንም ጊዜም እስረኞች ሐሳባቸውን ለመግለጽ ይፈራሉ፣ ይሁን እንጂ ወደሞቀ ክርክርውስጥ ሲገቡ ፍርሃት ሊያስከትል የሚችለውን ነገር ሁሉ ይረሱታል፡፡ በክርክሩ ከሚሳተፉት መካከልትቂቶቹ የአሰብሁትን መናገር ሳልችል ድምፄ ታፈነ፣” ይላሉ፡፡

እስረኞች ተቆጥረው የእስር ቤቱ በሮች ተቆለፉ፣ ከግድግዳዉ በስተጀርባ ነፋሱ እየነፈሰነበር፤ ግግሩ በረዶ መስኮቶችን እንዳይከፈቱ አደረጋቸው፣ ክፍሉ የታፈነና ዕርጥበት-አዘል ነበር፣ሆኖም ግን ውስጡ ሞቃት ነው፡፡ አምፖሎቹ ከሚፈለገው ከግማሽ በታች ብርሃናቸው መጠን ባነሰያበሩ ነበር፡፡ እነዚህ ሁሉ ትካዜና ሐዘን እንዲኖር ያደርጋሉ፡፡ በመሆኑም ሰዎች ብቸኛ ይሆናሉ፡፡እስረኞቹ በአንድነት ተሰበስበው መነጋገር፣መከራከርና ያለፈውን ማስታወስ ጀመሩ፡፡ ወንጀለኛእስረኞች ካርድ ወይም እንዶሚኖ ለብር ወይም ለመቁኑን እየተጫወቱ ነበር፡፡ አባ አርሴኒ ካረፉበትአልጋ አጠገብ የተሰበሰቡ እስረኞች በመንግሥት ላይ ያላቸውን አመለካከት ርእሰ-ጉዳይ በማድረግኃይለኛ ክርክር አደረጉ፡፡ በ15 ደቂቃዎች ውስጥ 20 የሚሆኑ ሰዎች ወደ ክርክሩ ተቀላቀሉና ክርክሩጦፈ፡፡ አንዱ የአንዱን ንግግር በማቋረጥ ሥጋት ጨመረ፡፡ ከተከራካሪዎች መካከል ቀድሞ የፓርቲአባል የነበሩ፤ ከልዩ ልዩ የሕይወት ተሞክሮዎች የተማሩ ሰዎች፤ በጣም ትቂት ቭላስቶቭትሲዎችናx1ሌሎችም ነበሩ፡፡ “እዚህ ያለነው ለምድነው? ለምንም! ፍትሕ የት አለ? ሁሉም መረሸን አለባቸው!”በማለት ፊታቸውን አኮሳትረው ይጮሁ፡፡ አራት ወይም አምስት የሚሆኑ ቀድሞ የፓርቲ አባልየነበሩ በነገሩ ባለስማማታቸው “አሳዛኝ ስሕተት እየተፈጸመ ነው” በማለት ገለጹ፡፡ እንደአበባላቸውከሆነ እየሆነ ያለው ሁሉ እራሱ ስታሊን በማያውቀው በትቂት ሠርጎ-ገቦች በመሞኘት የሚፈጸምመሆኑን ገለጹ፡፡

“የሩስያ ሕዝብ ግማሹ በእስር ቤት ታጉሮ ሳለ ተታለልን! አስተዳዳሪዎቹም እንዲደመሰሱታቀደ!” በማለት አንድ ድምፅ ጮኸ፡፡

ስታሊን አሳምሮ ያውቃል፣ የራሱ ትእዛዝ ነው፣” አለ ሌላዉ፡፡

ስታሊንን በመግደል አሲርሃል ተብሎ የተያዘው ከስረኞቹ አንዱ እጅግ በጣም በመበሳጨቱድምፁ ተቆራረጠ፡፡ ትቂት ቭላስቭትስኪዎች ማነኛውንም ሐሳብና በመቃወም ጮኹ፡፡

“እነዚያ የፓርቲ አባላት መሰቀል ወይም መረሸን አለባቸው!” አለ ሌላ አንድ ሰው፡፡ከ1917 ዓ/ም ጀምሮ ዋና የቮልሼቪክ ፓርቲ አባል የነበረ አንድ ሽማግሌ ሰው በመጀርመንጦር ሠራዊት ውስጥ ካገለገለ ሰው ጋር ተደባደበና በኃይል መሳደብ፡፡

“አንተ ባንዳ ነህ!” ብሎ ጮኸ፡፡ “መረሸን ነበረብህ፣ ነገር ግን በሕይወት እስካሁን አለህ! እኔራሴ እንዳተ ያሉትን ባንዳዎች እረሽናቸዋለሁ ወይም እሰቅላቸዋለሁ፡፡ እስካሁን ድረስ ወደናንተባለመዝቴ አዝናለሁ፡፡ ስሕተትም ፈጽሜያለሁ፣ ይሁን እንጂ አንተ ባንዳዉ በዚህ እስር ቤት ውስጥከኔ ጋር ትሞታለህ ብየ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡

“እኔ ባንዳ ነኝ? እኔ የሶቭየትን መንግሥት ከሚደግፉት አንዱ ነኝ!” “ማለት ትችላለህ፣ ነገር ግን አንተም ባንዳ ነህ፣ ለዚህ ነው መንግሥት እዚህ እስር ቤትያመጣህ፡፡”

በርቀት የነበሩ ሰዎች ሳቁ፣ ሆኖም ግን ክርክሩ በሞቀ ሁኔታ ቀጠለ፡፡ አንድ ሰው ድንገት“አብያተ ክርስቲያናትን አውድመው ሃይማኖትን አጠፉ፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ አንድ ሰው ካጠገቡ ቁጭ(1) ያሉትን አባ አርሴኒን አስታወሰና “ደህና፣ ፒዮትር አንድሬየቪች ንገረን፣ ባለሥልጣናቱን እንዴትታያቸዋለህ?” ሲል ጠየቀ፡፡

አባ አርሴኒ ዝም ብለው ክርክሩን ሲያዳምጡ ቆዩ፣ ነገር ግን አሁን ያለፍላጎታቸው ወደክርክሩ ጎትተው ከተቷቸው፡፡ አባ አርሴኒ ምን እንደሚመልሱ ግልጽ ነበር፡፡ በእስር ቤቱ ውስጥ ብዙየተሰቃዩ ሰው ስለነበሩ የአባ አርሴኒ ጓደኞች ተጨነቁ፡፡

በጂትሎቭስኪ የሚመሩት ቭላስቭትሲዎች ከሌላዉ እስረኛ ራሳቸውን አግለው እየኖሩ ነበር፡፡የሚፈሩት ምንም ነገር አልነበረም፤ በምን ምክንያት እንደተያዙ ያውቃሉ፣ የሕይወታቸው ፍጻሜምቅርብ እንደሆም ይገምታሉ፡፡ ከነርሱ አንዱ “እንግዲህ በል አፍስሰው ቄሴ!” አለ፡፡

አባ አርሴኒ ላፍታ ዝም አሉና “የጦፈ ክርክር ስለያዛችሁ ክርክሩ ወደ ጭቅጭቅ ተቀየረ፣ሊትቆጣጠሩት ወደማትችሉት ደረጃ ደረሰ፡፡ በእስር ቤት መኖር አስቸጋሪ እየሆነ በመምጣቱሁላችንም ፍጻሜያችን ምን እንደሚሆን እናውቃለን፡፡ ክርክሩም መራራ የሆነው ለዚህ ነው፡፡የማይረሸን ወይም በሕይወት የሚተርፍ የለም፡፡ ሁላችሁም ባለሥልጣናቱን፣ ትእዛዛቱንና ሰዎችንትዎነጅላላችሁ፤ ሌላውን ለማስቆጣት ጎትታችሁ ወደ ክርክሩ አስገባችሁኝ፡፡

“ኮሚኒስቶች ምዕመናንን አስረዋል፣ አብያተ ክርስቲያናትን ዘግተዋል፣ ሃይማኖትን ትተዋልብላችኋል፡፡ አዎ፣ ላዩን ሲታይ እውነት ይመስላል፤ ነገር ግን እስቲ በጥልቀት እንመልከተው፣ያለፉትን ጊዜያት በጥልቀት እንመልከት፡፡ ከኛ ከሩስያውያውን ሕዝቦች መካከል ብዙዎቹሃይማኖታቸውን ክደዋል፣ ባለፉት ዘመናት ውስጥ ለነበሩ አባቶች ክብር መሥጠት አቆሙ፡፡በመሆኑም ብዙ መልካምና ብርቅ ነገሮችን አጠናል፡፡ በስሕተት ጎዳና እየሄደ ያለ ማነው?ባለሥልጣናቱ ብቻ ናቸውን? አይደሉም፣ እኛም ራሳችን በስሕተት መንገድ ላይ ነን፣ ስለሆነምአሁን ራሳችን የዘራነውን እያጨድን ነው፡፡

“በምሁራኑ፣ በመኳንንቱ፣ በነጋዴዎችና በሲቪሉ ማኅበረ-ሰብ የተደረጉትን መጥፎምሳሌዎች እናስታውስ፡፡ እኛም በቤተ ክህነቱ ዘርፍ ያለን ሰዎች የበለጠ ክፉዎች ነበርን፡፡“የካህናቱ ልጆች አርቲስቶችና አብዮተኞች ሆኑ፣ የካህናቱ ቤተሰቦች አባቶቻቸው በየምክንያቱበመዋሸታቸው እምነት ስላጡባቸው ካህናቱን ከነሃይማኖታቸው ናቋቸው፡፡ ከአብዮቱ ረጅም ዓመታትአስቀድሞ ካህናቱ ለነፍስ ልጆቻቸው ታማኝ እረኞች አልነበሩም፡፡ ቅስና እንደማነኛውም የሙያ ዘርፍበመቆጠሩ ካህናቱ በሀልወተ-እግዚአብሔር የማያምኑና ከቤተ ክርስቲያን በሚገኘው ገንዘብ እየጠጡየመጠጥ ሱሰኞች ሆኑ፡፡

“ካገራችን ገዳማት መካከል አምስቱ ወይም ስድስቱ የክርስትና ማዕከሎች ነበሩ፤ የቫላምገዳም፣ ኦፕቲና ፑስቲን ከነታዋቂ መምህራኑ/ስተራርትሲx2 ፣ ዲቬዮቭስኪ ኮንቬንትና እንዲሁምየሳሮቭ ገዳም ይገኛሉ፡፡ ሌሎችም ገዳማት አሁን እምነት-አልባ በመሆናቸው የሃይማኖተኛ መነኮሳትመገኛ ሳይሆኑ ተራ የማኅበረ-ሰብ መጠራቀሚያ ሆነዋል፡፡

“አሁን ሰዎች ከነዚህ ገዳማት ምን ይማራሉ? ምን ዓይነት ምሳሌ የሚሆን ነገርስ ተቀመጠ?“ልጆቻችንን በተገቢው መንገድ አላሳደግናቸውም፣ ጠንካራ የእምነት መሠረትአላስቀመጥንላቸውም፡፡ እንግዲህ ይህን ሁሉ ልብ በሉ! ለዚህ ነው ሰዎቻችን ፈጥነው ሁላችንንምየረሱን፣ ካህናቶቻቸውን ረስተዋል፣ እምነታቸውንና ቤተ ክርስቲያናቸውንም በመርሳት ለማፍረስቆርጠው ተነሡ፣ እንዲሁም የጥፋት ዘዴ በመቀመር ካህናቱ የጥፋት መሪዎች ሆኑ፡፡

“ይህን ሁሉ ልብ ካልነው ጣታችንን ወደባለሥልጣኖቻችን ብቻ አንቀስርም፣ ምክንያቱምየእምነት-አልባ ዘሮች ራሳችን ባዘጋጀነው አፈር ላይ ተዘሩ፡፡ ከዚያም እነዚያ ዘሮች ተራቡ፤ እናምመታሰርን፣ መሰቃየትን፣ የንጹሐንን ደም መፍሰስ አቆጠቆጡ፡፡ ይሁን እንጂ በሀገሬ ውስጥ የሆነውሁሉ ቢሆንም ዜጋዋ ነኝ፡፡ ካህን እንደመሆኔ መጠን ሀገራችንን የመጠበቅና የመርዳት ኃላፊነት(2):: እንዳለብን የነፍስ ልጆቼን እመክራለሁ፡፡ አሁን እየተፈጸመ ያለው መቆም አለበት፤ በፍጥነትመስተካከል ያለበት እጅግ ታላቅ ስሕተት ነው፡፡”

“ስለዚህ የኛዉ ቄሴም ኮሚ ሆንሃላ! አለ አንድ ሰው “ኮሚኒስት” የሚለውን ኮሚ ብሎበማሳጠር፡፡ ቅዱስ ትመስላለህ፣ ይሁን እንጂ አንተ በሁለት ቢላዋ የምትበላ አራጆ ነህ፣ ለካስ ቅስቀሳእያካሄድህ ነው! ለባለሥልጣናቱ እየሠራህ ነው!” አለና አባ አርሴኒን በመጥፎ ሁኔታ ገፍትሮከሚከራከረው ሕዝብ መከካከል አስወጣቸው፡፡

ክርክሩ በጦፈ ሁኔታ ቀጠለ፣ ነገር ግን ብዙ ሰዎች ቡድኑን እየተውት ወጡ፡፡

ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ትቂት እስረኞች አባ አርሴኒን መበቀል ጀመሩ፡፡ በምሸት ደበደቧቸው፣አንድ ሰው ባልጋቸው ላይ የፊኛዉን ፈሳሽ ለቀቀባቸው፣ ሌላዉም ደግሞ መቁኑናቸውንሠረቃቸው፡፡ እኛ የርሳቸው ጓደኞቻቸው ደግሞ ካጥቂዎቻቸው ለመታግ ሞከርን፡፡ ሆኖም ግን አጥቂቡድኖቹ አመለ-ብልሹዎች ስለነበሩ ማነኛውንም ጉዳት የማድረስ አቅሙ ነበራቸው፡፡ባንድ ምሸት ጆራ ግሪጎሬንኮ የሚባል ከኪየቭ የመጣ ሰው አባ አርሴኒን የቭላሶቭቲዎች መሪወደ ሆነው ጂሎቭስኪ ወሰዳቸው፣ ጂሎቭስኪ ካልጋዉ ላይ ተጋድሞ ከጓደኞቹ ጋር እያወራ ነበር፡፡“ቄሴ፣ ከኛ ወገን ነህን ወይስ ከኮሚኒስቶች? ለእስር ቤቱ ባለሥልጣናት እየሠራህ መሆኑንደርሰንብሃል፣ ኑዛዜ ትቀበልና አሳልፈህ ለነሱ ትሠጣለህ፡፡ አሁን ምን እንደምናደርግህ እኛ ብቻ ነንየምናውቅ፣ ትምህርት ሊሆንህ የሚችል ምት እንመታሃለን፡፡ እንሂድ ጆራ! በቅድሚያ ግን ቄሴየሚለውን እንስማ፡፡”

ጆራ ግሪጎሬንኮ በሁሉም ሰው ዘንድ የተጠላ ነበር፡፡ አጭር፣ ወፍራምና ትክሻዉ ሰፋ በማለቱአንገት የሌለው ይመስላል፣ ፊቱ ጠባሳ ስለበዛበት መልከ-ጥፉ ሲሆን በሆነ ባልሆነው የሐሰትፈገግታ ፈገግ ይላል፡፡ ይህ ተዳምሮ ሰውየውን አስቀያሚ አድርጎታል፡፡ ምንም እንኳን የቭላሶቭአባል በመሆኑ ብቻ በእስር ቤቱ ውስጥ ቢገኝም በጀርመን ሠራዊት ውስጥ በመረሸን ተግባር ላይየተሳተፈ ነው የሚል የሐሜት ወሬ ይወራበታል፡፡ አባ አርሴኒ በዕርጋታ ወደጂትሎቭስኪተመለከቱና “በሰዎች ሕይወት ላይ መወሰን የሚችለው እግዚአብሔር ብቻ ነው፤ አንተ አይደለህም፡፡የአንተ ቡድን አባል አልሆንም፣” አሉት፡፡ ከዚያም ከጂትሎቭኪ በተቃራኒ ካልጋው ላይ ቁጭ አሉና“ልታስፈራራኝ አትሞክር፡፡ ለኡኡታ፣ ለድብደባና ለሞት ዛቻ ቤተሰቡ ነኝ፡፡ በዚህ ዓለም ላይየምኖረውን ጊዜና የእያንዳንዳችንን ዕድሜ በሚወስን በእግዚአብሔር ያለምንም ቅድመ-ሁኔታአምናለሁ፡፡ የምሞትበት ጊዜ አሁን ከሆነ የእግዚአብሔር ፈቃድ ነው፡፡ እኔም ሆንሁ አንተ ይህንመለወጥ አንችልም፡፡ ሁላችንም እንደሥራችን ሊፈረድብን ወደእግዚአብሔር ፍርድ መቅረባችንአይቀርም፡፡

“በእግዚአብሔርና በደጋግ ሰዎች መልካም ሥራ አምናለሁ፣ እስከመጨረሻዋ እስትንፋሴድረስ በዕርግጥም አምናለሁ፡፡ አንተስ? አምላክህ የት አለ? እምነትህስ የት አለ? ስለሚሳደዱትአሳዳጆች ብዙ ትናገራለህ፣ ነገር ግን እስካሁን ራስህ እያሳደድህ ነው፣ እያዋረድህና እየገደልህ ነው፡፡እጆችህን ተመልከት፣ በደም ተጨማልቀዋል!”

ጂትሎቭስኪ እጆቹን አነሣና በተለየ ሁኔታ አተኩሮ አያቸው፤ ከዚያም ወደአባ አርሴኒተመለከተ፡፡ እጆቹን ከጭኑ ላይ አሳረፋቸውና በጣቶቹ ሲጥጥ የሚል ድምፅ በፍጠር “ስለማላውቀውማነኛውም ነገር ለመናገር አትሞክር!” አለና አባ አርሴኒን እንደገና በጥልቀት ተመለከታቸው፡፡ግሪጎሬንኮ ከላይኛው ተደራቢ አልጋ ላይ ሆኖ “አርካዲ ሴሚዮኖቪች፣ ቄሴ በሃይማኖት በዐልየሚያስተምር ሰው ይመስላል፤ ለምን አሁን ገድለን አንገላገልም?” በማለት በብስጭት ተናገረ፡፡

“ዝም በል፣ ግሪንጎሬንኮ!” ሲለው መለሰና ጂትሎቭስኪ “ወደውስጥ ከማስገባታችን በፊትየሚለውን ሁሉ ይበል፡፡ ቄሶች ማነብነብ ሥራቸው ነው፣ ልክ እንደኮሞኒስት ካድሮዎች፣” አለ፡፡

አባ አርሴኒ ቀጠሉ፤ “አንድ ሰው አንድ ቀን አንተን ሃይማኖተኛ ነበረ አለኝ፣ ግን ለምንታምናለህ? ሰዎችን አሰቃይተህ የገደልህ በማን ስም ነው? ስለዶስቶቭስኪ--ስትናገር አስታውሳለሁ፣በጣም የምትወደው ደራሲና የሩስያውያን ነፍስ መሆኑን ተናግረሃል፤ “ዘ-ብራጊስ ካራማዞቭ”በተሰኘው መጽሐፉ የዞሲማን ቃለ-ምክር እጠቅሳለሁ፡፡ ከመሞቻ አልጋዉ ላይ ሆኖ በዙሪያዉከበውት ለነበሩ ሰዎች እንዲህ አለ፤ “ከሀድያንን፣ ክፋት የሚያስተምሩትን፣ ማቴሪያሊስቶችንናክፉዎችንም ሳይቀር አትጥሏቸው፣ ምክንያቱም ከእነርሱ መካከልም ትቂቶቹ በእውነት ርኅሩኆችአሉና፣ በተለይ ደግሞ በዘመናችን፡፡ የእግዚአብሔርን ሰዎች ውደዱ፡፡ እመኑና ታላቅ የእምነት ደረጃይኑራችሁ፡፡ ለሁሉም ሰዎች መልካም ሥሩ፣ ስቃዮቻቸውን በመሸከም ዕርዷቸው፡፡ እያንዳንዱ ሰውስለሕይወት እንደገና እንዲያስብና ስህተቱንም እንዲያርም ጊዜ አለው፣ ይህን ማድረግም ይገባዋል፡፡ይህን ከተናገሩ በኋላ አባ አርሴኒ ተነስተው ወደአልጋቸው አመሩ፡፡ ነገር ግን ግሪጎሬንኮከአልጋዉ ላይ ዘለለና አባ አርሴኒን አንገታቸውን አነቃቸው፡፡ በዚያ ቅጽበት በተሰበሰቡት ሰዎችመካከል አንድ ረጅምና ጠንካራ ሰውየ እየተጎማለለ ብቅ አለ፣ ይህ ሰው በእስር ቤቱ ውስጥ“መርከበኛዉ” በሚል ስም ይታወቃል፡፡ ኦዴሳ ላይ በፖለቲካ ምክንያት ተይዞ ለአስራ-አምስትዓመታት በዚህ እስር ቤት ውስጥ እንዲቆይ እስከተፈረደበት ጊዜ ድረስ በእርግትም መርከበኛ ነበር፡፡”ግዴለሽ፣ ደስተኛና ጥሩ ጀግና ሰው ነበር፣ እንደማናችንም በእስር ቤት ቢቆይም ጤናማ የሰውነትአቋሙን እንዳለ ነበር፡፡

መርከበኛዉን ከበው የሚመለከቱትን ሰዎች እየገፈተረ መጣና ግሪጎሬንኮን ያለማመንታትአነሣና በዕቃ እንደተሞላ ጆንያ ወደጂትሎቭስኪ ቡድን አባላት ወረወረው፡፡

“ስማ አንተ ምናምን! አሁን ሩስያ ውስጥ እንጂ ጀርመን ውስጥ አለመሆንህን ልታውቅይገባል!” አለና ወደጂትሎቭስኪ ዞሮ ያለማመንታት በኦዴስያኛ የአነጋገር ዘይቤ “የኔ ክቡር ሆይ፣ጓደኞችህን ፀጥ ብታሰኛቸው ይበጃሃል! ያለበለዚያ ማንቁርታችሁን እዘጋዋለሁ፡፡ ሁላችሁም ፀጥበሉ!”

የጂትሎቭስኪ ቡድን አባላት ተንቀጠቀጡ፤ ብዙ እስረኞችም መጡና አባ አርሴኒንናመርከበኛዉን ለማገዝ በተጠንቀቅ ቆሙ፡፡

መርከበኛዉ ወደግሪጎሬንኮ መጣና “ፒዮትር አንድሬየቪችን መንካት አትችልም! አንድ ነገር ቢሆኑእኔ በግሌ ስለእርሳቸው እገድላሃለሁ፣ ከመግደሌ በፊት ስስ ብልትህን መትቼ በመጣልእጫወትብሃለሁ፣” አለው፡፡ ከዚያም አባ አርሴኒን ጠራቸውና “ፒዮትር አንድሬቪች፣ እንሂድ! አሁንአስጨንቀናቸዋል፡፡ ለእርስዎ የተለየ አክብሮት አለኝ፡፡ በሰላም ደግመን እንደምንገናኝ ተስፋአደርጋለሁ፡፡”

በሦስት ሳምንታት ውስጥ ጆራ ግሪጎሬንኮ ወደሌላ እስር ቤት ተዛወረ፡፡ ከዚያ ጊዜ ጀምሮጂትሎቭስኪዎች ፀጥ አሉ፣ ለሰዎችም ከበሬታ ማሳየት ጀመሩ፡፡ ክርክሩ ግን እንደቀጠለ ነበር፣ አባአርሴኒ ግን ከዚያ ጊዜ ጀመሮ በክርክር መሳተፋቸውን አቆሙ፡፡

(1)  ቭላሶቨትስ በጄነራል ቭላሶቭ ስር ይታዘዙ የነበሩ ሩስያውያውን ወታደሮች ሲሆኑ ከውጭ ሆነው ኮሚኒዝምን ለመዋጋትከጀርመን ጦር ሠራዊት ጋር ተቀላቀሉ፡፡ ጦርነቱ በጀርመኖች ተሸናፊነት በመደምደሙ በመጨረሻ በጦር ቃል-ኪዳን ተባባሪሀገራት ወደሩስያ እንዲመለሱ ተደረገና ከሞላ-ጎደል ሁሉም ሲሰቀሉ የቀሩት ደግሞ ወደልዩ የሞት ካምፕ ተላኩ፡፡


(2) ስተራርትስ “ስታሬትዝ” ለሚለው ቃል የብዙ ቁጥር ሲሆን ትርጉሙ ሰዎች ሃይማኖታዊ ምክር ለማግኘት የሚሄዱበትታዋቂ መምህር ማለት ነው፡፡ የኦፕቲና ገዳም እንደነዚህ ዐይነት መምህራንን በማፍራት የታወቀ ነው፡፡ 

Friday, 30 September 2016

ጥፋት አለብኝ ብዬ ካላመንኩኝ «ወያኔ» ነኝ!

2009/1/19 ዓ.ም. (2016/9/29)

ከዲያስፖራ እየኖርኩኝ ስጋዊ ምቾቴን አጠናቅቄ ህሊናዬ እየወቀሰኝ ሀገር ቤት ያሉትን ወንድሞች እህቶቼን ታገሉ እላለሁ። ሀግሬን እወዳለሁ እላለውንጂ ያሳደገችኝ ብትሆንም ለሷ ያለኝን ሃላፊነት ከተውኩኝ ቆይቻለሁ። ክጃታለሁ ጥያታለሁም። ሆኖም ግን ሀገሬን መበደሌ አይታየኝም። ስለሌሎችን ኅጢአትና በደል እጮሀለው እንጂ። ከአይኔ ያለውን ግንድ አላየውም የሌላውን ጉድፍ ብቻ ነው የሚታዬኝ።

ምሬቴ ትንሽ በመሆኗ ምክንያት አጥሬን መግፋት መብቴ ነው እላለሁ! ገፈዋለሁ፤ ከጎረቤት ጋርም እጣላለሁ፤ መንገድንም አጠባለሁ። ለሰፈሩ ችግር እያመጣሁኝ ነው። ግን የእለት ወሬዬ ስለ ቀበሌአችን ሹማምንት የምስና ባህሪ ነው። አይኔ ውስጥ ግንድ የለም።

እውነት ነው፤ ሲያስፈልግ ጉቦ ሰጣለሁ። መብቴን ለማስከበር ብቻ ሳይሆን የማይገባኝን ለማግኘትም። ምን ይደረግ፤ የሀገራችን እውነታ ነው ብዬ እራሴን አታልላለው። ግን መሪዎቻችን እንዴት ሞራል ቢስ ናቸው ብዬ አማርራለሁ።

አንዱ የኦርቶኦክስ መሰረታዊ እምነት ሁላችንም ለሁሉም ሰው ኅጢአት በተወሰነ ደረጃ አስተዋጾ እድርገናልና ሃላፊነት አለብን የሚል ነው። ኅጢአቶቻችን የተገናኙም የተወራረሱም ናቸው። ይህንን ለማብራራት ያህል የታወቀው ሩሲያዊ ደራሲ ፊኦዶር ዶስቶኤቭስኪ በ«ካራማዞቭ ወንድማማቾች» የጻፈውን ጥቅስ እንመልከት። ታላቁ የሃይማኖት አባት ዞሲማ ልጆቻቸውን ሲመክሩ እንደዚህ አሉ፤
«አንድ ሰው በዚህ ዓለም ከሚኖሩት በሙሉ የባሰ ኅጢአተኛ እንደሆነ ሲያምን፤ በተጨማሪም ከሁሉም ሕዝብ ፊት ጥፋተኛ እንደሆነ...፤ ለዓለምም ለያንዳንዱ ሰውንም ኅጢአት እና ጥፋት እንዳለበት ስያምን ነው የ(ክርስቲያናዊ) አንድነት ድላችንን ማስመዝገብ የምንችለው..።
«ሁላችሁም ልባችሁን በደምብ አዳምጡና ለራሳችሁ ሳትሰለቹ ንስሐ ግቡ። እስከ ተጸጸታችሁ ድረስ ኅጢአታችሁ የጎላ ቢመስላችሁም አትፍሩት...።
«በጸሎታችሁ እንደዚህ አስታውሷቸው፤ «አምላካችን ሆይ የሚጸልይላቸው የሌሏቸውንም ላንተ መጸለይ የማይፈልጉትንም አድናቸው» ብላችሁ ጸልዩ። እንደዚህም ቀጥሉ «አምላኬ ሆይ እኔ ከሁሉም የባሰ ርኩስ ነኛ፤...»»
በተጨማሪ ባለፈው ጽሁፌ የጠቀስኩት በጾቪዬት እስር ቤት የተሰቃዩት አለክሻንደር ሶልዠኒትሲን ከእስር ቤት ሆነው የጻፉትን እንደገና ልጥቀስ፤

ከእስርቤታችን አልጋ የሆነው የበሰበሰው ገለባ ላይ ጋደም ብዬ ነው ለመጀመርያ ከውስጤ የበጎ መንፈስ የተሰማኝ። ቀስ በቀስ መረዳት የጀመርኩት ይህ ነው፤ ጥሩና ክፉን የሚለየው መስመር በሀገሮች፤ መደቦች፤ የፖለቲካ ፓርቲዎችም መካከል አይደለም የሚያልፈው፤ ይህ መስመር የሚያልፈው በያንዳንዱ የሰው ልብ መኻል ነው። መስመሩ እድሜአችን በሙሉ ከውስጣችን ወደፊት ወደኋላ ይላል። በክፉ የተሞሉ ልቦችም ቢያንስ ቅንጣት ያህል ጥሩነት ይኖራል፤ ከሁሉም ጥሩ ከሚባለውም ልብ ከአንድ ጥጓ ትንሽ ክፉነት ይኖራል።
«በየቦታው እየዞሩ ያሉ ክፉ ስራ የሚሰሩ ክፉ ሰዎች ቢኖሩና እነሱን ከኛ መለየትና ማጥፋት ብቻ ቢሆን ኖሮ እንዴት ቀላል ነበር? ግን ጥሩና ክፉን የሚለየው መስመር ከያንዳንዱ የሰው ልጅ ልብ መካከል ነው የሚያልፈውና ማን አለ ከራሱ ልብ ቁራጭ ቆርጦ ለማጥፋት ፈቃደኛ ይሆነ?»
ሶልዠኒትሲን በመታሰራቸው፤ በእስር ቤት ለደረሰባቸው በደልና ስቃይ፤ ያሰሯቸውን የዘመኑን መንግስት መሪዎች፤ የፍርድ ቤት ዳኞች፤ የደህንነት አዛዦች፤ ወዘተ ብቸኛ ጥፋተኛ አድርገው ሊቆትሩ ይችሉ ነበር። ማንናችንም ደካሞች በሳቸው ቦታ ብንሆን እንደዛ ነበር የምናስበው።

ግን እየተሰቃዩም ቢሆን ይህን ቀላሉ የውሸት መንገድን ከመከተል እውነትን መረጡ። እውነትን ፈለገው ህሊናቸውን ተጠንቅቀው መርምረው የራሳቸውም ግድፈት እንዳለ ተገነዘቡ። ከነዛ ክፉዎች እንደማይሻሉ አመኑ።

ሶልዠኒትሲን በሁለተኛ ዓለም ጦርነት ጀግና ወትደር ነበሩ። ሀገሬን እንደዚህ አገልግዬ እንዴት በማግስቱ ለማይረባ ምክንያት እታሰራለሁ ነበር በመጀመርያ ያሰቡት። ግን ህሊናቸውን ሲመረምሩ ከጦር ሜዳ የሰሩትንና ሲሰራ አይተው ዝም ያሉትን ግፍ አስታወሱ። ሀገርን በመከላከል አሳበው ህሊናቸውን እንዴት እንደሸጡ አስተዋሉ። አብረዋቸው የታሰሩትንን የመንግስት ሰለቦች ሲመለከቱም ምንም ንጹ የሚመስሉትም በተወሰነ ደረጋ ተመሳሳይ የህሊና ሽያጭ እንዳካሄዱ ተገነዘቡ።

ከዝ ቀጥሎ የበደሏቸውን ሲመለከቱ በፊት የነበራቸው እነሱ ክፉ እኔ ንጹ የሚለው አስተሳሰባቸው ውሸት እንደሆነ ገባቸው። በዳዮቻቸውም እንደራሳቸው በተለላየ አታላይና የማይረባ ምክንያት ህሊናቸውን ሽተዋል። ስንቱ ናቸው በስመ ሀገር ወዳድነት እንደ ሶልዠኒትሲን አይነቱን የሀገር ከሃዲ ብለው ያሳሰሩት። እነዚህ «እውነት አማኞች» ርዕዮት ዓለማቸውን እንደ ሃይማኖት አድረገው የሚያምኑበት ስለሱ ምንም ለማድረግ ወደኋላ አይሉም ነበር። ሶልዠኒትሲን እነሱን ሲያዩ እራሳቸውን አዩ።

የመጨረሻ ግንዛቤአቸው ንስሃ መግባት እንዳለባቸው ነበር። ንስሃ ቢገቡ በራሳቸው ብቻ ሳይሆን በባልደረቦቻቸው በሙሉ የደረሰው እንደማይደርስ ገባቸው። በሶቪዬት ህብረት የሚገኙት ሀገራት በሙሉም ሰላምና እውነታዊ መንግስት ሊያገኙ የሚችሉት በዚህ አይነት መንገድ ብቻ እንደሆነ ተገነዘቡ። ሌሎቻችንም እንደዚህ አድርገን እንድናስብ ጋበዙን።

እሺ፤ የምጨረሻ ጥቅስ ከአባ ዶሮቴዎስ፤
«አንድ ሰው በእግዚአብሔርን ፊት እራሱን በደምብ ቢመረመረ ለሚደርስበት ያለው በደል ባተግባር፤ በሃሳብ፤ በንግግር፤ በፀባይ፤ ወይም በባህሪይ ሃላፊነት እንዳለበትና ከፊል ተጠቅያቂ እንደሆነ ይገለጽለታል።»
እንዲሁም ለኢትዮጵያ ችግሮች ሁሉ፤ የፖለቲካ ችግር ተጨምሮ፤ ሁላችንም ኢትዮጵያኖች አስተዋጾ አድርገናል ሃላፊነትም አለብን ብለን ማመን አለብን። ቀጥሎ ይህን ሃላፊነት ብንወታው ችግሩ ይፈታል ብለን ማመን አለብን። አባ ዶሮቴዎስ እንዳሉት እራሳችንን ተጠንቅቀን በኢግዚአብሔር ፊት እንመርምር። ይህ ወደ ሰላምና እውነት ብጨኛው መንገድ ነው።