ሃብታሙ አያሌው እንዳለው ፍትህ መታየቱ ጥሩ ነው። ሆኖም ለበረከትም፤ ለቤተሰቦቹም፤ ለኢትዮጵያም አዝናለሁ።
እንደ ኢትዮጵያዊ አፍራለሁ። እንደ ሀገር እንደ በረከት፤ ታደሰ፤ አዲሱ፤ መለስ ወዘተ አይነት አስተሳሰብ ያላቸውን ሰዎችን ማፍራታችን ያሳፍራል። መቶ እጥፍ የሚያሳፍረው ግን እንደዚህ አይነት አስተሳሰብ ያላቸው ሰዎችን መሪዎቻችን እንዲሆኑ መፍቀዳችን ነው።
ሌላ ላይ መፍረድ ቀላል ነው ግን ልክ አይደለም አዋጪም አይደለም። ሃላፊነት የወሰደ ብቻ ነው ህይወቱን በትክክል መምራት የሚችለው። እኛም እንደ ኢትዮጵያዊያን በነ በረከት መኖር እና ስልጣን መያዝ ሃላፊነት መውሰድ አለብን። በተለይም የፖለቲካ መደባችን ከጃንሆይ ዘመን ጀምሮ ያደረግነው ተደጋጋሚ ጥፋቶችን አይተን፤ አምነን፤ ህፍረታችንን አምነን፤ ተቀብለን፤ ንስሃ መግባት አለብን።
ከበረከት ስመዖን መማር የሚገባኝ ይህ ነው ብዬ አምናለሁ።
የሰላም ክፍሌ ይትባረክ ብሎግ፤ ስለ ሀገራችን ኢትዮጵያ ያለኝን ትናንሽ ሀሳቦች በትህትና አቀርባለሁ። ለስሕተቶቼም በቅድሚያ ይቅርታ እጠይቃለሁ
Showing posts with label personal responsibility. Show all posts
Showing posts with label personal responsibility. Show all posts
Thursday, 24 January 2019
Thursday, 1 February 2018
Short Memories!
Some of us seem surprised at comments by a certain political commentator, Muluwerq Kidanemariam, that given the current political atmosphere, Tigray Region might find it necessary to invoke article 39 of the constitution and exit Ethiopia. But given the history of the TPLF, such comments are nothing unusual and nothing to be alarmed about.
It seems that many have forgotten, or were too young to remember, the TPLF and EPRDF of the 1990's, particularly until the 2000 Ethio-Eritrean War. This was the peak of ethnic nationalism and anti-Ethiopian nationalist rhetoric in Ethiopia, sponsored and encouraged by the TPLF and EPRDF. TPLF supporters, arm in arm with their EPLF comrades, gleefully lorded it over us 'chauvinists'. It was de rigueur for EPRDF members and supporters to identify with their ethnicity first, and Ethiopia second, and reluctantly at that. Often us naïve and shell-shocked Ethiopian nationalists would during the course of a discussion ask a TPLF or OPDO/OLF supporter if they consider themselves Ethiopian, and the defiant answer would be that they are Tigrean or Oromo first, and then Ethiopian (maybe)!
EPRDF officials and supporters would often say that if by some improbable tragedy the TPLF/EPRDF would fall from power and the 'chauvinists' replace them, they would promptly exit Ethiopia. Their 'Ethiopianness' hung on a thread. This was the tone of Ethiopian politics during the 1990's, and this is merely what Ato Muluwerq has repeated in his interview. Nothing new!
During the Ethio-Eritrean war, things changed a little. The departure of EPLF officials and supporters from Ethiopian political circles resulted in a lowering of anti-Ethiopianism in Addis Ababa. In addition, the war effort required the EPRDF to mobilize a good degree of patriotism - Ethiopian patriotism - all around Ethiopia, even in Oromia, the region that the EPRDF claimed was most victimized by Ethiopian nationalism. The EPRDF were very pragmatic - they did what they needed to do to achieve their goal which was, via war, saving face over the EPLF. So pragmatic were they that they recruited former military officers of their arch-enemy Dergue into the Ethiopian military for the fight!
After the war, and leading up to the 2005 elections, the EPRDF began to shift from fervent anti-Ethiopian nationalism to a little more centrist position. Its anti-chauvinist rhetoric began to be accompanied by anti-'narrow nationalist' rhetoric. Eventually, driven by a more flexible Meles Zenawi, the EPRDF even tried the open 2005 elections, leaving itself vulnerable to the feared and hated chauvinist political forces. When the course of the elections did not go as planned, Meles reverted to form and raised the specter of anti-Tigrayan violence and even talked about genocide! Again, this is what we are seeing now - again, many TPLF supporters are interpreting the threat to the monopoly that the TPLF/EPRDF has on political power as an anti-Tigrayan pogrom!
After crushing the 2005 anti-government movement - with indispensable help from the opposition I might add - the ERPDF moved quickly to an agenda of political monopoly through economic growth - the China/East Asia 'developmental state' model. In the Ethiopian context, the EPRDF named this model 'lmatawi mengst'. The EPRDF figured that a focus on development would make the people forget about politics and, just as importantly, ethnicity. The developmental state was a bargain with the Ethiopian people - high economic growth in exchange for monopoly political power - and it was a great success for the EPRDF. Far more successful than it would have ever imagined. Any political opposition was squashed with impunity, but we, the masses, generally acquiesced, was we were to busy making money - or trying to.
During this time, the EPRDF continued moving slowly away from ethnic nationalism. The rhetoric about Tigrawi-first, Ethiopian-second became a distant memory. Instead, members and supporters of the EPRDF began to portray themselves as being 'more Ethiopian' than their opponents, including the 'chauvinists'! The term 'chauvinist' itself became passé in EPRDF circles, and was replaced by terrorists and anti-Ethiopians! What a change from the old days!
However, with time, the developmental state began to display its own problems. As elsewhere, for example China, the masses began to express intense dissatisfaction with the corruption of the ruling party and the resulting lack of civic and economic justice. This is a significant problem in and of itself. But in Ethiopia, it has been increased orders of magnitude because of ethnic nationalism. Because of ethnic nationalism, this dissatisfaction is expressed not just in civic terms, but ethnic terms, and as we all know, any conflict is greatly increased if ethnicity becomes a factor.
So now, the TPLF and its supporters see themselves faced with an existential crisis, and they don't seem to have anyone to help them figure out an innovative solution. So they retreat into old theories and clichés of their childhood, such as what Ato Muluwerq talks about in his interview.
This is not surprising, neither should it be alarming. But it is folly to expect the TPLF, a small partner in the EPRDF, to continue to manufacture solutions - good or bad - to Ethiopian political problems. Inevitably, they will reach a state of exhaustion - they might even be there now. Their never ending yearning for Meles, who had a way of assessing and finding a way out of problems, shows this. They should be relieved of this huge burden that we have saddled them with for decades. By 'we', I mean the general political opposition, especially those who consider ourselves Ethiopian nationalists. It is we who have failed the nation, and even though we have severely debilitated ourselves, we have no choice but to somehow grow up and do our fair share.
So let us not worry about the Ato Muluwerq's of this world. They are at their wits end, and for this I don't blame them. It us up to us to find a way out of this quagmire.
It seems that many have forgotten, or were too young to remember, the TPLF and EPRDF of the 1990's, particularly until the 2000 Ethio-Eritrean War. This was the peak of ethnic nationalism and anti-Ethiopian nationalist rhetoric in Ethiopia, sponsored and encouraged by the TPLF and EPRDF. TPLF supporters, arm in arm with their EPLF comrades, gleefully lorded it over us 'chauvinists'. It was de rigueur for EPRDF members and supporters to identify with their ethnicity first, and Ethiopia second, and reluctantly at that. Often us naïve and shell-shocked Ethiopian nationalists would during the course of a discussion ask a TPLF or OPDO/OLF supporter if they consider themselves Ethiopian, and the defiant answer would be that they are Tigrean or Oromo first, and then Ethiopian (maybe)!
EPRDF officials and supporters would often say that if by some improbable tragedy the TPLF/EPRDF would fall from power and the 'chauvinists' replace them, they would promptly exit Ethiopia. Their 'Ethiopianness' hung on a thread. This was the tone of Ethiopian politics during the 1990's, and this is merely what Ato Muluwerq has repeated in his interview. Nothing new!
During the Ethio-Eritrean war, things changed a little. The departure of EPLF officials and supporters from Ethiopian political circles resulted in a lowering of anti-Ethiopianism in Addis Ababa. In addition, the war effort required the EPRDF to mobilize a good degree of patriotism - Ethiopian patriotism - all around Ethiopia, even in Oromia, the region that the EPRDF claimed was most victimized by Ethiopian nationalism. The EPRDF were very pragmatic - they did what they needed to do to achieve their goal which was, via war, saving face over the EPLF. So pragmatic were they that they recruited former military officers of their arch-enemy Dergue into the Ethiopian military for the fight!
After the war, and leading up to the 2005 elections, the EPRDF began to shift from fervent anti-Ethiopian nationalism to a little more centrist position. Its anti-chauvinist rhetoric began to be accompanied by anti-'narrow nationalist' rhetoric. Eventually, driven by a more flexible Meles Zenawi, the EPRDF even tried the open 2005 elections, leaving itself vulnerable to the feared and hated chauvinist political forces. When the course of the elections did not go as planned, Meles reverted to form and raised the specter of anti-Tigrayan violence and even talked about genocide! Again, this is what we are seeing now - again, many TPLF supporters are interpreting the threat to the monopoly that the TPLF/EPRDF has on political power as an anti-Tigrayan pogrom!
After crushing the 2005 anti-government movement - with indispensable help from the opposition I might add - the ERPDF moved quickly to an agenda of political monopoly through economic growth - the China/East Asia 'developmental state' model. In the Ethiopian context, the EPRDF named this model 'lmatawi mengst'. The EPRDF figured that a focus on development would make the people forget about politics and, just as importantly, ethnicity. The developmental state was a bargain with the Ethiopian people - high economic growth in exchange for monopoly political power - and it was a great success for the EPRDF. Far more successful than it would have ever imagined. Any political opposition was squashed with impunity, but we, the masses, generally acquiesced, was we were to busy making money - or trying to.
During this time, the EPRDF continued moving slowly away from ethnic nationalism. The rhetoric about Tigrawi-first, Ethiopian-second became a distant memory. Instead, members and supporters of the EPRDF began to portray themselves as being 'more Ethiopian' than their opponents, including the 'chauvinists'! The term 'chauvinist' itself became passé in EPRDF circles, and was replaced by terrorists and anti-Ethiopians! What a change from the old days!
However, with time, the developmental state began to display its own problems. As elsewhere, for example China, the masses began to express intense dissatisfaction with the corruption of the ruling party and the resulting lack of civic and economic justice. This is a significant problem in and of itself. But in Ethiopia, it has been increased orders of magnitude because of ethnic nationalism. Because of ethnic nationalism, this dissatisfaction is expressed not just in civic terms, but ethnic terms, and as we all know, any conflict is greatly increased if ethnicity becomes a factor.
So now, the TPLF and its supporters see themselves faced with an existential crisis, and they don't seem to have anyone to help them figure out an innovative solution. So they retreat into old theories and clichés of their childhood, such as what Ato Muluwerq talks about in his interview.
This is not surprising, neither should it be alarming. But it is folly to expect the TPLF, a small partner in the EPRDF, to continue to manufacture solutions - good or bad - to Ethiopian political problems. Inevitably, they will reach a state of exhaustion - they might even be there now. Their never ending yearning for Meles, who had a way of assessing and finding a way out of problems, shows this. They should be relieved of this huge burden that we have saddled them with for decades. By 'we', I mean the general political opposition, especially those who consider ourselves Ethiopian nationalists. It is we who have failed the nation, and even though we have severely debilitated ourselves, we have no choice but to somehow grow up and do our fair share.
So let us not worry about the Ato Muluwerq's of this world. They are at their wits end, and for this I don't blame them. It us up to us to find a way out of this quagmire.
Thursday, 5 October 2017
ኢሳት፤ ተስፋ የሚሰጥ ወይም የሚያስቆጥ?
ይህን ቪዲዮ (https://www.youtube.com/watch?v=OUGKE49Lagg) ይመልከቱ። እኔ እጅግ ከምወዳቸው ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና ስለ ኦህዴድና በአዴን ለህወሃት ሙሉ ተገዥነት ይተቻል። ቪዲዮውን ካያችሁ በኋላ እስቲ ንገሩኝ፤ ስለሀገራችን ኢትዮጵያ በተስፋ ተሞላችሁ ወይም ቆረጣችሁ? ይህ ለናንተም ለሃገሪቷም ይበጃል አይበጅም? የፖለቲካ ለውጥ ለዘላለም አይመጣም ወይም አንድ ቀን ይመጣል ያሰኛችኋል? ከዚም አልፎ በሀገሬ ለውጥ ለማምጣት ሚና መጫወት እችላለሁ አልችልም፤ የትኛው ስሜት ይይላል?
ከዚህ በፊት ደጋግሜ እንደጻፍኩት፤
1. የትግራይ ተወላጆች በምክላከያ አናሳ ቁጥር ነው ያላቸው። የሌሎች ጎሳ ተወላጆች ከነኦሮሞና አማራ እጅግ አብዛኛው ናቸው። ይህ ሃቅ ነው። ህወሃትም ፍልጎት ሳይሆን ምርጫ የለውም፤ ትግሬ ቢበዛ ለውግያም ለሰላምም አይበጅም። ስለዚህ ትግሬዎች የስልጣን ቦታዎኦች ተቆጣጥረው ሌሎቹ ሌላውን ይዘዋል። ግን ይህ ሁኔታ ለርጅም ጊዜ አይዘልቅም። ሌሎቹ ወደፊት ግድ ሹመት ያገኛሉ ሰላምን ለመጠበቅ።
2. የደህንነቶ የጎሳ ክፍፍል በዪፋ ባይታወቅም ከሸፈቱ ምስክሮች ዘንድ በርካታ ቲግራይ ያልሆኑ ደህንነት ውስጥ እንዳሉ መረጃ አለን። ሆኖም ከሁሉም የመንግስት አካል ደህንነት ነው በህወሃት ታንቆ የተያዘው። ማንኛውም አምባገነን መንግስት ከሁሉም በላይ ደህንነትን ነው ተጠንቅቆ የሚይዘውና።
3. የትግራይ ህብረተሰብ አሁንም የኢትዮጵያ 8% በላይ አይደለም።
እነዚህ ሃቆች የሚነግሩን ህውሃት ኢትዮጵያን የሚገዛት በበርካታ ህዝብ ፈቃድና ተባባሪነት ነው። ግን በዛው መጠን ፈቃደኛውም ተባባሪውም በሙሉ ልቡ አምኖበት ሳይሆን በአቅም፤ በብስለት፤ በመተባብር፤ ወዘተ ጉድለት ነው የሚያደርኩትን የሚያደርጉት። አቅም፤ ብስለት፤ ትብብር በትንሹም ቢጨእር ያለው አገዛዝ በሰላም ይዘየር ነበር። ስለዚህ ይህ ሁኔታ እንዲፈጥር ነው ማድረግ ያለብን።
ለዚህ ነው ከዚህ በፊትም አሁንም የምለው ከነ የሩሲያ ቭላዲሚር ፑቲን አይነቱ እንማር። ፑቲን ከጎጀውን ከሀዲው የልትሲን መንግስት እየሰራ ውስጥ ለወስጥ ጥሩ ስራ እየሰራ ግን ማንነቱን ደብቆ ሃይሉን አከማቸ። ተቃዋሚ አልሆንም። ለምን፤ እንደማያዋጣና እንደምይሆን ገቡንም ለማሳካት እንደማይሆን ተረድቶ ከመንግስት ውስት በስውር መስራቱ ያዋጣልብሎ ሰራ። የሱም ቢጤዎች ብዙ ነበሩ ጉብዝናና ብልጥነታቸውም እንዲአሸንፉ ረዳቸው።
የኢትዮጵያም ሁኔታ እንደዚህ ነው። በደርግ ጊዜ ታላቅ የሆነ የግዥ መደብ ሞተ እራሱንም አጠፋ አቅምም አጣ። አሁን ያለው አማራጭ ከውስጥ ሆኖ መስራት ነው።
ደግሞ ይቻላል። ከላይ እንደጠቀስኩት ህውሃትም ደጋፊዎቻቸውም እጅግ አናሳ ናቸው። ዛሬም እንደሚታየው ተገዥ ፓርቲዎቻቸውን ኦህድድና በአዴንን እንደፈለጉት በዘላቂነት ማሽከርከር አቅቷቸዋል። ስለዚህ ተስፋ አለን፤ ከሰራን። ከመሸሽ ወይም ከማይሆን የፊትለፊት ግጭት መንገድ ከመያዝ ብልጥ ሆነን ከውስጥ ሃገሪትን መያዝ ነው።
ከዚህ በፊት ደጋግሜ እንደጻፍኩት፤
1. የትግራይ ተወላጆች በምክላከያ አናሳ ቁጥር ነው ያላቸው። የሌሎች ጎሳ ተወላጆች ከነኦሮሞና አማራ እጅግ አብዛኛው ናቸው። ይህ ሃቅ ነው። ህወሃትም ፍልጎት ሳይሆን ምርጫ የለውም፤ ትግሬ ቢበዛ ለውግያም ለሰላምም አይበጅም። ስለዚህ ትግሬዎች የስልጣን ቦታዎኦች ተቆጣጥረው ሌሎቹ ሌላውን ይዘዋል። ግን ይህ ሁኔታ ለርጅም ጊዜ አይዘልቅም። ሌሎቹ ወደፊት ግድ ሹመት ያገኛሉ ሰላምን ለመጠበቅ።
2. የደህንነቶ የጎሳ ክፍፍል በዪፋ ባይታወቅም ከሸፈቱ ምስክሮች ዘንድ በርካታ ቲግራይ ያልሆኑ ደህንነት ውስጥ እንዳሉ መረጃ አለን። ሆኖም ከሁሉም የመንግስት አካል ደህንነት ነው በህወሃት ታንቆ የተያዘው። ማንኛውም አምባገነን መንግስት ከሁሉም በላይ ደህንነትን ነው ተጠንቅቆ የሚይዘውና።
3. የትግራይ ህብረተሰብ አሁንም የኢትዮጵያ 8% በላይ አይደለም።
እነዚህ ሃቆች የሚነግሩን ህውሃት ኢትዮጵያን የሚገዛት በበርካታ ህዝብ ፈቃድና ተባባሪነት ነው። ግን በዛው መጠን ፈቃደኛውም ተባባሪውም በሙሉ ልቡ አምኖበት ሳይሆን በአቅም፤ በብስለት፤ በመተባብር፤ ወዘተ ጉድለት ነው የሚያደርኩትን የሚያደርጉት። አቅም፤ ብስለት፤ ትብብር በትንሹም ቢጨእር ያለው አገዛዝ በሰላም ይዘየር ነበር። ስለዚህ ይህ ሁኔታ እንዲፈጥር ነው ማድረግ ያለብን።
ለዚህ ነው ከዚህ በፊትም አሁንም የምለው ከነ የሩሲያ ቭላዲሚር ፑቲን አይነቱ እንማር። ፑቲን ከጎጀውን ከሀዲው የልትሲን መንግስት እየሰራ ውስጥ ለወስጥ ጥሩ ስራ እየሰራ ግን ማንነቱን ደብቆ ሃይሉን አከማቸ። ተቃዋሚ አልሆንም። ለምን፤ እንደማያዋጣና እንደምይሆን ገቡንም ለማሳካት እንደማይሆን ተረድቶ ከመንግስት ውስት በስውር መስራቱ ያዋጣልብሎ ሰራ። የሱም ቢጤዎች ብዙ ነበሩ ጉብዝናና ብልጥነታቸውም እንዲአሸንፉ ረዳቸው።
የኢትዮጵያም ሁኔታ እንደዚህ ነው። በደርግ ጊዜ ታላቅ የሆነ የግዥ መደብ ሞተ እራሱንም አጠፋ አቅምም አጣ። አሁን ያለው አማራጭ ከውስጥ ሆኖ መስራት ነው።
ደግሞ ይቻላል። ከላይ እንደጠቀስኩት ህውሃትም ደጋፊዎቻቸውም እጅግ አናሳ ናቸው። ዛሬም እንደሚታየው ተገዥ ፓርቲዎቻቸውን ኦህድድና በአዴንን እንደፈለጉት በዘላቂነት ማሽከርከር አቅቷቸዋል። ስለዚህ ተስፋ አለን፤ ከሰራን። ከመሸሽ ወይም ከማይሆን የፊትለፊት ግጭት መንገድ ከመያዝ ብልጥ ሆነን ከውስጥ ሃገሪትን መያዝ ነው።
Wednesday, 26 October 2016
ያልተጠበቀው ህዝባዊ ዐመፅ የት ይደርስ ይሆን?
(pdf)
ላለፉት
የተወሰኑ ወራት የተካሄደው የህዝባዊ ዐመፅ
እንደሚከሰት አውቅ ነበር የሚል ካለ ቀልደኛ
ነው። መንግስት አልጠበቀውም፤ ተቃዋሚዎች
አልጠበቁትም፤ ሚዲያውም የፖለቲካ ተንታኞችም
አልጠበቁትም። እኔም ጭራሽ አልጠበኩትም።
እርግጥ
የኢህአዴግን መርህዎች ለሀገሪቷ አደገኛ
ናቸው ብለን የምናምነው ሁልጊዜ ችግር ይመጣል
ብለን እንዘፍናለን። እንደዚህ ሊቀጥል
አይችልም፤ የሰውዉ ብሶት አንድ ቀን ይፈነዳል
እንል ነበር...
ለ25
ዓመት።
ግን አሁን ይህ ዐመፅ ይነሳል ብለን አልጠበቅንም።
ዐመፁ
አንዴ ከተነሳ በኋላ ትልቅ ችግር መኖሩን
የሚያሳዩ ምልክቶች እንደነበሩ ማየት እንችላለን።
ባለፉት ሁለት ዓመታት ጠቅላይ ሚኒስቴሩ ሙስናን
ለመቆጣጠር የነበራቸው ጠንካራ ፍላጎት፤ ይህ
ባለመሆኑ ብስጭታቸውን በአደባባይ እስከ
መግለጽ ያደረጋቸው ሙስናና አድሎ ምን ያህል
ያሳሰባቸው እንደነበረ ያሳያል። ህብረተሰብ
ውስጥም ስለ ሙስናና በተለይ አድሎ የነበረው
ማግሮምሮም በየዓመቱ እጅግ እያየለ እንደሆነ
ይታወሳል። ስለ አዲስ አበባ «ማስተር
ፕላን»
የነበረው
አቤቱታ ትልቅ ምልከትም ነበር። ግን ማንም
ይህ አይነት ዐመፅ ይከተላል ብሎ የገመተ
የለም።
እኔ
ያልገመትኩበት ምክንያት እኛ ኢትዮጵያኖች
የኢህአዴግን የመንግስት ስረዓት ተቀብለነዋል
ብዬ ገምቼ ስለነበር ነው። ይህ እጅግ ያሳዝነኝ
ነበር። ልክ እንደ
የቻይና ህዝብ ለ «ልማት»
(ገንዘብ)
ብሎ
ለገዥ ፓርቲው ክብሩንና መብቱን እንደሸጠ
የኛም ህዝብ ለገንዘብ፤ ለኮንዶሚኒየም፤
ለስራ እድል፤ ልድጎማ፤ ለሞቢለ ስልክ፤ ወዘተ
የ«ልማት»
ውጤቶች
ብሎ ማንነቱን ክብሩንና መብቱን ለኢህአዴግ
ሽቷል ብዬ ገምቼ ነበር።
ጎረቤቱ
ቤቱንንና መረቱን መንግስት ነጥቆት ከከተመ
ውጭ ባዶ መሬት ላይ ሲወረወር መልካም እድል
ብሎ ምንም ሳይረዳውም የሚሸኘው አይነት ህዝብ
ነው የተገነዘብኩት። በሙስና ምክንያት ፍርድ
ሜቱ ለባለንጀራው ትክክለኛ ፍትህ ሲያጎልበት
ከማጽናናት ፋንታ ዞር ብሎ የማይጠይቀው ህዝብ።
የቀበሌ ሹሞች ለልማት የመጣውን ገንዘብ ሲሰርቁ
ለኔም ትንሽ ባካፈሉኝ የሚል ህዝብ። እንደዚህ
አይነት ኢሰባዊ ድርጊቶች ቅርም የማይለው
ህዝብ። ሙስና ምንም የማይመስለው ህዝብ።
እርስ በርስ መተሳሰብ የጠፋበት ህዝብ። እንደ
ጥሩ ምሳሌ የሆኑት መሪዎቹ ለገንዘብ ብሎ ምንም
የሚያደርግ፤ የገዛ ወንድሙን ጎረቤቱን ዘመዱን
የሚሸጥ። ልጁን ለገንዘብ ብሎ እየማቀቀች
«ዶላር»
እንድትልክ
አረብ ሀገር የሚልክ ህዝብ። ስለ እድር
የሚያግሮምርም የመሃበራዊ ኑሮ ጥቅም የጠፋበት
ህዝብ። ማንነቱን ለማጥፋት የቸኮለ ህዝብ፤
ለፈረንጅ የሚሰግድ፤ ልጁን ወደ ውጭ ሀገር
ለመላክ የፈለገውን የሚያደርግ፤ ቤት ቁች
ብሎ የፈረንጅ ቅኝ ግዛት ማስፈጸምያ የቴሌቪዥን
«ድራማ»
ሲከታተል
የሚውል የደነዘዘ ህዝብ። ወጣቶቹ ስለአርሴናል
የሚገዳደሉ ህዝብ። ቤተ ክርስቲያኑ በሙስና
የተሞላች፤ መስጊዷ የተከፋፈለች ህዝብ።
የኢትዮጵያ ህዝብ በዚህ ሁኔታ ናትና በቅርቡ
ምንም አይነት ፖለቲካዊ ለውጥ አይመጣም ብዬ
ደምድሜ ነበር።
ግን
ይሄው ዐመፅ ተጀመረ። ሆኖም የሚዘልቅ አይመስልም።
ይህን የምለው ለመተንበይ አይደለም፤ ትንቢቴ
ዋጋ እንደሌለው ታይቷል። ዐመፁ ይቀሽፋል
የምለው ዐመፁ ወደ ጥሩ ነገር እንዲመራ፤
ፍሬአማ እንዲሆን ብዙሃኑም የፖለቲካ መሪዎችም
በቂ ስራ እንዳልሰሩ ለማሳየት ያህል ብዬ ነው።
እስካሁን ማንም የህዝቡን ጥያቄና ፍላጎት
በተገቢው ደረጃ ያሰባሰበና ለውይይት ያቀረበ
የለም። እስካሁን ብሶትና እሮሮ ብቻ ነው
የሚሰማው። ብዙሃኑ ብሶቱንና እሮሮውን መግለጹ
ተገቢ ነው ግን ከፖለቲካ መሪዎቹ ማቀናበርና
ማወሃድ ከሌለ የትም አይደረስም።
በኔ
እምነት ዐመፁን ያስነሳው የመጀመሪያ ደረጃ
ምክንያት አድሎ ነው፤ በተለይ በዘር የተመሰረተ
አድሎ። ህብረተሰብ ውስጥ ተቀላቅሎ አስተውሎ
ለሚመለከት ይህ ሊያመልጠው አይችልም፤
የአብዛኛው ህዝብ እሮሮ ከአድሎና ሙስና ጋር
የተያያዘ ነው። የፍትህ ጉድለት፤ የዴሞክራሲ
ጉድለት፤ የጎሳ አስተዳደር፤ ወዘተ ሁለተኛ
ደረጃ ምክንያቶች ነበሩ። ግን መፍትሄ ከተፈለገ
እነዚህ፤ ፍትህ፤ ዴሞክራሲ ወይም ተጠሪነት፤
እኩልነት፤ ናቸው መሰረታዊ ጉዳዮቹ!
ሙስናና
አድሎ የኔዚህ ርዥራዦች ናቸው። ስለዚህ
የህዝቡም የፖለቲካ መሪዎችም የምሁራንም
ቱክረት እነዚህ ጉዳዮች ላይ ካልሆነ ትክክለኛ
ለውጥ ሊመጣ አይችልም።
ዐመፁ
እንደምጠብቀው ከበረደ ቀጥሎ ምን ይደረግ?
ከዚህ
በፊት እንደጻፍኩት መልካም አስተዳደርና
መልካም ህብረተሰብ እንዲሆንልን የምንፈልገው
በየ ጎራችን፤ ከምነግስት
አስተዳደር ውስጥ ቢሆንም፤ በበኩላችን
መልካም
ስራ መስራትና ጥሩ ዜጋና ምሳሌ መሆን ነው
ማድረግ ያለምን። ለውጥ
የምንፈልገው አብዛኛ ከሆንን ሁላችንም
ይህን ካረግን የምንፈልገው ህብረተሰባዊና
መንግስታዊ ለውጥ ይመጣል።
Tuesday, 25 October 2016
የአንድ ዲያስፖራ ኑዛዜ
2009/2/15 ዓ.ም. (2016/10/25)
በአንድ ዲያስፖራ የተጻፈ…
ችግርን ለመፍታት በመጀመሪያ የችግሩ ዋና ምክንያቶች በትክክሉ መገኘት አለባቸው። እነዚህ ምክንያቶች ተገኝተው ሲፈቱ ነው ዋናው ችግር የሚፈታው። የችግሩ ምክንያቶች ወይም ምንጮች በትክክሉ ካልተገኙ ችግሩ መቼም አይፈታም። ይህን ሁላችንም የምናውቀው እውነታን በመጀመርያ የምጠቅሰው እኔ ከሀገሬ ኢትዮጵያ የፖለቲካና መሃበረሰባዊ ችግሮች ምክንያቶች አንዱ ነኝ ብዬ ስለማምን ነው።
ከማልፈልገው መንግስት ለመሸሽ «ኑሮ ለማሸነፍ» ብዬ ያሳደገችኝን ሀገሬ ኢትዮጵያን ትችያት ወጣሁኝ። በምሳሌ ደረጃ ቤቴን ትቼ ወጣሁኝ ማለት ይቻላል፤ በጣም በመቸኮሌም የቤቴን ቁልፍ ለማንም በአደራነት አልተውኩም። ባዶና አለ ጠባቂ የተውኩትን ቤት ሌላ ሰው ገብቶ ማስተዳደር ጀመረ። የቤቱን እቃ በሚፈልገው መልክ አሸጋሸገ፤ የማይፈልገውን እቃ ሸጠ ወይም ጣለ፤ የሚፈልገውን አዲስ እቃ ደግሞ ገዛና አስገባ። እኔ ከሩቅ ከዲያስፖራ ሆኜ እመለከተለሁ አዝናለው እናደዳለው እጮሃለውም። ቤቴን በመጀመሪያው ባልተውኩኝ ኖሮ።
በርካታ የትምህርት ጓደኞቼ እንደኔ ውጭ ሀገር ናቸው። አቃቸዋለሁ፤ ጥሩ ችሎታ ያላቸው ደህና ሰዎች ናቸው። ዩኒቨርሲቲ ለመግባት የበቁ የሀገራችን ምርጥ ተማሪዎች ነበሩ፤ ሀገሪቷን በደምብ ማገልገል የሚችሉ። ግን ዛሬ ሀገራቸውን ለቀው ውጭ ናቸው፤ አሜሪካንን ያገለግላሉ፤ ወይ ስዊድንን ያገለገላሉ። ታድያ እነዚህ ሁሉ ከሀገር ወጥተው ማን ነው የቀረው? እኔ ከሀገራችንን ከሚመሩት የተሻልኩኝ፤ እንደነሱ ክፉ ያልሆንኩኝ፤ ሀገር ወዳድ ነኝ ብዬ የማምን ከሆነ ከሀገሬ መውጣቴ ምን ይባላል። እራሴን አውጥቼ ሀገሬን ለክፉ ናቸው የምላቸው ሰዎች ትችያታለሁ ማለት ነው። ትልቅ ጥፋት አለብን።
አንድ አስተማሪ የቤተ ክርስትያን ተረት ልንገራችሁ… በአንድ ወክት የቤተ ክርስትያን አመራርና ካህናት በከባድ የመንፈሳዊ ፈተና ተይዘው ነበር። በካህናቱ መካከል የእምነት ጉድለት፤ የስነ መግባር ጉድለት፤ የሙስና ብዛት፤ ወዘተ ይታይ ነበር። እጅግ ከባድ ዘመን ነበር። በዚህ ጊዜ አንድ ደህና ኑሮ ያላት ሴት ወይዘሮ ወደ አንድ የታወቁ መንፈሳዊ አባት ለራስዋ ጉዳዮች ምክር ለማግኘትና ንስሀ ለመግባት ትሄዳለች። ከኚህ አባት ጋር ቁጭ ብላ መወያየት ስትጀምር ግን ዋና ጉዳይዋን ትታ ስለ ቤተ ክርስቲያን አመራሮችና ካህናት ችግር ብቻ ታወራለች ታጉረመርማለችም። የምታማክራቸው አባት በትዕግስት አቤቱታዋንና ወሬዋን እስክትጨርስ ድረስ አዳመጧት። ሁሉንም ተችታና ኮንና ጨረሰች። ቀጥሎ እኚህ ታላቅ አባት ልጆች እንዳሏት ጠየቋት። አዎን ሁለት ሴቶችና ሁለት ወንዶች አሉኝ አለች። ከነዚህ ወንድ ልጆችሽ አንዱ ቄስ ቢሆንስ ብለው ጠየቋት። በፍጹም፤ እንዴት ይሆናል ብላ ተቆጣች። እንዴት ለልጀ ገንዘብም እውቀጥም የሌለውን ስራ እመኝለታለሁ አለች! ታድያ የራስሽ ልጆች ካህን እንዲሆኑ ካልፈለግሽ ማን ነሽ በፈቃዳቸው ካህን እንሆናለን ያሉትን የምትኮንኙ ብለው ታላቁ አባት ወቀሷት አስተማሯትም።
ሀገር ችግር ላይ በሆነበት ጊዜ መሸሽ ክህደት ነው ማለት ይቻላል። እኔ ሀገሬን ከድጂያታለሁ ለማለት ወደኋላ አልልም። ጥፋትንና ድክመትን ማመን የመጀመሪያ የችግርን መፍታት እርምጃ ነው። አንድ ሰው ቤተሰብ ውስጥ ችግር ካለ ቤተሰብነቱን ክዶ ሸሽቶ አይሄድም። ልጀ ካስቸገረኝ ልጄ አይደለህም ብዬ አላባርረውም። ካባረርኩት ካድኩት ማለት ነው። ሀገርም እንደዚህ ነው። ሀገር ወዳድ ነኝ ማለትና ሀገር ችግር ላይ ስትወድቅ መሸሽ ተጻራሪ ናቸው!
እውነት ነው፤ አንዳንዴ ሽሽት ግድ ነው። ድንግል ማርያም ልጇን ክርስቶስን ይዛ ሸሽታለች። ግን ሽሽቱ አላማን ለማሳካት ነው እንጂ ለመሸሽ አይደለም። እውነቱን ለመናገር እኔ ግን ወደ ዲያስፖራ የመጣሁት ለመሸሽና የሀገሬን ችግር ለሌሎች ለመተው ነው። ለሀገሬ አላማ ኖሮኝ አይደለም። ኢትዮጵያ ያሉት ታግለውልኝ ደህና መንግስት ሲያመጡ እመለሳለሁ ብዬ ነው። ግን ያም ቢሆን የምመለስ ይመስላችኋልን? ከሃዲ ነኝ፤ እውነት ነው፤ ጥፋቴን አምናለሁ።
ግን ሀገሬን እውዳለሁ፤ ፖለቲካዋ እንደዚህ ወይም እንደዛ መሆን አለበት፤ መሃበረሰቧም እንደዚህ ወይም እንደዛ መምሰል አለበት፤ ህዝቡ መሰልጠን አለበት፤ መንግስትም አሰራሩ እንደዚህ መሆን አለበት ብዬ አስባለሁ እለፈልፋለውም። ሀሳብና ወሬ ብቻ ሀገር ወዳድ የሚያደርግ ይመስለኛል።
ሀገር ወዳድ ሆኜ ግን እንዴት ነው ተግባሬ ያንን የሀገር ፍቅርን ሊያንጸባርቅ የሚችለው? ልጆቼን እንኳን ቋንቋቸውን አላስተማርኳቸውም። ሀገረ ወዳድነት ይህ ነው? ያውም «አላስተማርኳቸውም» የሚለው ቃል በቂ አይገልጸውም፤ አላስተማርኳቸውም ሳይሆን እንዳይማሩ ከልኪያቸዋለሁ። ሌላው ሁሉ መጤ፤ ሂስፓኒኩ፤ ቻይናው፤ ሶማሌው፤ ጣሊያኑ፤ ወዘተ ቋንቋውን ከቤት እየተናገረ ልጆቻቸው በተዘዋዋሪ ቋንቋቸውን ይችላሉ። እኔ ግን ከቤቴ በደምብ የማልችለውን እንግሊዘኛ (ወይም ጀርመን ስዊድኛ ወዘተ) እየተናገርኩኝ ልጆቼ ቋንቋቸውን እንዳይችሉ አረጋለሁ። ባህላቸውን ወጋቸውንም ላይላዩን ብቻ ነው የማስተምራቸው። እውነቱን ለመናገር ልጆቼን ፈረንጅ እንዲሆኑ አድርግያለሁ። ኢትዮጵያዊ ትውልድ በኔ ቆሟል። ታድያ ምን አይነት ሀገር ወዳድ ነኝ?
ወደ ክህደቴ ልመለስና… እርግጥ እራሴን ለማጽናናት ያህል አንዳንድ ግዜ ለክህደቴ ስበቦችና አጉል ምክንያቶች እፈጥራለሁ። አንዱ «ከሀገሬ ብቆይ እታሰር ነበር» ነው። «ህሊናዬን ሽጥቼ ካልሆነ ሀገሬ መስራት አልችልም።» ታድያ ሀገር ቤት ያሉት ወገኖቼ በሙሉ ወይ ታስረዋል ወይ ህሊናቸውን የሸጡ አደርባዮች ሆኖዋል ማለት ነው? ወይ ፍርድ! በአንድ በኩል ገዥው መንግስት የአናሳ ህዝብ ነው እላለሁ። በሌላው በኩል ሁሉንም ይቆጣጠራሉ እላለሁ። እነዚህ የሚጻረሩ ሀሳቦች ናቸው! እውነቱ እንደዚህ ነው፤ አብዛኛው ህዝብ ክፉ ላለማድረግ ከወሰነ ከተባበረ በሀገሪቷ ያለውን ክፋት ይጠፋ ነበር። እራሴን እንደዚህ ማታለል አልችልም፤ ከሀገሬ ሆኜ ለሀገሬ በርካታ ጠቃሚ ነበር አፈራ ነበር።
አንዳንድ ጊዜ ደግሞ ክሀገሬ የሸሸሁት ኑሮ አሸንፌ ቤተሰቤን ለመርዳት ነው ብዬ እራሴን ማጽናናት እሞክራለሁ። ከቅዠቴ ስነቃ ግን ለዚህም አጉል ምክንያት መልስ አለኝ። ሀገር የሚያድገው ገንዘብ ሲያገኝ ነው ወይም ህዝቡ በእውቀትና ችሎታ ሲበለጽግ ነው? ጃፓን ምንም ተፈጥሮ ሃብት ሳይኖራት ህዝቧን በእውቀትና ችሎታ እንዲበለጽግ አድርጋ ነው ያደገችው። ሳውዲ ደግሞ በተፈጥሮ ሃብት ምክንያት በገንዘብ ሃብታም ሆና ግን በህዝብ ደሃ ናት። ገንዘብ ለቤተሰቤ መላክ ምን ያህል ሀገሪቷንም እነሱንም ይጠቅማል? እርገጥ አንዳንድ ቤተሰብ ገንዘቡን ለዘላቂ ነገር ለትምህርት ለንግድ ወዘተ ይጠቅምበታል። በርካታው ደግሞ ለለት ኑሮ ይጠቀምበታል። ምንም ቢሆን ገንዘቤ እኔን አይተካም ሊተካም አይችልም ይተካል የሚለው አስተሳሰብም ጎጂ ነው። ማንም በድጎማ አይበለጽግም። ይህ ከሀገር ለመሸሽ ምክንያቴ ሊሆነ አይገባም።
አዎን ለክህደቴ ምንም ስበብ የለም። አምኛለሁ። ንስሀ ገባለሁም። እግዚአብሔር ሀገር ቤት እንድመለስና ከወገኖቼ አብሬ ደስታቸውንም ችግራቸውንም እንድካፈል ብርታቱ ይስጠኝ። እራሴንም ማታለል እንዳቆም ይርዳኝ። አሜን።
በአንድ ዲያስፖራ የተጻፈ…
ችግርን ለመፍታት በመጀመሪያ የችግሩ ዋና ምክንያቶች በትክክሉ መገኘት አለባቸው። እነዚህ ምክንያቶች ተገኝተው ሲፈቱ ነው ዋናው ችግር የሚፈታው። የችግሩ ምክንያቶች ወይም ምንጮች በትክክሉ ካልተገኙ ችግሩ መቼም አይፈታም። ይህን ሁላችንም የምናውቀው እውነታን በመጀመርያ የምጠቅሰው እኔ ከሀገሬ ኢትዮጵያ የፖለቲካና መሃበረሰባዊ ችግሮች ምክንያቶች አንዱ ነኝ ብዬ ስለማምን ነው።
ከማልፈልገው መንግስት ለመሸሽ «ኑሮ ለማሸነፍ» ብዬ ያሳደገችኝን ሀገሬ ኢትዮጵያን ትችያት ወጣሁኝ። በምሳሌ ደረጃ ቤቴን ትቼ ወጣሁኝ ማለት ይቻላል፤ በጣም በመቸኮሌም የቤቴን ቁልፍ ለማንም በአደራነት አልተውኩም። ባዶና አለ ጠባቂ የተውኩትን ቤት ሌላ ሰው ገብቶ ማስተዳደር ጀመረ። የቤቱን እቃ በሚፈልገው መልክ አሸጋሸገ፤ የማይፈልገውን እቃ ሸጠ ወይም ጣለ፤ የሚፈልገውን አዲስ እቃ ደግሞ ገዛና አስገባ። እኔ ከሩቅ ከዲያስፖራ ሆኜ እመለከተለሁ አዝናለው እናደዳለው እጮሃለውም። ቤቴን በመጀመሪያው ባልተውኩኝ ኖሮ።
በርካታ የትምህርት ጓደኞቼ እንደኔ ውጭ ሀገር ናቸው። አቃቸዋለሁ፤ ጥሩ ችሎታ ያላቸው ደህና ሰዎች ናቸው። ዩኒቨርሲቲ ለመግባት የበቁ የሀገራችን ምርጥ ተማሪዎች ነበሩ፤ ሀገሪቷን በደምብ ማገልገል የሚችሉ። ግን ዛሬ ሀገራቸውን ለቀው ውጭ ናቸው፤ አሜሪካንን ያገለግላሉ፤ ወይ ስዊድንን ያገለገላሉ። ታድያ እነዚህ ሁሉ ከሀገር ወጥተው ማን ነው የቀረው? እኔ ከሀገራችንን ከሚመሩት የተሻልኩኝ፤ እንደነሱ ክፉ ያልሆንኩኝ፤ ሀገር ወዳድ ነኝ ብዬ የማምን ከሆነ ከሀገሬ መውጣቴ ምን ይባላል። እራሴን አውጥቼ ሀገሬን ለክፉ ናቸው የምላቸው ሰዎች ትችያታለሁ ማለት ነው። ትልቅ ጥፋት አለብን።
አንድ አስተማሪ የቤተ ክርስትያን ተረት ልንገራችሁ… በአንድ ወክት የቤተ ክርስትያን አመራርና ካህናት በከባድ የመንፈሳዊ ፈተና ተይዘው ነበር። በካህናቱ መካከል የእምነት ጉድለት፤ የስነ መግባር ጉድለት፤ የሙስና ብዛት፤ ወዘተ ይታይ ነበር። እጅግ ከባድ ዘመን ነበር። በዚህ ጊዜ አንድ ደህና ኑሮ ያላት ሴት ወይዘሮ ወደ አንድ የታወቁ መንፈሳዊ አባት ለራስዋ ጉዳዮች ምክር ለማግኘትና ንስሀ ለመግባት ትሄዳለች። ከኚህ አባት ጋር ቁጭ ብላ መወያየት ስትጀምር ግን ዋና ጉዳይዋን ትታ ስለ ቤተ ክርስቲያን አመራሮችና ካህናት ችግር ብቻ ታወራለች ታጉረመርማለችም። የምታማክራቸው አባት በትዕግስት አቤቱታዋንና ወሬዋን እስክትጨርስ ድረስ አዳመጧት። ሁሉንም ተችታና ኮንና ጨረሰች። ቀጥሎ እኚህ ታላቅ አባት ልጆች እንዳሏት ጠየቋት። አዎን ሁለት ሴቶችና ሁለት ወንዶች አሉኝ አለች። ከነዚህ ወንድ ልጆችሽ አንዱ ቄስ ቢሆንስ ብለው ጠየቋት። በፍጹም፤ እንዴት ይሆናል ብላ ተቆጣች። እንዴት ለልጀ ገንዘብም እውቀጥም የሌለውን ስራ እመኝለታለሁ አለች! ታድያ የራስሽ ልጆች ካህን እንዲሆኑ ካልፈለግሽ ማን ነሽ በፈቃዳቸው ካህን እንሆናለን ያሉትን የምትኮንኙ ብለው ታላቁ አባት ወቀሷት አስተማሯትም።
ሀገር ችግር ላይ በሆነበት ጊዜ መሸሽ ክህደት ነው ማለት ይቻላል። እኔ ሀገሬን ከድጂያታለሁ ለማለት ወደኋላ አልልም። ጥፋትንና ድክመትን ማመን የመጀመሪያ የችግርን መፍታት እርምጃ ነው። አንድ ሰው ቤተሰብ ውስጥ ችግር ካለ ቤተሰብነቱን ክዶ ሸሽቶ አይሄድም። ልጀ ካስቸገረኝ ልጄ አይደለህም ብዬ አላባርረውም። ካባረርኩት ካድኩት ማለት ነው። ሀገርም እንደዚህ ነው። ሀገር ወዳድ ነኝ ማለትና ሀገር ችግር ላይ ስትወድቅ መሸሽ ተጻራሪ ናቸው!
እውነት ነው፤ አንዳንዴ ሽሽት ግድ ነው። ድንግል ማርያም ልጇን ክርስቶስን ይዛ ሸሽታለች። ግን ሽሽቱ አላማን ለማሳካት ነው እንጂ ለመሸሽ አይደለም። እውነቱን ለመናገር እኔ ግን ወደ ዲያስፖራ የመጣሁት ለመሸሽና የሀገሬን ችግር ለሌሎች ለመተው ነው። ለሀገሬ አላማ ኖሮኝ አይደለም። ኢትዮጵያ ያሉት ታግለውልኝ ደህና መንግስት ሲያመጡ እመለሳለሁ ብዬ ነው። ግን ያም ቢሆን የምመለስ ይመስላችኋልን? ከሃዲ ነኝ፤ እውነት ነው፤ ጥፋቴን አምናለሁ።
ግን ሀገሬን እውዳለሁ፤ ፖለቲካዋ እንደዚህ ወይም እንደዛ መሆን አለበት፤ መሃበረሰቧም እንደዚህ ወይም እንደዛ መምሰል አለበት፤ ህዝቡ መሰልጠን አለበት፤ መንግስትም አሰራሩ እንደዚህ መሆን አለበት ብዬ አስባለሁ እለፈልፋለውም። ሀሳብና ወሬ ብቻ ሀገር ወዳድ የሚያደርግ ይመስለኛል።
ሀገር ወዳድ ሆኜ ግን እንዴት ነው ተግባሬ ያንን የሀገር ፍቅርን ሊያንጸባርቅ የሚችለው? ልጆቼን እንኳን ቋንቋቸውን አላስተማርኳቸውም። ሀገረ ወዳድነት ይህ ነው? ያውም «አላስተማርኳቸውም» የሚለው ቃል በቂ አይገልጸውም፤ አላስተማርኳቸውም ሳይሆን እንዳይማሩ ከልኪያቸዋለሁ። ሌላው ሁሉ መጤ፤ ሂስፓኒኩ፤ ቻይናው፤ ሶማሌው፤ ጣሊያኑ፤ ወዘተ ቋንቋውን ከቤት እየተናገረ ልጆቻቸው በተዘዋዋሪ ቋንቋቸውን ይችላሉ። እኔ ግን ከቤቴ በደምብ የማልችለውን እንግሊዘኛ (ወይም ጀርመን ስዊድኛ ወዘተ) እየተናገርኩኝ ልጆቼ ቋንቋቸውን እንዳይችሉ አረጋለሁ። ባህላቸውን ወጋቸውንም ላይላዩን ብቻ ነው የማስተምራቸው። እውነቱን ለመናገር ልጆቼን ፈረንጅ እንዲሆኑ አድርግያለሁ። ኢትዮጵያዊ ትውልድ በኔ ቆሟል። ታድያ ምን አይነት ሀገር ወዳድ ነኝ?
ወደ ክህደቴ ልመለስና… እርግጥ እራሴን ለማጽናናት ያህል አንዳንድ ግዜ ለክህደቴ ስበቦችና አጉል ምክንያቶች እፈጥራለሁ። አንዱ «ከሀገሬ ብቆይ እታሰር ነበር» ነው። «ህሊናዬን ሽጥቼ ካልሆነ ሀገሬ መስራት አልችልም።» ታድያ ሀገር ቤት ያሉት ወገኖቼ በሙሉ ወይ ታስረዋል ወይ ህሊናቸውን የሸጡ አደርባዮች ሆኖዋል ማለት ነው? ወይ ፍርድ! በአንድ በኩል ገዥው መንግስት የአናሳ ህዝብ ነው እላለሁ። በሌላው በኩል ሁሉንም ይቆጣጠራሉ እላለሁ። እነዚህ የሚጻረሩ ሀሳቦች ናቸው! እውነቱ እንደዚህ ነው፤ አብዛኛው ህዝብ ክፉ ላለማድረግ ከወሰነ ከተባበረ በሀገሪቷ ያለውን ክፋት ይጠፋ ነበር። እራሴን እንደዚህ ማታለል አልችልም፤ ከሀገሬ ሆኜ ለሀገሬ በርካታ ጠቃሚ ነበር አፈራ ነበር።
አንዳንድ ጊዜ ደግሞ ክሀገሬ የሸሸሁት ኑሮ አሸንፌ ቤተሰቤን ለመርዳት ነው ብዬ እራሴን ማጽናናት እሞክራለሁ። ከቅዠቴ ስነቃ ግን ለዚህም አጉል ምክንያት መልስ አለኝ። ሀገር የሚያድገው ገንዘብ ሲያገኝ ነው ወይም ህዝቡ በእውቀትና ችሎታ ሲበለጽግ ነው? ጃፓን ምንም ተፈጥሮ ሃብት ሳይኖራት ህዝቧን በእውቀትና ችሎታ እንዲበለጽግ አድርጋ ነው ያደገችው። ሳውዲ ደግሞ በተፈጥሮ ሃብት ምክንያት በገንዘብ ሃብታም ሆና ግን በህዝብ ደሃ ናት። ገንዘብ ለቤተሰቤ መላክ ምን ያህል ሀገሪቷንም እነሱንም ይጠቅማል? እርገጥ አንዳንድ ቤተሰብ ገንዘቡን ለዘላቂ ነገር ለትምህርት ለንግድ ወዘተ ይጠቅምበታል። በርካታው ደግሞ ለለት ኑሮ ይጠቀምበታል። ምንም ቢሆን ገንዘቤ እኔን አይተካም ሊተካም አይችልም ይተካል የሚለው አስተሳሰብም ጎጂ ነው። ማንም በድጎማ አይበለጽግም። ይህ ከሀገር ለመሸሽ ምክንያቴ ሊሆነ አይገባም።
አዎን ለክህደቴ ምንም ስበብ የለም። አምኛለሁ። ንስሀ ገባለሁም። እግዚአብሔር ሀገር ቤት እንድመለስና ከወገኖቼ አብሬ ደስታቸውንም ችግራቸውንም እንድካፈል ብርታቱ ይስጠኝ። እራሴንም ማታለል እንዳቆም ይርዳኝ። አሜን።
Friday, 14 October 2016
Stop Crying About The EPRDF And Fix Ethiopia's Main Problem – The Opposition
2009/2/3
(Ethiopian calendar)
2016/10/13
(European calendar)
[Note:
An Amharic version of this post will appear sometime!]
(pdf)
Let's
decide once and for all: Is the EPRDF a party that represents a
majority of Ethiopians? Or is the EPRDF a minority party, dominated
by the TPLF, which represents a minority from the state of Tigray,
along with some hangers on from other ethnic groups? Which is it?
Before
answering, think about the question carefully. If we say that the
EPRDF represents a majority of Ethiopians, then why do we claim that
there is lack of pluralism and democracy, and that power and
resources are controlled by a few? This is a contradiction. We cannot
at the same time say that the EPRDF represents a majority and at the
same time claim there is no democracy.
How
about the second answer – if we answer that yes, the EPRDF is
indeed a minority party – a tiny minority party at that? Then we
are admitting that we are being ruled and have been ruled by a tiny
minority for 25 years. But this again raises a contradiction – a
contradiction with the usual opposition (by opposition I mean not
only political parties but media, organizations, individuals, etc.)
rhetoric. After all a tiny minority cannot rule without the consent
of the large majority it's ruling. This is even more the case when
the minority rule is primarily ethnic based. It is this consent that
keeps the EPRDF in power – absent this consent, the EPRDF would
fall. So whose responsibility is it that the EPRDF rules Ethiopia –
the minority rulers or the majority consentors? And who is it that
can end EPRDF rule? The answer is obvious – it is the majority. Yet
opposition rhetoric is solely focused on the evils of the minority
EPRDF! This is the contradiction. The problem is with the majority,
yet we talk about the minority.
So
the fact is that yes, the EPRDF is a minority party, and yes,
responsibility for its rule lies fully in the hands of the majority
which has agreed to be ruled by it. To put it bluntly, Ethiopia's
problems today are not the fault of the EPRDF, but the fault of the
Ethiopian people and elites which have enabled the EPRDF's rule. And
if we are seeking a solution to the problems, our focus should be on
what we can change – the attitudes and abilities of the majority –
rather than what we cannot change – the EPRDF.
I
understand that this fact, even after 25 years, remains difficult for
those of us who oppose the EPRDF to accept, let alone discuss. Only a
few have talked about it in the past
and a few make mention of it today, if only in passing.
And it is precisely because we refuse to address it, instead spending
all our ink, time, and airtime on the EPRDF's evils, that the EPRDF
still rules.
At
this point, let me digress... I am afraid that there are still many
who still believe that somehow it is the awesome might, cruelty, and
ingenuity of the EPRDF that has led to majority consent. How the
might, cruelty, and ingenuity of 6% or even 10% beats 90% is beyond
me, but let me remind them of the following brief facts. In all
government institutions, members of the TPLF are a small minority.
Outside Tigray, almost all the governing is done by non-TPLF members,
and even the TPLF 'minders' are few in number. The EPRDF is majority
non-TPLF. Even the military and federal police, and this is a fact,
is composed of a large majority of non-Tigreans. To put it simply,
the ones with the guns are not Tigreans, only the leadership is
overwhelmingly TPLF. Note that if only rank and file soldiers decided
to stop following orders, the EPRDF would lose power instantly. Even
the security apparatus, which we assume has proportionately many more
TPLF members, would not be able to do anything once the military
ceases to be an EPRDF tool.
A
second digression, to address those who are still stuck in the
thinking that the opposition elites are weak because of EPRDF
oppression. Is the diaspora opposition also weak because of EPRDF
oppression?! Are the historical problems with the AAPO/AEUP, Kinijit,
Andinet, Medrek, not to mention various Oromo ethno-nationalist
groups. because of EPRDF pressure? Everyone knows the answer is no.
That opposition elites have been weak for the last 25 years and
remain weak is of our own doing. We and only we are responsible, and
the solution for the weakness can come only from us.
So
I propose that those of us who are really interested in bringing an
end to EPRDF rule as it is rather than just venting their anger start
spending more of our time, dare I say all our time, focusing on the
problem of majority consent to EPRDF rule and what can be done about
it.
I
understand this is a complicated problem. A lot of issues, not least
of which the ethnic divide, have to be frankly discussed. There has
to be investment in raising social and political awareness. Given the
EPRDF's zero political space policy, this work has to be done in
various non-political contexts, in various institutions, and in a
clandestine or seamless manner. It's long, slow, and non-glamourous
work. It's not as easy as simply heaping blame on the EPRDF and
looking for the next protest on which to hang our hopes. But it's the
only way to go.
I
would like to end with a note of urgency. As many commentators have
noted, we have a grassroots uprising today with little coordination
and little elite input. Frankly speaking, given the absence of a
solid opposition elite, the political situation a few years ago, with
the EPRDF in firm control, was far less risky for the country than
what we have today. Today, there is a chance that the protests could
result in upheaval and anarchy, and this in the absence of a solid
opposition elite. The consequences of such anarchy would be terrible.
For this reason, I urge all of us to get our act together, focus on
the right problem, and work on the solution.
Friday, 30 September 2016
ጥፋት አለብኝ ብዬ ካላመንኩኝ «ወያኔ» ነኝ!
2009/1/19 ዓ.ም. (2016/9/29)
ከዲያስፖራ እየኖርኩኝ ስጋዊ ምቾቴን አጠናቅቄ ህሊናዬ እየወቀሰኝ ሀገር ቤት ያሉትን ወንድሞች እህቶቼን ታገሉ እላለሁ። ሀግሬን እወዳለሁ እላለውንጂ ያሳደገችኝ ብትሆንም ለሷ ያለኝን ሃላፊነት ከተውኩኝ ቆይቻለሁ። ክጃታለሁ ጥያታለሁም። ሆኖም ግን ሀገሬን መበደሌ አይታየኝም። ስለሌሎችን ኅጢአትና በደል እጮሀለው እንጂ። ከአይኔ ያለውን ግንድ አላየውም የሌላውን ጉድፍ ብቻ ነው የሚታዬኝ።
ምሬቴ ትንሽ በመሆኗ ምክንያት አጥሬን መግፋት መብቴ ነው እላለሁ! ገፈዋለሁ፤ ከጎረቤት ጋርም እጣላለሁ፤ መንገድንም አጠባለሁ። ለሰፈሩ ችግር እያመጣሁኝ ነው። ግን የእለት ወሬዬ ስለ ቀበሌአችን ሹማምንት የምስና ባህሪ ነው። አይኔ ውስጥ ግንድ የለም።
እውነት ነው፤ ሲያስፈልግ ጉቦ ሰጣለሁ። መብቴን ለማስከበር ብቻ ሳይሆን የማይገባኝን ለማግኘትም። ምን ይደረግ፤ የሀገራችን እውነታ ነው ብዬ እራሴን አታልላለው። ግን መሪዎቻችን እንዴት ሞራል ቢስ ናቸው ብዬ አማርራለሁ።
አንዱ የኦርቶኦክስ መሰረታዊ እምነት ሁላችንም ለሁሉም ሰው ኅጢአት በተወሰነ ደረጃ አስተዋጾ እድርገናልና ሃላፊነት አለብን የሚል ነው። ኅጢአቶቻችን የተገናኙም የተወራረሱም ናቸው። ይህንን ለማብራራት ያህል የታወቀው ሩሲያዊ ደራሲ ፊኦዶር ዶስቶኤቭስኪ በ«ካራማዞቭ ወንድማማቾች» የጻፈውን ጥቅስ እንመልከት። ታላቁ የሃይማኖት አባት ዞሲማ ልጆቻቸውን ሲመክሩ እንደዚህ አሉ፤
ከእስርቤታችን አልጋ የሆነው የበሰበሰው ገለባ ላይ ጋደም ብዬ ነው ለመጀመርያ ከውስጤ የበጎ መንፈስ የተሰማኝ። ቀስ በቀስ መረዳት የጀመርኩት ይህ ነው፤ ጥሩና ክፉን የሚለየው መስመር በሀገሮች፤ መደቦች፤ የፖለቲካ ፓርቲዎችም መካከል አይደለም የሚያልፈው፤ ይህ መስመር የሚያልፈው በያንዳንዱ የሰው ልብ መኻል ነው። መስመሩ እድሜአችን በሙሉ ከውስጣችን ወደፊት ወደኋላ ይላል። በክፉ የተሞሉ ልቦችም ቢያንስ ቅንጣት ያህል ጥሩነት ይኖራል፤ ከሁሉም ጥሩ ከሚባለውም ልብ ከአንድ ጥጓ ትንሽ ክፉነት ይኖራል።
ግን እየተሰቃዩም ቢሆን ይህን ቀላሉ የውሸት መንገድን ከመከተል እውነትን መረጡ። እውነትን ፈለገው ህሊናቸውን ተጠንቅቀው መርምረው የራሳቸውም ግድፈት እንዳለ ተገነዘቡ። ከነዛ ክፉዎች እንደማይሻሉ አመኑ።
ሶልዠኒትሲን በሁለተኛ ዓለም ጦርነት ጀግና ወትደር ነበሩ። ሀገሬን እንደዚህ አገልግዬ እንዴት በማግስቱ ለማይረባ ምክንያት እታሰራለሁ ነበር በመጀመርያ ያሰቡት። ግን ህሊናቸውን ሲመረምሩ ከጦር ሜዳ የሰሩትንና ሲሰራ አይተው ዝም ያሉትን ግፍ አስታወሱ። ሀገርን በመከላከል አሳበው ህሊናቸውን እንዴት እንደሸጡ አስተዋሉ። አብረዋቸው የታሰሩትንን የመንግስት ሰለቦች ሲመለከቱም ምንም ንጹ የሚመስሉትም በተወሰነ ደረጋ ተመሳሳይ የህሊና ሽያጭ እንዳካሄዱ ተገነዘቡ።
ከዝ ቀጥሎ የበደሏቸውን ሲመለከቱ በፊት የነበራቸው እነሱ ክፉ እኔ ንጹ የሚለው አስተሳሰባቸው ውሸት እንደሆነ ገባቸው። በዳዮቻቸውም እንደራሳቸው በተለላየ አታላይና የማይረባ ምክንያት ህሊናቸውን ሽተዋል። ስንቱ ናቸው በስመ ሀገር ወዳድነት እንደ ሶልዠኒትሲን አይነቱን የሀገር ከሃዲ ብለው ያሳሰሩት። እነዚህ «እውነት አማኞች» ርዕዮት ዓለማቸውን እንደ ሃይማኖት አድረገው የሚያምኑበት ስለሱ ምንም ለማድረግ ወደኋላ አይሉም ነበር። ሶልዠኒትሲን እነሱን ሲያዩ እራሳቸውን አዩ።
የመጨረሻ ግንዛቤአቸው ንስሃ መግባት እንዳለባቸው ነበር። ንስሃ ቢገቡ በራሳቸው ብቻ ሳይሆን በባልደረቦቻቸው በሙሉ የደረሰው እንደማይደርስ ገባቸው። በሶቪዬት ህብረት የሚገኙት ሀገራት በሙሉም ሰላምና እውነታዊ መንግስት ሊያገኙ የሚችሉት በዚህ አይነት መንገድ ብቻ እንደሆነ ተገነዘቡ። ሌሎቻችንም እንደዚህ አድርገን እንድናስብ ጋበዙን።
እሺ፤ የምጨረሻ ጥቅስ ከአባ ዶሮቴዎስ፤
ከዲያስፖራ እየኖርኩኝ ስጋዊ ምቾቴን አጠናቅቄ ህሊናዬ እየወቀሰኝ ሀገር ቤት ያሉትን ወንድሞች እህቶቼን ታገሉ እላለሁ። ሀግሬን እወዳለሁ እላለውንጂ ያሳደገችኝ ብትሆንም ለሷ ያለኝን ሃላፊነት ከተውኩኝ ቆይቻለሁ። ክጃታለሁ ጥያታለሁም። ሆኖም ግን ሀገሬን መበደሌ አይታየኝም። ስለሌሎችን ኅጢአትና በደል እጮሀለው እንጂ። ከአይኔ ያለውን ግንድ አላየውም የሌላውን ጉድፍ ብቻ ነው የሚታዬኝ።
ምሬቴ ትንሽ በመሆኗ ምክንያት አጥሬን መግፋት መብቴ ነው እላለሁ! ገፈዋለሁ፤ ከጎረቤት ጋርም እጣላለሁ፤ መንገድንም አጠባለሁ። ለሰፈሩ ችግር እያመጣሁኝ ነው። ግን የእለት ወሬዬ ስለ ቀበሌአችን ሹማምንት የምስና ባህሪ ነው። አይኔ ውስጥ ግንድ የለም።
እውነት ነው፤ ሲያስፈልግ ጉቦ ሰጣለሁ። መብቴን ለማስከበር ብቻ ሳይሆን የማይገባኝን ለማግኘትም። ምን ይደረግ፤ የሀገራችን እውነታ ነው ብዬ እራሴን አታልላለው። ግን መሪዎቻችን እንዴት ሞራል ቢስ ናቸው ብዬ አማርራለሁ።
አንዱ የኦርቶኦክስ መሰረታዊ እምነት ሁላችንም ለሁሉም ሰው ኅጢአት በተወሰነ ደረጃ አስተዋጾ እድርገናልና ሃላፊነት አለብን የሚል ነው። ኅጢአቶቻችን የተገናኙም የተወራረሱም ናቸው። ይህንን ለማብራራት ያህል የታወቀው ሩሲያዊ ደራሲ ፊኦዶር ዶስቶኤቭስኪ በ«ካራማዞቭ ወንድማማቾች» የጻፈውን ጥቅስ እንመልከት። ታላቁ የሃይማኖት አባት ዞሲማ ልጆቻቸውን ሲመክሩ እንደዚህ አሉ፤
«አንድ ሰው በዚህ ዓለም ከሚኖሩት በሙሉ የባሰ ኅጢአተኛ እንደሆነ ሲያምን፤ በተጨማሪም ከሁሉም ሕዝብ ፊት ጥፋተኛ እንደሆነ...፤ ለዓለምም ለያንዳንዱ ሰውንም ኅጢአት እና ጥፋት እንዳለበት ስያምን ነው የ(ክርስቲያናዊ) አንድነት ድላችንን ማስመዝገብ የምንችለው..።በተጨማሪ ባለፈው ጽሁፌ የጠቀስኩት በጾቪዬት እስር ቤት የተሰቃዩት አለክሻንደር ሶልዠኒትሲን ከእስር ቤት ሆነው የጻፉትን እንደገና ልጥቀስ፤
«ሁላችሁም ልባችሁን በደምብ አዳምጡና ለራሳችሁ ሳትሰለቹ ንስሐ ግቡ። እስከ ተጸጸታችሁ ድረስ ኅጢአታችሁ የጎላ ቢመስላችሁም አትፍሩት...።
«በጸሎታችሁ እንደዚህ አስታውሷቸው፤ «አምላካችን ሆይ የሚጸልይላቸው የሌሏቸውንም ላንተ መጸለይ የማይፈልጉትንም አድናቸው» ብላችሁ ጸልዩ። እንደዚህም ቀጥሉ «አምላኬ ሆይ እኔ ከሁሉም የባሰ ርኩስ ነኛ፤...»»
ከእስርቤታችን አልጋ የሆነው የበሰበሰው ገለባ ላይ ጋደም ብዬ ነው ለመጀመርያ ከውስጤ የበጎ መንፈስ የተሰማኝ። ቀስ በቀስ መረዳት የጀመርኩት ይህ ነው፤ ጥሩና ክፉን የሚለየው መስመር በሀገሮች፤ መደቦች፤ የፖለቲካ ፓርቲዎችም መካከል አይደለም የሚያልፈው፤ ይህ መስመር የሚያልፈው በያንዳንዱ የሰው ልብ መኻል ነው። መስመሩ እድሜአችን በሙሉ ከውስጣችን ወደፊት ወደኋላ ይላል። በክፉ የተሞሉ ልቦችም ቢያንስ ቅንጣት ያህል ጥሩነት ይኖራል፤ ከሁሉም ጥሩ ከሚባለውም ልብ ከአንድ ጥጓ ትንሽ ክፉነት ይኖራል።
«በየቦታው እየዞሩ ያሉ ክፉ ስራ የሚሰሩ ክፉ ሰዎች ቢኖሩና እነሱን ከኛ መለየትና ማጥፋት ብቻ ቢሆን ኖሮ እንዴት ቀላል ነበር? ግን ጥሩና ክፉን የሚለየው መስመር ከያንዳንዱ የሰው ልጅ ልብ መካከል ነው የሚያልፈውና ማን አለ ከራሱ ልብ ቁራጭ ቆርጦ ለማጥፋት ፈቃደኛ ይሆነ?»ሶልዠኒትሲን በመታሰራቸው፤ በእስር ቤት ለደረሰባቸው በደልና ስቃይ፤ ያሰሯቸውን የዘመኑን መንግስት መሪዎች፤ የፍርድ ቤት ዳኞች፤ የደህንነት አዛዦች፤ ወዘተ ብቸኛ ጥፋተኛ አድርገው ሊቆትሩ ይችሉ ነበር። ማንናችንም ደካሞች በሳቸው ቦታ ብንሆን እንደዛ ነበር የምናስበው።
ግን እየተሰቃዩም ቢሆን ይህን ቀላሉ የውሸት መንገድን ከመከተል እውነትን መረጡ። እውነትን ፈለገው ህሊናቸውን ተጠንቅቀው መርምረው የራሳቸውም ግድፈት እንዳለ ተገነዘቡ። ከነዛ ክፉዎች እንደማይሻሉ አመኑ።
ሶልዠኒትሲን በሁለተኛ ዓለም ጦርነት ጀግና ወትደር ነበሩ። ሀገሬን እንደዚህ አገልግዬ እንዴት በማግስቱ ለማይረባ ምክንያት እታሰራለሁ ነበር በመጀመርያ ያሰቡት። ግን ህሊናቸውን ሲመረምሩ ከጦር ሜዳ የሰሩትንና ሲሰራ አይተው ዝም ያሉትን ግፍ አስታወሱ። ሀገርን በመከላከል አሳበው ህሊናቸውን እንዴት እንደሸጡ አስተዋሉ። አብረዋቸው የታሰሩትንን የመንግስት ሰለቦች ሲመለከቱም ምንም ንጹ የሚመስሉትም በተወሰነ ደረጋ ተመሳሳይ የህሊና ሽያጭ እንዳካሄዱ ተገነዘቡ።
ከዝ ቀጥሎ የበደሏቸውን ሲመለከቱ በፊት የነበራቸው እነሱ ክፉ እኔ ንጹ የሚለው አስተሳሰባቸው ውሸት እንደሆነ ገባቸው። በዳዮቻቸውም እንደራሳቸው በተለላየ አታላይና የማይረባ ምክንያት ህሊናቸውን ሽተዋል። ስንቱ ናቸው በስመ ሀገር ወዳድነት እንደ ሶልዠኒትሲን አይነቱን የሀገር ከሃዲ ብለው ያሳሰሩት። እነዚህ «እውነት አማኞች» ርዕዮት ዓለማቸውን እንደ ሃይማኖት አድረገው የሚያምኑበት ስለሱ ምንም ለማድረግ ወደኋላ አይሉም ነበር። ሶልዠኒትሲን እነሱን ሲያዩ እራሳቸውን አዩ።
የመጨረሻ ግንዛቤአቸው ንስሃ መግባት እንዳለባቸው ነበር። ንስሃ ቢገቡ በራሳቸው ብቻ ሳይሆን በባልደረቦቻቸው በሙሉ የደረሰው እንደማይደርስ ገባቸው። በሶቪዬት ህብረት የሚገኙት ሀገራት በሙሉም ሰላምና እውነታዊ መንግስት ሊያገኙ የሚችሉት በዚህ አይነት መንገድ ብቻ እንደሆነ ተገነዘቡ። ሌሎቻችንም እንደዚህ አድርገን እንድናስብ ጋበዙን።
እሺ፤ የምጨረሻ ጥቅስ ከአባ ዶሮቴዎስ፤
«አንድ ሰው በእግዚአብሔርን ፊት እራሱን በደምብ ቢመረመረ ለሚደርስበት ያለው በደል ባተግባር፤ በሃሳብ፤ በንግግር፤ በፀባይ፤ ወይም በባህሪይ ሃላፊነት እንዳለበትና ከፊል ተጠቅያቂ እንደሆነ ይገለጽለታል።»እንዲሁም ለኢትዮጵያ ችግሮች ሁሉ፤ የፖለቲካ ችግር ተጨምሮ፤ ሁላችንም ኢትዮጵያኖች አስተዋጾ አድርገናል ሃላፊነትም አለብን ብለን ማመን አለብን። ቀጥሎ ይህን ሃላፊነት ብንወታው ችግሩ ይፈታል ብለን ማመን አለብን። አባ ዶሮቴዎስ እንዳሉት እራሳችንን ተጠንቅቀን በኢግዚአብሔር ፊት እንመርምር። ይህ ወደ ሰላምና እውነት ብጨኛው መንገድ ነው።
Subscribe to:
Posts (Atom)