Showing posts with label agriculture. Show all posts
Showing posts with label agriculture. Show all posts

Thursday, 10 January 2019

በምሁራችን ተስፋ እንቁረጥ?

እስቲ ይህን የምጸሃፍ ትችት ያንብቡ፡ https://www.ethiopiaobserver.com/2019/01/06/book-review-overcoming-agricultural-and-food-crises-in-ethiopia/

የመጸሃፉ ጸሃፊ የኢትዮጵያ የእርሻ ምርት ችግር የኦርቶዶክስ ኃይማኖት ነው ይላል? ምሁራኖቻችን ከዚህ የፈረንጅ ማርክሲስት የ60 ዓመት በፊት አስተሳሰብ መውጣት አቅቷቸዋልን? ያሳዝናል።

ለ40 ዓመታት ኢትዮጵያ የተመራቸው በዚህ አይነት አስተሳሰብ ነው። የእርሻ ምርታችን እንደወረደ ነው። ታድያ አሁንም ምክንያቱ ቤተ ክርስቲያን ነው? እስቲ ምሁራን ትንሽ indoctrinate ካደረጋችሁ መጸሃፍት ውጡ እና imaginative ሁኑ። ምናልባት ወደ ወጋችን ብትመለሱ እና እሴቶቻችንን ብትመለከቱ መናባችሁ መስራት ይጀምር ይሆናል።

እስቲ ገበሬዎቻችንን እግዚአብሔር የሰጣቸውን ነጻነት እንስጣቸው። ከ43 ዓመት በፊት የነጠቅናቸውን መሬት እንመልስላቸው። ባለቤት እናንተ ናችሁ እንበል። ከዛ እንተዋቸው ድጋር ካስፈለጋቸው እንርዳቸው። እርስ በርስ መሻሻጥ ከፈለጉ ያድርጉት። ህበረቶች መፍጠፍ ከፈለጉ ያድርጉ። መንግስት/ወረዳ/ቀበሌ ጉዳያቸውስጥ አይግባ። እስቲ በዚህ እንጀምር።

ገቤሮዎቻችን የባህል እስረኞች አይደሉም። ለ43 ዓመት የመንግስት የማርክሲዝም የሞደርኒዝም እስረኞች ሆነው ቆይተዋል። በራሳቸው መሬት እና ክህሎት ኢንቬስት እንዳያደርጉ ተደርግዋል። ምሁራኖቻችን በትዕቢት የራሳቸውን ፍላጎት ጭነውባቸዋል። ከዛ ደግሞ ባህላቸውን እና ወጋቸውን ይተቻሉ! ህም።

Sunday, 4 November 2018

ጠ/ሚ አቢይ፤ መሬትን የግል በማድረግ የኤኮኖሚ ድል ያገኛሉ

እነ ጠ/ሚ አቢይ የለውጥ ሂደታቸውን ለማረጋጋት፤ አቅም ለመገንባት እና ጥሩ መሰረት ለመገንባት ኤኮኖሚይ እንዲጠነክርላቸው ይፈልጋሉ። ይህን ለማድረግም ብዙ እርምጃዎች እየወሰዱ እናያለን።

አንድ ያልወሰዱት እርምጃ መሬትን የግል ማድረግ ነው። ወይንም ህገ መንግስቱን ሳይቀይሩ በተዘዋዋሪ መንገድ ከተማም ገጠርም መሬት መሸጥ መለወጥ ማድረግ ነው። ልምሻሌ አማራ ክልል እንደተደረገው የረዥም ዓመት ግለሰብ ለግለሰብ ሊዝ (አማራ ክልል 25 ዓመት) መፍቀድ እና ማበረታቻ ህጎች ማርቀቅ ነው። ለምሳሌ 25 ዓመቱ 199 ዓመት ከሆነ de facto ሺያጭ ማለት ነው።

መቼስ ዛሬ መሬት መሸጥ መለወጥ ቢቻል ለኤኮኖሚውም ለማህበረሰብ ጤንነትም ታላቅ ድል እንደሚሆን ማስረዳት አያስፈልገኝም! ምርትን ይጨምራል፤ የገበሬ አቅምን (human capital) ይጨምራል፤ ሙስናን ይቀንሳል፤ የመሬት ዋስትናን (ማለትም የአዕምሮ ረፍት) ይጨምራል፤ መሬት በሚገባው ደረጃ ጥቅም እንዲውል ያደርጋል ወዘተ። ለዝርዝሩ እነዚህን ጽሁፎች  ተመልከቱ፤

፩፤ https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/03/blog-post_47.html
፪፤ https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/blog-post_94.html

በመጨረሻ የጎሳ ብሄርተኝነት ፖለቲካ ይህን እርምጃ ለመውሰድ የሚያግድ ከሆነ የጎሳ ብሄርተኝነት የማይበዛበት ቦታዎች እንደ አዲስ አበባ፤ አማራ፤ ደቡብ፤ ሌሎችም ይህን ፖሊሲ ማካሄድ ነው። ጥናቱ ቶሎ ይጀመር። ድሉ ብዙ ነው የሚሆነው።