Showing posts with label the West. Show all posts
Showing posts with label the West. Show all posts

Monday, 24 October 2022

ስደተኛን መቀበድ፤ በጎነት ወይንም ጥቅም

የዋህ ስለሆንን የካናዳ መንግስት የህወሓትን መሪዎች በስደተኝነት ከተቀበለ ካናዳ እንዴት በጎ አገር ነው ብለን እናስባለን። የምዕራባውያን አገራት ፕሮፓጋንዳ በዓስለም ታሪክ አንደኛ መሆኑ የሚመሰክረው እንዴት ለራሳቸው ጥቅም የሚያደርጉትን ነገር እንደ በጎነት አድርገው የማሳየት እና ሌሎችን የማሳመን ችሎታቸው ነው!

አንድ አገር የሌአ እገር የተሰደደ መሪ የሚቀበለው ዋጋ ስለሚያገኝበት ነው። አንድ፤ ብዙ እውቀት እና ችሎታ ያለው ሰው ያገኛል። ይህ ሰው እውቀቱን፤ ሚስጠሮችን፤ ምክሮችን ለአዲስ ባለሟሎቹ ይሰጣል! ሁለት፤ የተቀባይ አገሩን «በጎነት» ፕሮፓጋንዳ ያስመሰክራል።

የህወሓት ያረጁ መሪዎች ለካናዳ ምን ይሰሩለታል ብላችሁ ትጠቅቁ ይሆናል? እኛ የዋሆች ነን እኮ እንደዚህ በአጭሩ የምናስበው። ብልሃት ያላቸው መንግስታት እያንዳንዱን ትንሽ ነገር ዋጋ ይሰጡታል ያጠራቅማሉም። ሁሉም አብሮ ሲደመር ትልቅ ክምችት ይሆናል።

ዓለም እንደዚህ ነው እውነቱ። በዚ በኩል የዋህ ባንሆን ይሻላ።

Tuesday, 14 December 2021

Brief Note: Ethiopian Elites and the West

Ethiopia should pursue a rational and credible foreign policy. It should rationally, not emotionally and out of revenge, re-assess its relationship with the West and engage in cooperation where interests align. But it should also credibly punish the West for what it has done. At the same time, Ethiopia should reward allies such as China who stood by it while it was under attack. Ethiopia should completely re-assess its long term geostrategic policy in light of the West's attack on it and in light of current geopolitical realities.

One of the problems Ethiopia will have as it engages in revising its foreign policy is the ideological and emotional attachment of much of its elite with the West. Before and after the Cold War, the West used its soft power, including propaganda, to capture the hearts of elites all around the world. Ethiopia was no exception. The basics of the propaganda was that the West is moral and altruistic - exceptional. It wants the best for all the world. Shocking that we believed such obviously simplistic propaganda, but we did. We developed a dangerous, irrational, emotional attachment to the West.

For the sake of peace and survival, our elite has to rid itself of this emotional irrational perception of the West. All our silly assumptions should be swept away.

Thankfully, today, most of Ethiopia has realised that the West is not any more altruistic or moral than any place else. It can be cruel and nonsensical. Its ideological Messianic complex (neocolonial impulse) can make it extremely dangerous. This realisation has to set firm roots in our psyche. For the sake of our survival and peace in our region, we should never again be so naïve.

Monday, 20 September 2021

ምእራቡ ለምን ኢትዮጵያን ኢትዮጵያዊያንን ትንቃለች

የምእራቡ/ አሜሪካ ለኢትዮጵያ ያላቸው አቋም እንደዚህ ፅንፍ የያዛ የሆነው አንዱ መክነያት ለኢትዮጵያ በተለይም ለኢትዮጵያዊነት የፖለቲካ ጎራው ያለቸው መጠን የለሽ ንቀት ነው። ኢትዮጵያ/ ኢትዮጵያዊነት ምንም አቅም የለውም፣ በጣታችን ገፋ ካርግነው ይፈራርሳል የሚል ድምዳሜ ላይ ከደረሱ ቆይተዋል። ይህ ድምዳሜ ላይ የደረሱበት ምክነያቶቹ ባጭሩ ይህን ይመስላሉ፤ 

1. በ1983 የደርግ ጦር ባንዴ መቅለጡ፣ 
2. ህዝቡ ህወሓትን ከሞላ ጎደል በበቂ ሁኔታ አለማታገሉ፣
3. የኢትዮጵያዊነት ጎራው ፖለቲከኖች እርስ በርስ ሲፋጁ ለ30+ ዓመት አቅመ ቢስ ሆነው ሲቆዩ፣ 
4. 8%ን "የወከለው" ህወሓት ሀገሩን በቀላሉ ሲገዛ፣ 
5. የህወሓትና የሻብያ ዲያስፖራ የፖለቲካ ተሳትፎ የኛን በአስር እጥፍ በልጦ ሲገኝ። ለምሳሌ ሲጠየቁ ባንድ ቀን 20 ሚሊዮን ሲያዋጡ የኛ ዲያስፖራ ደግሞ በ27 ዓመት ጠቅላላ ሶስት ሚሊድንም ያላዋጣና ሳይደራጅ መቅረቱ፣
6. "በቅኝ ግዛት ያልወደቀችው ኢትዮጵያ" የስንዴና ስኮላርሺፕ ለማኝ ሆና ስትቀር፣
7. ዛሬም አንዳንድ ኢትዮጵያዊ ነን ባዮች መንግስትን ለማዳከም ይጥራሉ።

ምእራባውያን ይህን ሁሉ አይተው ነው ኢትዮጵያም (አማራውም) ደካማ አቅመ ቢስ ናቸው ብለው የደመደሙት።

በተጨማሪ የምእራቡ የኢትዮጵያ " አዋቂዎች" በኢትዮጵያ (ለነሱ አማራ) ባህል ጠንካራና አስፋሪ ቋንቋ ነው የሚሰራው ብለው በለብለብ ጥናቶቻቸው ደምድመዋል። ለዚህም ነው የአሜሪካ መንግስት መግለጫዎች ባልሰለጠነና ተራ ቋንቋ የተጻፉት።

መእራቡ ኢትዮጵያን እንደሚንቅ ማውቁ ምን ይጠቅመናል? እውነታንና የራስን ሰህተቶችን የላወቀ ስህተቶቹን ይደግማል፣ ችግር ውስጥ ይገባል፣ ሊጠፋም ይችላል። ከላ የተጠቀሱት የተናቅንበት ምክነያቶች ሁሉ እኛ ኢትዮጵያዊያን በራሳችን ላይ የመጣናቸው ችግሮች ናቸው። ከ1968-83 እርስ በርስ ሰንፋጀ እራሳችንን አጠፋንና በሩን ለጠላቶች ከፈትን። እና ህወሓትን ከተራ ሸፈታ ወደ ሀገር ገዥነት አጎለበትን። እኛ ነን ይህን የደረገ ነው፤ ባንከፋፈል ኖሮ የትም አይደርሱም ነበር። ወነኛው መማር ያለብ ትምሕርት ካሁን በሗላ የመከፋፈል ባህሪአችን መጥፋት አለበት። የህልውና ጉዳይ እንደሆነ መረዳት አለብን።

ሁለተኛ መማር ያለን ትምህርት ምን ያህል እራሳችን እንደጎዳንና ገና ጉድጓድ ውስጥ መሆናትን ነው። በጣም ብዙ የዓመታት ስራ እንዳለብን ማወቅ አለብን። ስራው ብዙ ስለሆነም ትእግስት እንደሚያስፈልግን አምነን መንግስትንም እራሳችንንም  መታገስ አለብን።