Thursday 11 October 2018

«ኢሳት ስለ ችግር አውርተው ሰማይ ተገለበጠ ብለው ያቆማሉ»

ዛሬ «ኢሳት ስለ ችግር አውርተው ሰማይ ተገለበጠ ብለው ያቆማሉ» አለችኝ እናቴ። ተስፋ የሚያስቆርጥ ነገር ላይ ለምን ያተኩራሉ አለች። እውነቷን ነው። ከኢሳት ተዕልኮ ጋር ይጋጫል። ሆኖም…

ኤርሚያስ ለገሰ በትላንቱ የኢሳት እለታዊ ፕሮግራም (https://youtu.be/mzQqTD-D2SM?t=2162) እንዳለው የወታደሮቹ አለ ቀጠሮ ወደ ቤተ መንግስት መሄዳቸው የህግ ወጥነት፤ ችልተኝነት፤ ስርዓትን አለማክበር፤ ስራ አለማክበር ወዘተ በሀገር እና መንግስት መብዛቱን የሚያሳይ አንድ ምሳሌ ነው። ችግር አለ ይቀጥላልም።

1. የ27/44 ወዘተ ዓመት ችግሮችን ለመፍታት እና ለማስተካከል ዓመታት ይፈጃል።
2. ስርዓትን በግዳጅ እና በፍርሃት ማቅበር የለመደ ሰው ግዳጁ እና ፍርሃቱ ሲቀሩ ልቅ ይሆናል።
3. የተለያዩ የህብረተሰባችን ክፍሎች ከነ ወታደሮች፤ አስተማሪዎች፤ ሰራተኞች ወዘተ ጥያቄዎቻቸው ለረዥም ዓመታት ተዳፍኖ በመቆየቱ አሁን ባንዴ ይፈነዳሉ።
4. አዲሱ መንግስት የማስፈራራት እና መረሸን ፍላጎት እንደሌለው ስለሚታወቅ የተለያዩ የህዝብ ክፍሎች ልቅ ሆነዋል።

ስለዚህ ተወያይቶ የተለያዩ መፍትሄዎች ማቅረቡ ጥሩ እና ገንቢ ነገር መሰለኝ። ከማማረር ይልቅ ተግባር!

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!