Monday 15 October 2018

የአዲስ አበባ ወጣቶቻችን፤ Nameless and faceless

ዛሬ በመሃበራዊ ሚዲያ ለ«ታፈሱት የአዲስ አበባ ወጣቶች» ፍትህ መጠየቂአ ቀን ይመስላል። ጥሩ እቅድ ነው።

ግን ማናቸው እነዚህ «ወጣቶች»? መስላቸው የት አለ? ስማቸውስ? ቤተሰቦቻቸው የት አሉ? ልጆች አላቸው ይሆን? ወላጆቻቸው የት ናቸው? እየተፈለጉ ነው ወይ? ማን ስለነሱ በየቤቱ እያለቀሰ ነው?

እኔ እስከመቀው ለነዚህ ጥያቄዎች መልስ የለንም። ለምን የለንም? እንዴት በመቶዎች ወይንም በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ታፍሰው ወደ ወታደራዊ ካምፕ ሲወሰዱ ምስላቸው፤ ስማቸው፤ ቤተሰቦቻቸው አይመዘገቡም? አዲስ አበባ የአምስት ሚሊዮን ህዝብ ከተማ ናት። ልጆቿ እንዲህ አይነት ነገር ሲደርስባት እንዴት ዝርዝሩን አናውቅም? ኤንዴንት ቤተሰቦቻቸው ወይንም ወኪሎቻቸው በተለያየ ሚዲያ ወጥተው እንዲታዩ ወይንም እንዲናገሩ አይደረግም? ለምንድነው faceless ሆነው የሚቀሩት?

ለነዚህ ጥያቄዎች መሰረታዊ ምክንያቱ የአዲስ አበባ እና የኢትዮጵያ ህዝብ እንደዚህ አይነት ጥቃቄዎችንም የሚያስተናግድ እና የሚመልሱ አቅም ያላቸው የፖለቲካ እና ማህበራዊ ተቋሞች ስለሌለው ነው! እነዚህ ወጣቶች ከተታፈሱ በኋላ ሁላቸውም ከነ ምስላቸው፤ ስማቸው እና ቤተሰቦቻቸው ተመዝግበው እንደ አግባቡ በሚድያ መቅረብ ነበረባቸው። ወጣቶቹን የሚመዘግብ፤ ሁኔታቸውን የሚከታተል፤ ሰለነሱ የሚሟገት እና የአዲስ አበባ ህዝብን ሰለ ጉዳያቸው የሚያሳውቅ ድርጅት ሊኖር ይገባ ነበር! የአምስት ሚሊዮን ከተማ ነው፤ ይህ ሊሳነው አይገባም።

ስለዚህ ይህ ነው መሰረታዊ ችግሩ/ችግራችን። አልተደራጀንም። መደራጀት ለህልውናችን ግድ ነው። ይህ መሰረታዊ ችግር ካልተፈታ ህመሞቻችን ይቀጥላሉ! (If we don't address the fundamental cause we'll keep running after the symptoms and never catch up)።

ስለዚህ ጉዳይ ሌላ ነገር ላንሳ። እስቲ ስንቶቻችን ነን የነዚህ ወጣቶችን ቤተሰቦች አይዝዋችሁ እያልን የምንገኘው? የሚያስፈልጋቸው እርዳታ ካለ የምናረግላቸው? ለባለንጀራዬ ካላሰብኩኝ ለምን ሌላው ያስባል ብዬ አስባለሁ። በችግር ጊዜ ካልደረስኩለት ምን አይነት መተማመን እና ትብብር ይኖረናል? ይህ ሌላ መሰረታዊ ችግር ነው። የእርስ በርስ ግንኙነታችን (social capital) መንኗል። ፍትህ እና ሰላም ከፈለግን ይህ መታደስ አለበት።

https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2016/09/blog-post_14.html

https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/09/blog-post_97.html

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!