Thursday 11 October 2018

የፌደራል መንግስት ዘመን አቆጣጠራችን (calendar) ይቀየር ይላሉ አቶ አብዱ አሊ ሂጅራ?!

ብስመ አብ! የፌደራል መንግስት ዘመን አቆጣጠራችን (calendar) ይቀየር ይላሉ አቶ አብዱ አሊ ሂጅራ?!

ከመአዛ አሸናፊ ጋር 10 ቀን በፊት ያደረጉትን ቋሚ ቃለ ምልልስ አሁን አዳመጥኩት (https://www.youtube.com/watch?v=s-ve5RiImNc)። ባጭሩ የቀን መቁጠርያችን እንደ ባህል እንጠብቀው፤ ለምሳሌ አዲስ አመትን አሁን እንደሚደረገው በመስከረም 1 ይከበር፤ ግን official ወይንም የመንግስት የቀን አቆጣጠር ወደ «ፈረንጁ» (Georgian calendar) አቆጣጠር ይቀየር። ምክነያቱ አብዛኛው ሀገራት በፈረንጁ አቆጣጠር ስለሚጠቀሙ በኢትዮጵያ አቆጣጠር መጠቀም ለበርካታ ስራ አይመችም። ሁልጊዜ ከአንዱ ወደ አንዱ መቀየር (convert) ስራን ያስተጓድላል አሉ አቶ አብዱ አሊ።

ይህ በብዞዎች ተቀባይነት ያለው አስተሳሰብ ነው። ግን ትክክል አይደለም… አይመስለኝም። ማንኛውም ትውፊታዊ ነገር እንደ ቀን መቁጠርያ እንደ «ባህል» ብቻ ይዘን በስራ ላይ ካልዋለ ቀስ ብሎ ይጠፋል! ለዚህም ነው ሀገራት የራሳቸውን ቋንቋ የሚጠብቁት። ከጃፓንኛ ወደ እንግሊዘኛ መከያየር ከባድ ስራ ነው። አብዛኛው የቴክኖሎጂ ነክ ነገሮች በእንግሊዘኛ ናቸው። ሆኖም ጃፓን በጃፓንኛ ቀልቋል። ያን ሁሉ ቴክኖሎሂ ነክ ስራዎችም ሲሰራ በጃፓንኛ ነው ያደረጉት። ድሮ የኮምፕዩተር ስራ በሌላ ቋንቋ መስራት በጣም ከባድ በሆነበት ዘመንም በጃፓንኛ ነበር የሰሩት። የማንነት ጉዳይ ስለሆነ እንደ ባህል አልትውትም። ሰሩበት አሁንም ይሰሩበታል። ይህ አስተያየት ለቋንቋ ብቻ ሳይሆን ለቀን መቁጠርያም ይሆናል።

በተዘዋዋሪ ኤርትራ የመንግስት የቀን መኩጠርያውን ሲቀይር እጅግ አዝኜ ነበር። ውጤቱ ዛሬ እና ነገ ይታያል እነ እንቁጣጣሽም እየተረሱ ይሄዳሉ።

ትንሽ ቃል ስለ ሃሳቡ ጠቅላላ መንፈስ ልጻፍ… ጣልያን ሀገር ብትሄዱ ሰንበት ሱቅ መከፈት የለበትም፤ እንደነ «ዎልማርት» አይነት ግዙፍ ሱቆች ሊኖሩ አይገባም፤ አማዞን ገደለን ወዘተ ይባላል። እነዚህ ነገሮች በማህበራዊ ኑሮ (including social capital)፤ ግለኝነት እና ብቸኝነት (individiualism and loneliness)፤ የትናንሽ ከተማ እና ሰፈር ህልውና፤ ወዘተ ላይ ያላቸው ሚና ይተቻሉ። ሁሉን ነገር 'rationalise' ማድረግ ጥቅም ብቻ ሳይሆን ጉዳትም እንዳሉእው ይታወቃል። በዚህ ምክንያት localism የሚባለው ርዕዮት ዓለም ባለፉት አስርት ዓመታት ወደ ልሂቃን መገናኛ ተመልሷል። ስለዚህ እንደዚህ አይነቱን ጉዳይ ላይላዩን ሳይሆን ጠልቀን መመርመር ይኖርብናል።

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!